PHPWord

 

 

حِصْنُ المُسْلِمِ

مِنْ أَذْكَارِ الكِتَابِ وَالسُّنَّةِ

 

 

 

 

የሙስሊም ምሽግ ከቁርኣንና ሐዲሥ የተውጣጡ ዚክሮች

 

 

 

 

 

د. سَعِيدُ بْنُ عَلِيِّ بْنِ وَهْفٍ الْقَحْطَانِيُّ

 

የላቀው አላህን እዝነት ከጃዩ

ዶ/ር ሰዒድ ቢን ዐሊይ ቢን ወህፍ አልቀሕጧኒይ

 

 


بِسْمِ اللهِ الرَّحمَنِ الرَّحِيمِ

የሙስሊም ምሽግ ከቁርኣንና ሐዲሥ የተውጣጡ ዚክሮች

በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው

መግቢያ

ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው፤ እናመሰግነዋለን፣ እገዛውን እንጠይቀዋለን፣ ምህረትንም እንለምነዋለን፤ ከነፍሳችን ክፋትና ከመጥፎ ስራችን በአላህ እንጠበቃለን፤ አላህ የመራውን የሚያጠም የለውም፤ ያጠመመውንም የሚመራ የለውም፤ ከአላህ ውጭ (በእውነት) የሚመለክ እንደሌለ ብቸኛና ተጋሪ የሌለው መሆኑን እመሰክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ ባሪያና መልክተኛ እንደሆኑ እመሰክራለሁ። የአላህ ሰላት በርሳቸው፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸውና እስከ ፍርዱ ቀን በመልካም በተከተላቸውም ላይ ይስፈን። የአላህ የበዛ ሰላምም ይስፈንባቸው። ከዚህ በመቀጠል፦

ይህ መጽሐፍ (አዝዚክሩ ወድዱዓኡ ወልዒላጁ ቢርሩቃ ሚነልኪታቢ ወስሱናህ) ከሚለው መጽሐፌ የተቀነጨበ ነው።1 በዚህ መጽሐፍ ውስጥ በጉዞ ላይ ለመያዝ ቀለል እንዲል ብዬ የአዝካርን ክፍል ብቻ ቀንጭቤያለሁ።

መትኑ ውስጥ በሚገኙ ዚክሮች ላይ ብቻ ተቆጥቤያለሁ፤ የግርጌ ማስታወሻን በተመለከተ በዋናው ኪታብ ውስጥ ከተገኙት መካከል አንድ ወይም ሁለት ምንጮችን ብቻ በመጥቀስ ተብቃቅቻለሁ። የሶሓቢውን ማንነት ማወቅ ወይም ተጨማሪ የግርጌ ማስታወሻን የፈለገ ሰው ወደ ዋናው መፅሀፍ ይመለስ። የላቀውንና የተከበረውን አላህ በውብ ስሞቹና ከፍ ባሉ ባህሪያቶቹ እየተማፀንኩ ይህን ስራ ለተከበረው ፊቱ ጥርት ተደርጎ የተሰራ እንዲያደርገው፤ እኔንም በሕይወቴም ሆነ ከሞትኩ በኋላ በእርሱ እንዲጠቅመኝ፤ ያነበበውን፣ ያሳተመውን ወይም ለማሰራጨት ሰበብ የሆነውን ሁሉ በእርሱ እንዲጠቅም እጠይቀዋለሁ። እነሆ ጥራት የተገባው እርሱ ለዚህ ረዳትና ቻይ ነውና። የአላህ ሰላትና ሰላም በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እና እስከ እለተ ትንሳኤ ቀን ድረስ በመልካም በተከተሏቸው ላይ ሁሉ ይስፈን።

አዘጋጅ

ጥንቅር በሶፈር ወር 1409 ዓ·ሂ

 


የዚክር ትሩፋት

የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦

﴿فَٱذۡكُرُونِيٓ أَذۡكُرۡكُمۡ وَٱشۡكُرُواْ لِي وَلَا تَكۡفُرُونِ 152﴾

"አስታውሱኝ አስታውሳችኋለሁና:: አመስግኑኝ አትካዱኝም::"2

﴿يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱذۡكُرُواْ ٱللَّهَ ذِكۡرٗا كَثِيرٗا41﴾

{እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ብዙ ማውሳትን አውሱት::}3

﴿...وَالذَّاكِرِينَ اللَّهَ كَثِيرًا وَالذَّاكِرَاتِ أَعَدَّ اللَّهُ لَهُم مَّغْفِرَةً وَأَجْرًا عَظِيمًا﴾

{… አላህን በብዙ አውሺ ወንዶችና አውሺ ሴቶችም አላህ ለእነርሱ ምህረትንና ታላቅን ምንዳ አዘጋጅቶላቸዋል።}4

﴿وَٱذۡكُر رَّبَّكَ فِي نَفۡسِكَ تَضَرُّعٗا وَخِيفَةٗ وَدُونَ ٱلۡجَهۡرِ مِنَ ٱلۡقَوۡلِ بِٱلۡغُدُوِّ وَٱلۡأٓصَالِ وَلَا تَكُن مِّنَ ٱلۡغَٰفِلِينَ 205﴾

{…(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ጌታህንም በሚስጥር ተናንሰህና ፈርተህ ከጩኸት በታች በሆነ ቃል በጠዋትና በማታ አውሳው:: ከዘንጊዎቹም አትሁን::}5

ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦

«مَثَلُ الَّذِي يَذْكُرُ رَبَّهُ، وَالَّذِي لَا يَذْكُرُ ربَّهُ، مَثَلُ الحَيِّ وَالمَيِّتِ».

«ጌታውን የሚያወሳና የማያወሳ ሰው ምሳሌ እንደ ህያውና እንደ ሞተ ሰው ምሳሌ ነው።»6

ነቢዩም የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦

«أَلَا أُنبِّئُكُم بِخَيْرِ أَعْمَالِكُمْ، وَأَزْكَاهَا عِنْدَ مَلِيكِكُمْ، وَأَرْفَعِهَا فِي دَرَجَاتِكُمْ، وَخَيْرٍ لَكُمْ مِنْ إِنْفَاقِ الذَّهَبِ وَالوَرِقِ، وَخَيْرٍ لَكُمْ مِنْ أَنْ تَلْقَوْا عَدُوَّكُمْ فَتَضْرِبُوا أَعْنَاقَهُمْ وَيَضْرِبُوا أَعْنَاقِكُم؟» قَالُوا بَلَى. «ذِكْرُ اللَّهِ تَعَالَى».

«በላጩን ሥራችሁ፣ ንጉሳችሁ ዘንድ የጠራችውን ሥራችሁ፣ ደረጃችሁንም ከፍ የምታደርገውን ስራችሁን፣ ለናንተ ወርቅና ብር ከመመፅወት የሚበልጥላችሁን ስራ፣ ጠላቶቻችሁን ተገናኝታችሁ አንገታቸውን ከምትመቱበት እነርሱም አንገታችሁን ከሚመቱበት ስራችሁ በላጩ የሆነውን ስራ አልነግራችሁምን?» ሶሐቦችም "እንዴታ!" አሉ። እርሳቸውም «አላህን ማውሳት ነው።» አሉ።"7

ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፦

«يَقُولُ اللَّهُ تَعَالَى: أَنَا عِنْدَ ظَنِّ عَبْدِي بِي، وَأَنَا مَعَهُ إِذَا ذَكَرَنِي، فَإِنْ ذَكَرَنِي فِي نَفْسِهِ، ذَكَرْتُهُ فِي نَفْسِي، وَإِنْ ذَكَرَنِي فِي مَلَأٍ ، ذَكَرْتُهُ فِي مَلَأٍ خَيْرٍ مِنْهُمْ، وَإِنْ تَقَرَّبَ إِلَيَّ شِبْرًا، تَقَرَّبْتُ إِلَيْهِ ذِرَاعًا، وَإِنْ تَقَرَّبَ إِلَيَّ ذِرَاعًا، تَقَرَّبْتُ إِلَيْهِ بَاعًا، وَإِنْ أَتَانِي يَمْشِي أَتَيْتُهُ هَرْوَلَةً».

«አላህ እንዲህ ብሏል: እኔ ባሪያዬ ባሰበኝ በኩል ነኝ። ባስታወሰኝም ጊዜ እኔ ከርሱ ጋር ነኝ። ለብቻው ካወሳኝ ለብቻዬ አወሳዋለሁ፤ በህብረት ካወሳኝ ደሞ ከነሱ የተሻለ በሆኑ ህብረቶች ዘንድ አወሳዋለሁ። አንድ ስንዝር ወደኔ ከቀረበ አንድ ክንድ ወደርሱ እቀርባለሁ። አንድ ክንድ ወደኔ ከቀረበ እጅ ሙሉ ወደርሱ እቀርባለሁ። እየተራመደ ወደኔ ከመጣ በሶምሶማ ወደርሱ እመጣለሁ።»8

ከዐብደላህ ቢን ቡስር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው «አንድ ሰውዬ እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! የእስልምና ድንጋጌዎች በርግጥም በኔ ላይ በዙብኝ። አጥብቄ የምይዘውን አንዳች ነገር ይንገሩኝ።" እርሳቸውም እንዲህ አሉ:

«لَا يَزَالُ لِسَانُكَ رَطْبًا مِنْ ذِكْرِ اللَّهِ».

«ምላስህ አላህን በማውሳት ከመርጠብ አይወገድ።»9

ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፡

«مَنْ قَرَأَ حَرْفًا مِنْ كِتَابِ اللَّهِ فَلَهُ بِهِ حَسَنَةٌ، وَالحَسَنَةُ بِعَشْرِ أَمْثَالِهَا، لَا أَقُولُ: ﴿الــم﴾ حَرْفٌ، وَلَكِنْ: أَلِفٌ حَرْفٌ، وَلَامٌ حَرْفٌ، وَمِيْمٌ حَرْفٌ».

«ከአላህ መፅሀፍ አንዲትን ፊደል የቀራ ሰው ለርሱ በእርሷ አንዲት ምንዳ ትመዘገብለታለች፤ አንዲት ምንዳ ደግሞ በአስር በአምሳያዋ ትባዛለች።﴿ አሊፍ ላም ሚም ﴾አንድ ፊደል ነው እያልኩ አይደለም። ነገር ግን፡ ‹አሊፍ› አንድ ፊደል ነው፣ ‹ላም› አንድ ፊደል ነው፣ ‹ሚም› አንድ ፊደል ነው።»10

ከዑቅበህ ቢን ዓሚር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «እኛ ሱፋ ላይ ሳለን የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ወጡና እንዲህ አሉ:

«أَيُّكُمْ يُحِبُّ أَنْ يَغْدُوَ كُلَّ يَوْمٍ إِلَى بُطْحَانَ، أَوْ إِلَى العَقِيقِ، فَيَأْتيَ مِنْهُ بِنَاقَتَيْنِ كَوْمَاوَيْنِ فِي غَيْرِ إِثْمٍ وَلَا قَطِيعَةِ رَحِمٍ؟»

«ከእናንተ ውስጥ ምንም ዓይነት ወንጀል ሳይሠራና ዝምድናንም ሳይቆርጥ በየቀኑ በማለዳ ወደ ቡጥሓን ወይም ወደ ዐቂቅ ሄዶ ሁለት ትልልቅ ሻኛ ያላቸውን ግመሎች ይዞ መምጣትን የሚወድ ማነው?" እኛም: "የአላህ መልእክተኛ ሆይ ይህንን እንወዳለን" አልን። እሳቸውም እንዲህ አሉ:

«أَفَلَا يَغْدُو أَحَدُكُمْ إِلَى المَسْجِدِ فَيَعْلَمَ، أَوْ يَقْرَأَ آيَتَيْنِ مِنْ كِتَابِ اللَّهِ عز وجل خَيْرٌ لَهُ مِنْ نَاقَتَيْنِ، وَثَلاثٌ خَيْرٌ لَهُ مِنْ ثَلَاثٍ، وَأَرْبَعٌ خَيْرٌ لَهُ مِنْ أَرْبَعٍ، وَمِنْ أَعْدَادِهِنَّ مِنَ الإِبِلِ».

«አንዳችሁ በማለዳ ወደ መስጂድ ወጥቶ ከአላህ ዐዘ ወጀል መጽሐፍ ሁለት አንቀፆችን ቢማር ወይም ቢያነብ ከሁለት ግመሎች ለሱ የተሻሉ ናቸው፤ ሶስት አንቀጾችም ከሶስት ግመሎች ለሱ የተሻሉ ናቸው፤ አራት አንቀጾችም ከአራት ግመሎች ለሱ የተሻሉ ናቸው፤ እንዲሁም በቁጥራቸው ልክ ከግመሎች የተሻሉ ናቸው።»11

ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፡

«مَنْ قَعَدَ مَقْعَدًَا لَمْ يَذْكُرِ اللَّهَ فِيهِ، كَانَتْ عَلَيْهِ مِنَ اللَّهِ تِرَةٌ، وَمَنِ اضْطَجَعَ مَضْجِعًا لَمْ يَذْكُرِ اللَّهَ فِيهِ كَانَتْ عَلَيْهِ مِنَ اللَّهِ تِرَةٌ».

«አላህን ሳያወሳበት አንድ ስፍራ ላይ የተቀመጠ ሰው ከአላህ ዘንድ በእርሱ ላይ ቁጭት ይሆንበታል። አላህን ሳያወሳበት አንድ መኝታ ላይ የተጋደመ ሰውም ከአላህ ዘንድ በእርሱ ላይ ቁጭት ይሆንበታል።»12

ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፡

«مَا جَلَسَ قَوْمٌ مَجْلِسًَا لَمْ يَذْكُرُوا اللَّهَ فِيهِ، وَلَمْ يُصَلُّوا عَلَى نَبِيِّهِمْ إِلَّا كَانَ عَلَيْهِمْ تِرَةً، فَإِنْ شَاءَ عذَّبَهُمْ، وَإِنْ شَاءَ غَفَرَ لَهُمْ».

«ሰዎች አላህን ያላወሱበትና በነቢያቸው ላይ ሶላት ያላወረዱበት መቀማመጥን ከተቀመጡ በነርሱ ላይ ቁጭት ይሆንባቸዋል። ከፈለገ ይቀጣቸዋል ከፈለገም ይምራቸዋል።»13

ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፦

«مَا مِنْ قَوْمٍ يَقُومُونَ مِنْ مَجْلِسٍ لَا يَذْكُرُونَ اللَّهَ فِيهِ إِلَّا قَامُوا عَنْ مِثْلِ جِيفَةِ حِمَارٍ، وَكَانَ لهُمْ حَسْرةً».

«ሰዎች በውስጧ አላህን ያላወሱበትን መሰባሰብን (ጨርሰው) አይነሱም። እንደ አህያ ሬሳ ሆነው ተነስተው እንደሚሄዱ አምሳያ ቢሆኑ ፣ (በስብሰባው አላህን ባለማውሳታቸው) በእነርሱ ላይ ጸጸት (ቁጭትን) ቢሆንባቸው እንጂ።»14

1. ከእንቅልፍ ሲነቁ የሚደረጉ ዚክሮች (ውዳሴዎች)

«الحَمْدُ للَّهِ الَّذِي أَحْيَانَا بَعْدَ مَا أَمَاتَنَا، وَإِلَيْهِ النُّشُورُ».

«ህይወታችንን በከፊል ከወሰደ በኋላ ነፍስ ለዘራብን (እንድንነቃ ላደረገን) አላህ ምስጋና ይገባው፤ ወደርሱም ተጓዦች ነን»15

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَريكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ، وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ، سُبْحَانَ اللَّهِ، وَالحَمْدُ للَّهِ، وَلَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَاللَّهُ أَكبَرُ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ العَلِيِّ العَظِيمِ، رَبِّ اغْفرْ لِي».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው፤ አጋር የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው። አላህ ጥራት የተገባው ነው። ምስጋናም ለአላህ ነው። ከአላህም በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። አላህም ታላቅ ነው። ልዑልና ታላቅ በሆነው በአላህ ቢሆን እንጅ ብልሃትም ሆነ ሃይል የለም። ጌታዬ ሆይ! ማረኝ።» 16

«الحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي عَافَانِي فِي جَسَدِي، وَرَدَّ عَلَيَّ رُوحِي، وَأَذِنَ لِي بِذِكْرِهِ».

«በአካሌ ላይ ጤንነትን ለሰጠኝ፣ ነፍሴን ለመለሰልኝና እርሱን እንዳወሳ ለፈቀደልኝ አላህ ምስጋና ይገባው።»17

﴿إِنَّ فِي خَلۡقِ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَٱخۡتِلَٰفِ ٱلَّيۡلِ وَٱلنَّهَارِ لَأٓيَٰتٖ لِّأُوْلِي ٱلۡأَلۡبَٰبِ 190 ٱلَّذِينَ يَذۡكُرُونَ ٱللَّهَ قِيَٰمٗا وَقُعُودٗا وَعَلَىٰ جُنُوبِهِمۡ وَيَتَفَكَّرُونَ فِي خَلۡقِ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ رَبَّنَا مَا خَلَقۡتَ هَٰذَا بَٰطِلٗا سُبۡحَٰنَكَ فَقِنَا عَذَابَ ٱلنَّارِ 191 رَبَّنَآ إِنَّكَ مَن تُدۡخِلِ ٱلنَّارَ فَقَدۡ أَخۡزَيۡتَهُۥۖ وَمَا لِلظَّٰلِمِينَ مِنۡ أَنصَارٖ192 رَّبَّنَآ إِنَّنَا سَمِعۡنَا مُنَادِيٗا يُنَادِي لِلۡإِيمَٰنِ أَنۡ ءَامِنُواْ بِرَبِّكُمۡ فَـَٔامَنَّاۚ رَبَّنَا فَٱغۡفِرۡ لَنَا ذُنُوبَنَا وَكَفِّرۡ عَنَّا سَيِّـَٔاتِنَا وَتَوَفَّنَا مَعَ ٱلۡأَبۡرَارِ 193 رَبَّنَا وَءَاتِنَا مَا وَعَدتَّنَا عَلَىٰ رُسُلِكَ وَلَا تُخۡزِنَا يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِۖ إِنَّكَ لَا تُخۡلِفُ ٱلۡمِيعَادَ 194 فَٱسۡتَجَابَ لَهُمۡ رَبُّهُمۡ أَنِّي لَآ أُضِيعُ عَمَلَ عَٰمِلٖ مِّنكُم مِّن ذَكَرٍ أَوۡ أُنثَىٰۖ بَعۡضُكُم مِّنۢ بَعۡضٖۖ فَٱلَّذِينَ هَاجَرُواْ وَأُخۡرِجُواْ مِن دِيَٰرِهِمۡ وَأُوذُواْ فِي سَبِيلِي وَقَٰتَلُواْ وَقُتِلُواْ لَأُكَفِّرَنَّ عَنۡهُمۡ سَيِّـَٔاتِهِمۡ وَلَأُدۡخِلَنَّهُمۡ جَنَّٰتٖ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ ثَوَابٗا مِّنۡ عِندِ ٱللَّهِۚ وَٱللَّهُ عِندَهُۥ حُسۡنُ ٱلثَّوَابِ 195 لَا يَغُرَّنَّكَ تَقَلُّبُ ٱلَّذِينَ كَفَرُواْ فِي ٱلۡبِلَٰدِ 196 مَتَٰعٞ قَلِيلٞ ثُمَّ مَأۡوَىٰهُمۡ جَهَنَّمُۖ وَبِئۡسَ ٱلۡمِهَادُ 197 لَٰكِنِ ٱلَّذِينَ ٱتَّقَوۡاْ رَبَّهُمۡ لَهُمۡ جَنَّٰتٞ تَجۡرِي مِن تَحۡتِهَا ٱلۡأَنۡهَٰرُ خَٰلِدِينَ فِيهَا نُزُلٗا مِّنۡ عِندِ ٱللَّهِۗ وَمَا عِندَ ٱللَّهِ خَيۡرٞ لِّلۡأَبۡرَارِ 198 وَإِنَّ مِنۡ أَهۡلِ ٱلۡكِتَٰبِ لَمَن يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ وَمَآ أُنزِلَ إِلَيۡكُمۡ وَمَآ أُنزِلَ إِلَيۡهِمۡ خَٰشِعِينَ لِلَّهِ لَا يَشۡتَرُونَ بِـَٔايَٰتِ ٱللَّهِ ثَمَنٗا قَلِيلًاۚ أُوْلَٰٓئِكَ لَهُمۡ أَجۡرُهُمۡ عِندَ رَبِّهِمۡۗ إِنَّ ٱللَّهَ سَرِيعُ ٱلۡحِسَابِ 199 يَٰٓأَيُّهَا ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ ٱصۡبِرُواْ وَصَابِرُواْ وَرَابِطُواْ وَٱتَّقُواْ ٱللَّهَ لَعَلَّكُمۡ تُفۡلِحُونَ 200﴾

{በሰማያትና በምድር መፈጠር፤ በሌሊትና በቀንም መተካካት ለባለ አእምሮዎች ሁሉ ታላላቅ ምልክቶች አሉት።(190)

እነርሱም እነዚያ ቆመው ተቀምጠዉም በጎኖቻቸው ተጋድመዉም አላህን የሚያወሱ በሰማያትና በምድር አፈጣጠርም የሚያስተነትኑና (እንዲህም) የሚሉ ናቸው: «ጌታችን ሆይ! ይህን በከንቱ አልፈጠርከዉም ጥራት ይገባህ:: ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን። (191)

ጌታችን ሆይ! አንተ እሳት የምታስገባው ሰው ሁሉ በእርግጥ አዋረድከው:: ለበደለኞች ምንም ረዳቶች የሏቸዉም። (192)

ጌታችን ሆይ! እኛ በጌታችሁ እመኑ በማለት ወደ እምነት የሚጠራን ጠሪ ሰማንና ወዲያዉኑ አመንም::ጌታችን ሆይ! ኃጢአቶቻችንንም ማርልን ክፉ ስራዎቻችንንም አብስልን:: ከንጹሆች ሰዎች ጋርም ግደለን:: (193)

ጌታችን ሆይ! በመልዕክተኞቹ አማካኝነት የሰጠኸንን፤ የገባህልንን የተስፋ ቃል ስጠን:: በትንሳኤ ቀንም አታዋርደን:: (አታሳፍረን::) አንተ ቀጠሮን አታፈርስምና።» (194)

እናም ጌታቸው «እኔ ከናንተ ውስጥ የወንድንም ሆነ የሴትን መልካም ስራ ወሮታ አላጠፋም:: ከፊላችሁ የከፊሉ አካል ነው።» በማለት ልመናቸውን ተቀበላቸው:: እነዚያ ለዲን ሲሉ የተሰደዱ፣ ከአገሮቻቸዉም በግፍ የተባረሩ፣ በመንገዴም (ሁከት የደረሰባቸው)፣ የተጠቁ፣ የተጋደሉ እና የተገደሉም ክፉ ስራዎቻቸውን አብስላቸዋለሁ:: በስሮቻቸዉም ወንዞች የሚፈሰባቸውን ገነቶች አስገባቸዋለሁ:: እነርሱም ከአላህ ዘንድ የሆነን ከፍተኛ ምንዳ ይመነዳሉ:: አላህ እርሱ ዘንድ መልካም ምንዳ አለና:: (195)

(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) የእነዚያ በአላህ የካዱ ሰዎች በየአገሮች መንፈላሰስ አያታልህ። (196)

አነስተኛ ጥቅም ነው። ከዚያ መኖሪያቸው ገሀነም ናት:: ገሀነም ደግሞ ማረፊያነቷ ምን ትከፋ! (197)

እነዚያ ጌታቸውን የፈሩት ግን ከስሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች በውስጧ ዘወታሪዎች ሲሆኑ አላህ ዘንድ የተሰጡ መስተንግዶዎች አሏቸው:: አላህ ዘንድ ያለውም ምንዳ ለበጎ ሰሪዎች ሁሉ በላጭ ነው:: (198)

ከመጽሐፉ ባለቤቶች መካከል አላህን ፈሪዎችና በአላህ አናቅጽም ጥቂትን ዋጋ የማይለውጡ ሲሆኑ በአላህና በዚያ ወደ እናንተ በተወረደው ቁርኣን በዚያም ወደ እነርሱ በተወረዱት ልዩ ልዩ መጽሐፍት የሚያምኑ ሰዎች አሉ:: እነዚያ ለእነርሱ በጌታቸው ዘንድ ተገቢው ምንዳቸው አለላቸው አላህ ምርመራው ፈጣን ነው:: (199)

እናንተ ያመናችሁ ሆይ! ከእሳት ቅጣት ትድኑ ዘንድ ታገሱ፣ ተበራቱም፣ በጦር ኬላ ላይ ሆናችሁም ሶላትን ተጠባበቁ:: አላህንም በትክክል ፍሩ:: (200)}

[አሊ-ዒምራን: 190-200]18

2. ልብስ ሲለበስ የሚባል ዱዓእ

«الحَمْدُ للَّهِ الَّذِي كَسَانِي هَذَا (الثَّوْبَ) وَرَزَقَنِيهِ مِنْ غَيْرِ حَوْلٍ مِنِّي وَلَّا قُوَّة...».

«ትርጉሙም፡ «የኔ አቅም ወይም ብልሀት ሳይታከልበት ይህንን (ልብስ) እንድለብስ ላደረገኝ አላህ ምስጋና ተገባው...»19

3. አዲስ ልብስ ሲለበስ የሚባል ዱዓእ

«اللَّهُمَّ لَكَ الحَمْدُ أَنْتَ كَسَوْتَنِيهِ، أَسْأَلُكَ مِنْ خَيْرِهِ وَخَيْرِ مَا صُنِعَ لَهُ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّهِ وَشَرِّ مَا صُنِعَ لَهُ».

«አላህ ሆይ! አልብሰኸኛልና ምስጋና ላንተ ይሁን። ከመልካምነቱና ከተሰራበት መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። ከክፋቱና ከተሰራበት ክፋትም ጥበቃህን እሻለሁ።»20

4. አዲስ ልብስ ለለበሰ ሰው የሚደረግ ዱዓእ

«تُبْلِي وَيُخْلِفُ اللَّهُ تَعَالَى».

«ልብሱ ተጠቅመህበት ይለቅ፤ አላህ (ሌላ ልብስ) ይተካልህ።»21

«اِلبَسْ جَدِيدًا، وَعِشْ حَمِيدًا، وَمُتْ شَهِيدًا».

«አዲስ ልበስ፣ ምስጉን ሆነህ ኑር፣ ሸሂድ ሆነህ ሙት»22

5. ልብስ ሲያወልቁ የሚባል ዱዓእ

«بِسْمِ اللَّه».

«በአላህ ስም" ማለት ነው።»23

6. ወደ መፀዳጃ ቤት ሲገባ የሚባል ዱዓእ

«[بِسْمِ اللَّهِ] اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ الخُبْثِ وَالخَبَائِثِ».

«[በአላህ ስም] አላህ ሆይ! ከወንድም ሆነ ከሴት ሸይጣን ባንተ እጠበቃለሁ።»24.

7 - ከመጸዳጃ ቤት ሲወጣ የሚባለው ዱዓእ

«غُفْرَانَكَ».

«ትርጉም፡ ጌታዬ ሆይ ማረኝ».25

8. ከዉዱእ በፊት የሚባል ዚክር

«بِسْمِ اللَّهِ».

«በአላህ ስም" ማለት ነው።»26

9. ዉዱእ ካጠናቀቁ በኋላ የሚባል ዚክር

«أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ وَأَشْهَدُ أَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُهُ وَرَسُولُهُ..».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ እንደሌለና ተጋሪ የሌለው ብቸኛ መሆኑን እመስክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ መልዕክተኛው እና ባሪያው መሆናቸውንም እመስከራለሁ..»27

«اللَّهُمَّ اجْعَلْنِي مِنَ التَّوَّابِينَ وَاجْعَلْنِي مِنَ المُتَطَهِّرِينَ».

«አላህ ሆይ! ከኃጢአት በንሰሀ ተመላሽ ከሆኑት ሰዎች ጎራ አድርገኝ፤ ከተጥራሪዎች (ራሳቸውን በብዛት ከሚያጸዱ) ሰዎች ጭፍራም አድርገኝ።»28

«سُبْحانَكَ اللَّهُمَّ وَبِحَمْدِكَ، أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، أَسْتَغْفِرُكَ وَأَتوبُ إِلَيْكَ».

«አላህ ሆይ! ጥራት ላንተ የተገባ ነው፤ ምስጋናም ላንተ ይሁን፤ ካንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እመሰክራለሁ፤ ምሕረትህንም እለምንሃለሁ፤ ከኃጢኣቴ ተጸጽቼ ወደ አንተ እመለሳለሁ፡፡»29

10. ከቤት ሲወጣ የሚባለው ዚክር

«بِسْمِ اللَّهِ، تَوَكَّلْتُ عَلَى اللَّهِ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّّا بِاللَّهِ».

«በአላህ ስም፤ በአላህ ተመካሁ። በአላህ ካልሆነ በቀርም ምንም ኃይልም ብልሀትም የለም።»30

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ أَنْ أَضِلَّ، أَوْ أُضَلَّ، أَوْ أَزِلَّ، أَوْ أُزَلَّ، أَوْ أَظْلِمَ، أَوْ أُظْلَمَ، أَوْ أَجْهَلَ، أَوْ يُجْهَلَ عَلَيَّ».

«አላህ ሆይ! እኔ ከመጥመም ወይም ከማጥመም ወይም ወንጀል ላይ ከመውደቅ ወይም ሌላን ወንጀል ላይ ከመጣል ወይም ከመበደል ወይም ከመብበደል ወይም የመሃይማን ስራ ከመስራት ወይም የመሃይማን ስራ እኔ ላይ ከሚሰራብኝ ባንተ እጠበቃለሁ።»31

11. ወደ ቤት ሲገቡ የሚባለው ዚክር

«بِسْمِ اللَّهِ وَلَجْنَا، وَبِسْمِ اللَّهِ خَرَجْنَا، وَعَلَى اللَّهِ رَبِّنَا تَوَكَّلْنَا، ثُمَّ لِيُسَلِّمْ عَلَى أَهْلِهِ».

«በአላህ ስም ገባን፤ በአላህም ስም ወጣን፤ የምንመካውም በአላህ ነው።) ከዚያም ቤተሰቡን ሰላምታ ይስጥ።»32

12. ወደ መስጂድ ሲኬድ የሚባለው ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اجْعَلْ فِي قَلْبِي نُورًا، وَفِي لِسَانِي نُورًا، وَفِي سَمْعِي نُورًا، وَفِي بَصَرِي نُورًا، وَمِنْ فَوْقِي نُورًا، وَمِنْ تَحْتِي نُورًا، وَعَنْ يَمِينِي نُورًا، وَعَنْ شِمَالِي نُورًا، وَمِنْ أَمَامِي نُورًا، وَمِنْ خَلْفِي نُورًا، وَاجْعَلْ فِي نَفْسِي نُورًا، وَأَعْظِمْ لِي نُورًا، وَعَظِّمْ لِي نُورًا، وَاجْعَلْ لِي نُورًا، وَاجْعَلْنِي نُورًا، اللَّهُمَّ أَعْطِنِي نُورًا، وَاجْعَلْ فِي عَصَبِي نُورًا، وَفِي لَحْمِي نُورًا، وَفِي دَمِي نُورًا، وَفِي شَعْرِي نُورًا، وَفِي بَشَرِي نُورًا».

«አላህ ሆይ! በልቤ ውስጥ ብርሀን አድርግልኝ ፤ በምላሴም ብርሀን ፤ በመስሚያዬም ብርሀን ፤ በማያዬም ብርሀን ፤ ከበላዬም ብርሀን ፤ ከበታቼም ብርሀን ፤ ከቀኜም ብርሀን ፤ ከግራዬም ብርሀን ፤ ከፊቴም ብርሀን ፤ ከኋላዬም ብርሀን ፤ በነፍሴም ውስጥ ብርሀን አድርግልኝ ፤ ብርሀንንም ታላቅ አድርግልኝ ፤ ብርሀንንም አሳድግልኝ ፤ ለኔም ብርሀን አድርግልኝ ፤ እኔንም ብርሀን አድርገኝ ፤ አላህ ሆይ! ብርሀንን ስጠኝ ፤ በጅማቴም ውስጥ ብርሀን አድርግልኝ ፤ በስጋዬም ብርሀን ፤ በደሜም ብርሀን፤ በፀጉሬም ብርሀን ፤ በቆዳዬም ብርሀን አድርግልኝ።»33

«اللَّهُمَّ اجْعَلْ لِي نُورًا فِي قَبْرِي... وَنُورًا فِي عِظَامِي» «وَزِدْنِي نُورًا، وَزِدْنِي نُورًا، وَزِدْنِي نُورًا» «وَهَبْ لِي نُورًا عَلَى نُورٍ».

«አላህ ሆይ! በቀብሬ ውስጥ ብርሃንን አድርግልኝ... በአጥንቶቼም ውስጥ ብርሃንን አድርግልኝ34፤ ብርሃንንም ጨምርልኝ፣ ብርሃንንም ጨምርልኝ፣ ብርሃንንም ጨምርልኝ35፤ በብርሃን ላይ ብርሃንንም ለግሰኝ36፡፡»

13. መስጂድ ሲገባ የሚባለው ዱዓእ

(ቀኝ እግሩን ያስቀድማል)37፣ እንዲህም ይላል፦

«أَعُوذُ بِاللَّهِ العَظِيمِ، وَبِوَجْهِهِ الكَرِيمِ، وَسُلْطَانِهِ القَدِيمِ، مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ»

«በታላቁ አላህ፣ በክቡር ፊቱም እንዲሁም ከጥንት በነበረው ስልጣኑም ከተረገመው ሰይጣን እጠበቃለሁ።"38

«بِسْمِ اللَّهِ، وَالصَّلَاةُ» «وَالسَّلَامُ عَلَى رَسُولِ اللَّهِ»

«በአላህ ስም፤ የአላህ እዝነትና››39 ‹‹ሰላም በአላህ መልዕክተኛ ላይ ይሁን።»40

«اللَّهُمَّ افْتَحْ لِي أَبْوَابَ رَحْمَتِكَ».

«አላህ ሆይ! የእዝነት ደጆችህን ክፈትልኝ፡፡»41

14. ከመስጂድ ሲወጣ የሚባለው ዱዓእ

(ግራ እግሩን ያስቀድማል)42 እንዲህም ይላል፦

«بِسْمِ اللَّهِ وَالصَّلَاةُ وَالسَّلَامُ عَلَى رَسُولِ اللَّهِ،

«በአላህ ስም፤ የአላህ ሰላትና ሰላም በአላህ መልእክተኛ ላይ ይስፈን፣

اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ مِنْ فَضْلِك،

«አላህ ሆይ! ከችሮታህ እንድትለግሰኝ እማፀንሀለሁ።"

اللَّهُمَّ اعْصِمْنِي مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ».

«አላህ ሆይ! ከተረገመው ሰይጣን ጠብቀኝ።»43

15. የአዛን አዝካሮች

ልክ ሙአዚኑ የሚለውን አምሳያ ይላል፤ "ሐየ ዐለ ሰላህ" እና "ሐየ ዐለል ፈላሕ" ሲል ግን እንዲህ ይላል፡

«لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ».

«በአላህ ካልሆነ በስተቀር ምንም ኃይልና ዘዴ የለም።»44

እንዲህም ይላል:

«وَأَنَا أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُهُ وَرَسُولُهُ، رَضِيتُ بِاللَّهِ رَبًَّا، وَبِمُحَمَّدٍ رَسُولًا، وَبِالإِسْلَامِ دِينًَا».

«እኔም ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚገዙት አምላክ እንደሌለና ተጋሪ የሌለው ብቸኛ መሆኑን እመሰክራለሁ፤ ሙሐመድም መልእክተኛው እና ባሪያው መሆናቸውንም እመሰክራለሁ፤ በአላህ ጌትነት፣ በሙሐመድ መልእክተኛነትና በእስልምና ሃይማኖትነት ወደድኩ።»45

(ይህን የሚለው ከአዛን አድራጊው ተሸሁድ በኋላ ነው)46

(ለሙአዚን መልስ መስጠቱን ካጠናቀቀ በኋላ በነቢዩ ﷺ ላይ ሰለዋት ያወርዳል)47

እንዲህ ይላል:

«اللَّهُمَّ رَبَّ هَذِهِ الدَّعْوَةِ التَّامَّةِ، وَالصَّلَاةِ القَائِمَةِ، آتِ مُحَمَّدًا الوَسِيلَةَ وَالفَضِيلَةَ، وَابْعَثْهُ مَقَامًَا مَحمُودًا الَّذِي وَعَدْتَهُ، [إِنَّكَ لَا تُخْلِفُ المِيعَادَ]».

«የዚህ የተሟላ ጥሪና የተቋቋመው ሶላት ጌታ አላህ ሆይ! (ነቢዩ) ሙሐመድን "ወሲላ" እና "ፈዲላ"ን ለግሳቸው፤ ቃል በገባህላቸው ምስጉን ስፍራም ቀስቅሳቸው። [እነሆ አንተ ቃልህን አታጥፍምና።])»48

(በአዛንና በኢቃማ መካከል ለነፍሱ ዱዓ ያደርጋል፤ ምክንያቱም በዛ ሰአት የተደረገ ዱዓእ አይመለስምና።)49

16. የመክፈቻ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ بَاعِدْ بَيْنِي وَبَيْنَ خَطَايَايَ كَمَا بَاعَدْتَ بَيْنَ المَشْرِقِ وَالمَغْرِبِ، اللَّهُمَّ نَقِّنِي مِنْ خَطَايَايَ كَمَا يُنَقَّى الثَّوْبُ الأَبْيَضُ مِنَ الدَّنَسِ، اللَّهُمَّ اغْسِلْني مِنْ خَطَايَايَ، بِالثَّلْجِ وَالماءِ وَالبَرَدِ».

«አላህ ሆይ! በምሥራቅና በምዕራብ መካከል እንዳራራቅከው እኔንም ከወንጀሌ አርቀኝ፤ አላህ ሆይ! ነጭ ልብስ ከቆሻሻዎች እንደሚጸዳው እኔንም ከወንጀሌ አጥራኝ፤ አላህ ሆይ! እኔን ከወንጀሌ በውሃ እና በጤዛም በበረዶም እጠበኝ።»50

«سُبْحانَكَ اللَّهُمَّ وَبِحَمْدِكَ، وَتَبارَكَ اسْمُكَ، وَتَعَالَى جَدُّكَ، وَلَا إِلَهَ غَيْرُكَ».

«አላህ ሆይ! ጥራት ከምስጋና ጋር ላንተ የተገባ ነው፤ ስምህ የተባረከ ነው፤ ግርማህም ከፍ ያለ ነው፤ ካንተ በቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው የለም።»51

«وَجَّهْتُ وَجْهِيَ لِلَّذِي فَطَرَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضَ حَنِيفًَا وَمَا أَنَا مِنَ المُشْرِكِينَ، إِنَّ صَلَاتِي، وَنُسُكِي، وَمَحْيَايَ، وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ العَالَمِينَ، لَا شَرِيكَ لَهُ وَبِذَلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا مِنَ المُسْلِمِينَ، اللَّهُمَّ أَنْتَ المَلِكُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، أَنْتَ رَبِّي وَأَنَا عَبْدُكَ، ظَلَمْتُ نَفْسِي وَاعْتَرَفْتُ بِذَنْبِي فَاغْفِرْ لِي ذُنُوبي جَمِيعًَا إِنَّهُ لَا يَغْفِرُ الذُّنوبَ إِلَّا أَنْتَ، وَاهْدِنِي لِأَحْسَنِ الأَخْلاقِ لَا يَهْدِي لِأَحْسَنِها إِلَّا أَنْتَ، وَاصْرِفْ عَنِّي سَيِّئَهَا، لَا يَصْرِفُ عَنِّي سَيِّئَهَا إِلَّا أَنْتَ، لَبَّيْكَ وَسَعْدَيْكَ، وَالخَيْرُ كُلُّهُ بِيَدَيْكَ، وَالشَّرُّ لَيْسَ إِلَيْكَ، أَنَا بِكَ وَإِلَيْكَ، تَبارَكْتَ وَتَعَالَيْتَ، أَسْتَغْفِرُكَ وَأَتوبُ إِلَيْكَ».

«ፊቴን ለዚያ ሰማያትንና ምድርን ለፈጠረው (አምላክ) ቀጥተኛ ስሆን አዞርኩ እኔም ከአጋሪዎቹ አይደለሁም ስግደቴም መገዛቴም ህይወቴም ሞቴም ለአለማት ጌታ ለአላህ ነው ለእርሱ ተጋሪ የለውም በዚህም ታዘዝኩ እኔም ከሙስሊሞች ነኝ። አላህ ሆይ! አንተ ንጉሥ ነህ፤ ከአንተ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም፤ አንተ ጌታዬ ነህ እኔም ባሪያህ ነኝ፤ ነፍሴን በደልኩ በወንጀሌም አመንኩ፤ ወንጀሎቼን በሙሉ ማረኝ! እነሆ ካንተ በቀር ወንጀሎችን የሚምር የለምና። ወደ መልካም ስነ-ምግባርም ምራኝ፤ ወደ መልካሟ ካንተ በቀር የሚመራ የለምና። መጥፎዋንም ከእኔ ላይ መልስልኝ፤ መጥፎዋን ካንተ በቀር የሚመልስ የለምና። ጥሪህን ተቀብዬ ታዝዤሃለሁ፤ መልካም ነገር ሁሉ በእጆችህ ነው፤ ክፋትም ወዳንተ አይጠጋም፤ እኔ ባንተ ነኝ ወዳንተም ነኝ፤ ክብርህ ላቀ፤ ከፍም አልክ፤ ምህረትን እጠይቅሃለሁ ወዳንተም እመለሳለሁ።»52

«اللَّهُمَّ رَبَّ جِبْرَائِيلَ، وَمِيْكَائِيلَ، وَإِسْرَافِيلَ، فَاطِرَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ، عَالِمَ الغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ أَنْتَ تَحْكُمُ بَيْنَ عِبَادِكَ فِيمَا كَانُوا فِيهِ يَخْتَلِفُونَ، اهْدِنِي لِمَا اخْتُلِفَ فِيهِ مِنَ الحَقِّ بِإِذْنِكَ إِنَّكَ تَهْدِي مَنْ تَشَاءُ إِلَى صِرَاطٍ مُسْتَقيمٍ».

«የጂብራኢል፣ የሚካኢልና የኢስራፊል ጌታ፣ ሰማያትንና ምድርን የፈጠርክ ሩቁንም ቅርቡንም ዐዋቂ የኾንክ አላህ ሆይ! አንተ በባሮችህ መካከል በእዚያ በእርሱ ይለያዩበት በነበሩት ነገር ትፈርዳለህ። ከእውነት በርሱ ለተለያዩበት በፍቃድህ ምራኝ። አንተ የምትሻውን ሰው ወደ ቀጥተኛው መንገድ ትመራለህ።»53

«اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيرًَا، اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيرًا، اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيرًا، وَالحَمْدُ لِلَّهِ كَثيرًا، وَالحَمْدُ لِلَّهِ كَثيرًا، وَالحَمْدُ لِلَّهِ كَثيرًا، وَسُبْحَانَ اللَّهِ بُكْرَةً وَأَصِيلًا».

«አላህ እጅግ በጣም ታላቅ ነው፤ አላህ እጅግ በጣም ታላቅ ነው፤ አላህ እጅግ በጣም ታላቅ ነው። ለአላህም ብዙ ምስጋና ይገባው፤ ለአላህም ብዙ ምስጋና ይገባው፤ ለአላህም ብዙ ምስጋና ይገባው። በጠዋትም በማታም ለአላህ ጥራት ይገባው።»

ሦስት ጊዜ

«أَعُوذُ بِاللَّهِ مِنَ الشَّيْطَانِ: مِنْ نَفْخِهِ، وَنَفْثِهِ، وَهَمْزِهِ».

«ከሰይጣን፤ ከኩራቱ፣ ከድግምቱና ከጉትጎታው በአላህ እጠበቃለሁ።»54

«اللَّهُمَّ لَكَ الحَمْدُ، أَنْتَ نُورُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ وَمَنْ فِيهِنَّ، وَلَكَ الحَمْدُ أَنْتَ قَيِّمُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ وَمَنْ فِيهِنَّ، [وَلَكَ الحَمْدُ أَنْتَ رَبُّ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ وَمَنْ فِيهِنَّ] [وَلَكَ الحَمْدُ لَكَ مُلْكُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ وَمَنْ فِيهِنَّ] [وَلَكَ الحَمْدُ أَنْتَ مَلِكُ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ] [وَلَكَ الحَمْدُ] [أَنْتَ الحَقُّ، وَوَعْدُكَ الحَقُّ، وَقَوْلُكَ الحَقُّ، وَلِقاؤُكَ الحَقُّ، وَالجَنَّةُ حَقٌّ، وَالنَّارُ حَقٌّ، وَالنَّبِيُّونَ حَقٌّ، وَمحَمَّدٌ ﷺ حَقٌّ، وَالسَّاعَةُ حَقٌّ] [اللَّهُمَّ لَكَ أَسْلَمتُ، وَعَلَيْكَ تَوَكَّلْتُ، وَبِكَ آمَنْتُ، وَإِلَيْكَ أَنَبْتُ، وَبِكَ خاصَمْتُ، وَإِلَيْكَ حاكَمْتُ. فَاغْفِرْ لِي مَا قَدَّمْتُ، وَمَا أَخَّرْتُ، وَمَا أَسْرَرْتُ، وَمَا أَعْلَنْتُ] [وَمَا أَنْتَ أَعْلَمُ بِهِ مِنِّي] [أَنْتَ المُقَدِّمُ، وَأَنْتَ المُؤَخِّرُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ] [أَنْتَ إِلَهِي لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ] [وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ]».

«አላህ ሆይ! ምስጋና ሁሉ ላንተ የተገባ ነው55፤ አንተ የሰማያትና የምድር በውስጣቸውም ላለው ሁሉ ብርሃን ነህ፤ ምስጋናም ላንተ የተገባ ነው፤ አንተ የሰማያትና የምድር በውስጣቸውም ላለው ሁሉ አስተናባሪ ነህ፤ [ምስጋናም ላንተ የተገባ ነው፤ አንተ የሰማያትና የምድር በውስጣቸውም ላለው ሁሉ ጌታ ነህ፤] [ምስጋናም ላንተ የተገባ ነው፤ የሰማያትና የምድር በውስጣቸውም ላለው ሁሉ ንግስና ላንተ ብቻ ነው፤] [ምስጋናም ላንተ የተገባ ነው፤ አንተ የሰማያትና የምድር ንጉስ ነህ፤] [ምስጋናም ላንተ የተገባ ነው፤] [አንተ እውነት ነህ፤ ቀጠሮህም እውነት ነው፤ ቃልህም እውነት ነው፤ ከአንተ ጋር መገናኘትም እውነት ነው፤ ጀነት እውነት ነው፤ እሳትም እውነት ነው፤ ነቢያትም እውነት ናቸው፤ ሙሐመድም ﷺ እውነት ናቸው፤ ሰዓቲቱም እውነት ናት።] [አላህ ሆይ! ላንተ እጅ ሰጥቻለሁ፤ ባንተ ላይ ተመክቻለሁ፤ ባንተ አምኛለሁ፤ ወደ አንተም ተመልሻለሁ፤ ባንተም ተከራክሬያለሁ፤ ወዳንተም አቤት ብያለሁ። ስለዚህ ያሳለፍኩትንም ሆነ ያቆየሁትን፣ የደበቅኩትንም ሆነ ይፋ ያደረግኩትን ማረኝ፤] [እኔ ከማውቀው በላይ አንተ የምታውቀውንም ጭምር፤] [አንተ አሳላፊ ነህ፤ አንተ አዘግዪ ነህ፤ ካንተ በቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው የለም፤] [አንተ አምላኬ ነህ፤ ካንተ በቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው የለም፤] [ከአላህ በስተቀር ብልሃትም ሆነ ኃይል የለም።]")56

17 - የሩኩዕ ዱዓእ

«سُبْحانَ رَبِّيَ العَظِيمِ».

«ለኃያሉ ጌታዬ ጥራት (ልቅና) ተገባው።»

ሦስት ጊዜ57

«سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ رَبَّنَا وَبِحَمْدِكَ، اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي».

«ጌታችን አላህ ሆይ! ከምስጋና ጋር ጥራት ይገባህ። አላህ ሆይ! ማረኝ።»58

«سُبُّوُحٌ، قُدُّوسٌ، رَبُّ المَلَائِكَةِ وَالرُّوحِ».

«ከጉድለት ሁሉ የጠራና የተቀደሰ የመልአክቶችና የሩሕ (የጅብሪል) ጌታ።»59.

«اللَّهُمَّ لَكَ رَكَعْتُ، وَبِكَ آمَنْتُ، وَلَكَ أَسْلَمْتُ، خَشَعَ لَكَ سَمْعِي، وَبَصَرِي، وَمُخِّي، وَعَظْمِي، وَعَصَبِي، [وَمَا استَقَلَّتْ بِهِ قَدَمِي]».

«አላህ ሆይ! ላንተ ሩኩዕ አድርጌያለሁ፤ ባንተም አምኛለሁ፤ ላንተም እጅ ሰጥቻለሁ፤ መስማቴ፣ ማየቴ፣ መቅኔዬ፣ አጥንቴ፣ ጅማቴ፣ [እግሬ የተሸከመውም ሁሉ] ላንተ ተናነሱ።" ማለት ነው።60»

«سُبْحَانَ ذِي الجَبَرُوتِ، وَالمَلَكُوتِ، وَالكِبْرِيَاءِ، وَالعَظَمَةِ».

«ትርጉሙም: የኃያልነት፣ የንግሥና፣ የኩራትና የታላቅነት ባለቤት ጥራት ይገባው።»61

18. ከሩኩዕ ቀና ሲባል የሚደረግ ዱዓእ

«سَمِعَ اللَّهُ لِمَنْ حَمِدَهُ».

«አላህ ያመሰገነውን ሰሚ ነው።»62

«رَبَّنَا وَلَكَ الحَمْدُ، حَمْدًا كَثيرًا طَيِّبًا مُبارَكًا فِيهِ».

«ጌታችን ሆይ! ምስጋና ላንተ የተገባ ነው። ላንተ የበዛ፣ ምርጥ የሆነ፣ የተባረከ ምስጋና የተገባህ ነህ።»63

«مِلْءَ السَّمَوَاتِ وَمِلْءَ الأَرْضِ، وَمَا بَيْنَهُمَا، وَمِلْءَ مَا شِئْتَ مِنْ شَيءٍ بَعْدُ. أَهلَ الثَّناءِ وَالمَجْدِ، أَحَقُّ مَا قَالَ العَبْدُ، وَكُلُّنَا لَكَ عَبْدٌ، اللَّهُمَّ لَا مَانِعَ لِمَا أَعْطَيْتَ، وَلَا مُعْطِيَ لِمَا مَنَعْتَ، وَلَا يَنْفَعُ ذَا الجَدِّ مِنْكَ الجَدُّ».

«ሰማያትን የሞላ ምድርንም የሞላና በመካከላቸው ያለውንም የሞላ ከዚህም ሁሉ ኃላ ከነገሮች ሁሉ አንተ የፈለግከውን የሞላ ምስጋና የተገባህ ነህ። የውደሳና የልቅና ባለቤት ነህ። ሁላችንም ላንተ ባሪያዎች ከመሆናችንም ጋር ባሪያው ከተናገራቸው እጅግ ተገቢው ንግግር "አላህ ሆይ! አንተ ለሰጠኸው ከልካይ የለውም። አንተ ለከለከልከውም ሰጪ የለውም። የልቅና ባለቤትም ልቅናው አይጠቅመውም፤ ልቅናም ካንተው ነው።»64

19. የሱጁድ ዱዓእ

«سُبْحَانَ رَبِّيَ الأَعْلَى».

«ልዑሉ ጌታዬ ጥራት ተገባው።»

ሦስት ጊዜ65

«سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ رَبَّنَا وَبِحَمْدِكَ، اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي».

«ጌታችን አላህ ሆይ! ከምስጋና ጋር ጥራት ይገባህ። አላህ ሆይ! ማረኝ።»66

«سُبُّوحٌ، قُدُّوسٌ، رَبُّ المَلَائِكَةِ وَالرُّوحِ».

«ከጉድለት ሁሉ የጠራና የተቀደሰ የመልአክቶችና የሩሕ (የጅብሪል) ጌታ።»67

«اللَّهُمَّ لَكَ سَجَدْتُ وَبِكَ آمَنْتُ، وَلَكَ أَسْلَمْتُ، سَجَدَ وَجْهِيَ لِلَّذِي خَلَقَهُ، وَصَوَّرَهُ، وَشَقَّ سَمْعَهُ وَبَصَرَهُ، تَبَارَكَ اللَّهُ أَحْسَنُ الخَالِقِينَ».

«አላህ ሆይ! ላንተ ሱጁድ አድርጌያለሁ፤ ባንተም አምኛለሁ፤ ላንተም እጅ ሰጥቻለሁ፤ ፊቴ ለዚያ ለፈጠረው፣ ቅርጹንም ላሳመረው፣ መስሚያውንና ማያውን ለከፈተለት ጌታ ሱጁድ አደረገ። ከፈጣሪዎች ሁሉ በላጭ የሆነው አላህ ላቀ።»68

«سُبْحَانَ ذِي الجَبَرُوتِ، وَالمَلَكُوتِ، وَالكِبْرِيَاءِ، وَالعَظَمَةِ».

«የኃያልነት፣ የንግስና፣ የኩራትና እና የታላቅነት ባለቤት ለሆነው ጌታ ጥራት ይገባው።»69

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي ذَنْبِي كُلَّهُ: دِقَّهُ وَجِلَّهُ، وَأَوَّلَهُ وَآخِرَهُ، وَعَلَانِيَّتَهُ وَسِرَّهُ».

«አላህ ሆይ! ወንጀሌን ሁሉንም፤ ትንሹንም ትልቁንም፣ የመጀመሪያውንም የመጨረሻውንም፣ ግልፁንም ድብቁንም ማረኝ፡፡»70

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِرِضَاكَ مِنْ سَخَطِكَ، وَبِمُعَافَاتِكَ مِنْ عُقوبَتِكَ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْكَ، لَا أُحْصِي ثَنَاءً عَلَيْكَ، أَنْتَ كَمَا أَثْنَيْتَ عَلَى نَفْسِكَ».

«አላህ ሆይ! እኔ በውዴታህ ከቁጣህ ፣ በይቅር ባይነትህ ከቅጣትህ እጠበቃለሁ። ባንተው ካንተ እጠበቃለሁ። ባንተ ላይ አወድሼ አልዘልቅም ፣ አንተ ራስህን እንዳወደስከው ነህ።»71

20. በሁለቱ ሱጁዶች መካከል በምንቀመጥ ወቅት የሚደረግ ዱዓእ፤

«رَبِّ اغْفِرْ لِي، رَبِّ اغْفِرْ لِي».

«ጌታዬ ማረኝ፤ ጌታዬ ማረኝ፡፡»72

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي، وَارْحَمْنِي، وَاهْدِنِي، وَاجْبُرْنِي، وَعَافِنِي، وَارْزُقْنِي، وَارْفَعْنِي».

«አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ምራኝ፣ ጠግነኝ፣ ጤናን ስጠኝ፣ ሲሳይን ለግሰኝ፣ ከፍም አድርገኝ።»73

21. የቲላዋህ ሱጁድ ዱዓእ

«سَجَدَ وَجْهِيَ لِلَّذِي خَلَقَهُ، وَشَقَّ سَمْعَهُ وَبَصَرَهُ بِحَوْلِهِ وَقُوَّتِهِ، فَتَبارَكَ اللَّهُ أَحْسَنُ الخَالِقِينَ»

«ፊቴ ለዚያ ለፈጠረው፣ በችሎታውና በኃይሉ መስሚያውንና መመልከቻውን ለከፈተው ሱጁድ አደረገ፡፡ ከፈጣሪዎችም ሁሉ በላጭ የሆነው አላህ ላቀ (ተባረከ)፡፡»

[አል-ሙእሚኑን: 14]74

«اللَّهُمَّ اكْتُبْ لِي بِهَا عِنْدَكَ أَجْرًا، وَضَعْ عَنِّي بِهَا وِزْرًا، وَاجْعَلْهَا لِي عِنْدَكَ ذُخْرًا، وَتَقَبَّلْهَا مِنِّي كَمَا تَقَبَّلْتَهَا مِنْ عَبْدِكَ دَاوُدَ».

«አላህ ሆይ! በርሷ በአንተ ዘንድ ምንዳን ጻፍልኝ፤ በርሷም ከእኔ ላይ ኃጢአትን አንሳልኝ፤ በአንተ ዘንድም ለኔ ስንቅ አድርግልኝ፤ ከባሪያህ ዳውድ እንደተቀበልካት ሁሉ ከእኔም ተቀበላት፡፡»75

22. ተሸሁድ

«التَّحِيَّاتُ لِلَّهِ، وَالصَّلَواتُ، وَالطَّيِّبَاتُ، السَّلَامُ عَلَيْكَ أَيُّهَا النَّبِيُّ وَرَحْمَةُ اللَّهِ وَبَرَكَاتُهُ، السَّلَامُ عَلَيْنَا وَعَلَى عِبَادِ اللَّهِ الصَّالِحِينَ، أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَأَشْهَدُ أَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُهُ وَرَسولُهُ».

«ክብርና ልዕልና እንዲሁም ሶላቶችና መልካም ነገሮች ሁሉ ለአላህ ናቸው። አንቱ ነቢዩ ሆይ! የአላህ ሰላም፣ እዝነቱና በረከቶች በእርሶ ላይ ይስፈን፤ ሰላም በእኛና በአላህ ደጋግ ባሮችም ላይ ይስፈን፤ ከአላህ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፤ ሙሐመድም የአላህ ባርያና መልዕክተኛው መሆናቸውንም እመሰክራለሁ።»76

23. ከተሸሁድ በኋላ በነቢዩ ﷺ ላይ ሶላት ማውረድ

«اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ، وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا صَلَّيتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ، وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، اللَّهُمَّ بَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبْرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».

«አላህ ሆይ! በኢብራሂምና በቤተሰቦቻቸው ላይ ውዳሴህን እንዳወረድክ ሁሉ በሙሐመድና በቤተሰቦቻቸው ላይም ውዳሴህን አውርድ፤ አንተ ምስጉንና የላቅክ አምላክ ነህና። አላህ ሆይ! በኢብራሂምና በቤተሰቦቻቸው ላይ በረከትህን እንዳሰፈንክ ሁሉ በሙሐመድና በቤተሰቦቻቸው ላይም በረከትህን አዉርድ፤ አንተ ምስጉንና የላቅክ አምላክ ነህና።»77

«اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى أَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى أَزْواجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ، كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبْرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».

«አላህ ሆይ! በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ውዳሴህን እንዳወረድክ ሁሉ በሙሐመድ፣ በሚስቶቻቸውና በዝርዮቻቸው ላይም ውዳሴህን አውርድ፤ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ በረከትህን እንዳሰፈንክ ሁሉ በሙሐመድ፣ በሚስቶቻቸውና በዝርዮቻቸው ላይም በረከትህን አውርድ። አንተ ምስጉንና የላቅክ ነህና።»78

24. ከመጨረሻው ተሸሁድ በኋላ ከማሰላመት በፊት ዱዓእ ማድረግ።

«اللَّهُــمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنْ عَذَابِ القَبْرِ، وَمِنْ عَذَابِ جَهَنَّمَ، وَمِنْ فِتْنَةِ المَحْيَا وَالمَمَاتِ، وَمِنْ شَرِّ فِتْنَةِ المَسِيحِ الدَّجَّالِ».

«አላህ ሆይ! ከመቃብር ቅጣት፣ ከጀሀነም ቅጣት፣ ከሕይወትና ከሞት ፈተና፣ እንዲሁም ከሐሰተኛው መሲሕ (ደጃል) ፈተና ክፋት በአንተ እጠበቃለሁ»79

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنْ عَذَابِ القَبْرِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ فِتْنَةِ المَسِيحِ الدَّجَّالِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ فِتْنَةِ المَحْيَا وَالمَمَاتِ، اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ المَأْثَمِ وَالمَغْرَمِ».

«አላህ ሆይ! ከቀብር ቅጣት በአንተ እጠበቃለሁ፣ ከመሲሕ አድ-ደጃል ፈተናም በአንተ እጠበቃለሁ፣ ከሕይወትና ከሞት ፈተናም በአንተ እጠበቃለሁ፣ አላህ ሆይ! ከወንጀልና ከዕዳ በአንተ እጠበቃለሁ»80

«اللَّهُمَّ إِنِّي ظَلَمْتُ نَفْسِي ظُلْمًا كَثِيرًا، وَلَا يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إِلَّا أَنْتَ، فَاغْفِرْ لِي مَغْفِرَةً مِنْ عِنْدِكَ وَارْحَمْنِي، إِنَّكَ أَنْتَ الغَفُورُ الرَّحِيمُ».

«አላህ ሆይ! እኔ ነፍሴን ብዙ በደል በድያታለሁ። ወንጀሎችን ካንተ በቀር ማንም አይምርምና ካንተ ዘንድ በሆነች ምህረት ለኔ ማረኝም እዘንልኝም። እነሆ አንተ እጅግ መሀሪውና አዛኙ ነህና።"81

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي مَا قَدَّمْتُ، وَمَا أَخَّرْتُ، وَمَا أَسْرَرْتُ، وَمَا أَعْلَنْتُ، وَمَا أَسْرَفْتُ، وَمَا أَنْتَ أَعْلَمُ بِهِ مِنِّي، أَنْتَ المُقَدِّمُ، وَأَنْتَ المُؤَخِّرُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ».

«አላህ ሆይ! ያስቀደምኩትን፣ ያዘገየሁትን፣ የደበቅኩትን፣ ግልፅ ያወጣሁትን፣ ወሰን ያለፍኩትንና አንተ ከኔ የበለጠ የምታውቀውንም ወንጀል ማረኝ፤ አንተ አስቀዳሚ ነህ፣ አንተም የሚያዘገይ ነህ፤ ከአንተ ውጭ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም።"82»

«اللَّهُمَّ أَعِنِّي عَلَى ذِكْرِكَ، وَشُكْرِكَ، وَحُسْنِ عِبادَتِكَ».

"አላህ ሆይ! አንተን በማውሳት፣ በማመስገንና አምልኮህን በማሳመር ላይ አግዘኝ።"83

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ البُخْلِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنَ الجُبْنِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ أَنْ أُرَدَّ إِلَى أَرْذَلِ العُمُرِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ فِتْنَةِ الدُّنْيَا وَعَذَابِ القَبْرِ».

«አላህ ሆይ! ከስስት በአንተ እጠበቃለሁ፣ ከፈሪነትም በአንተ እጠበቃለሁ፣ ወደ እጅግ ደካማ የእርጅና ዕድሜ ከመመለስም በአንተ እጠበቃለሁ፣ ከዱንያ ፈተና እና ከቀብር ቅጣትም በአንተ እጠበቃለሁ»84.

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ الجَنَّةَ وَأَعُوذُ بِكَ مِنَ النَّارِ».

«አላህ ሆይ! እኔ ጀነትን እጠይቅሀለሁ። ከእሳትም ባንተ እጠበቃለሁ።"85»

«اللَّهُمَّ بِعِلْمِكَ الغَيْبَ وَقُدْرَتِكَ عَلَى الخَلقِ أَحْيِنِي مَا عَلِمْتَ الحَيَاةَ خَيْرًا لِي، وَتَوَفَّنِي إِذَا عَلِمْتَ الْوَفَاةَ خَيْرًا لِي، اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ خَشْيَتَكَ فِي الغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ، وَأَسْأَلُكَ كَلِمَةَ الحَقِّ فِي الرِّضَا وَالغَضَبِ، وَأَسْأَلُكَ القَصْدَ فِي الغِنَى وَالفَقْرِ، وَأَسْأَلُكَ نَعِيمًا لَا يَنْفَدُ، وَأَسْأَلُكَ قُرَّةَ عَيْنٍ لَا تَنْقَطِعُ، وَأَسْأَلُكَ الرِّضَا بَعْدَ القَضَاءِ، وَأَسْأَلُكَ بَرْدَ العَيْشِ بَعْدَ المَوْتِ، وَأَسْأَلُكَ لَذَّةَ النَّظَرِ إِلَى وَجْهِكَ، وَالشَّوْقَ إِلَى لِقَائِكَ فِي غَيرِ ضَرَّاءَ مُضِرَّةٍ، وَلَا فِتْنَةٍ مُضِلَّةٍ، اللَّهُمَّ زَيِّنَا بِزِينَةِ الإِيمَانِ، وَاجْعَلْنَا هُدَاةً مُهْتَدِينَ».

«አላህ ሆይ! በሩቅ እውቀትክ፣ በፍጡራን ላይ ባለህ ችሎታክ ህይወት ለኔ መልካም መሆኗን ካወቅክ እንድታኖረኝ፤ ሞት ለኔ መልካም መሆኗን ካወቅክ እንድትገድለኝ እማፀንሀለሁ። አላህ ሆይ! እኔ በሩቅም በቅርብም ፍራቻህን እጠይቅሀለሁ፤ በውዴታም ሆነ በቁጣ ወቅት እውነት መናገርን እጠይቅሀለሁ፤ በሀብትም ሆነ በድህነት ውስጥ ሚዛናዊነትን እጠይቅሀለሁ፤ የማይጠፋ ፀጋን እጠይቅሀለሁ፤ የማይቋረጥ የአይን ማረፊያን እጠይቅሀለሁ፤ ከውሳኔ በኋላ መውደድን እጠይቅሀለሁ፤ ከሞት በኋላ ያማረ ኑሮን እጠይቅሀለሁ፤ ወደ ፊትህ የመመልከትን እርካታ፣ ያለምንም ጎጂ ጉዳትና አጥማሚ ፈተና አንተን የመገናኘትን ናፍቆት እንድትሰጠኝ እጠይቅሀለሁ፤ አላህ ሆይ በኢማን ጌጥ አስውበን፤ የተመሩ ቅኖችም አድርገን።»86

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ يَا أَللَّهُ بِأَنَّكَ الوَاحِدُ الأَحَدُ الصَّمَدُ الَّذِي لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ، وَلَمْ يَكُنْ لَهُ كُفُوًا أَحَدٌ، أَنْ تَغْفِرَ لِي ذُنُوبِي إِنَّكَ أَنْتَ الغَفُورُ الرَّحِّيمُ».

«አላህ ሆይ! አንተ አንድ፣ ብቸኛ፣ መጠጊያ፣ ያ የማይወልድ፣ የማይወለድ፣ ለርሱ አንድም ቢጤ የሌለው ነህ። አላህ ሆይ! ለኔ ወንጀሎቼን እንድትምር እጠይቅሀለሁ። እነሆ አንተ እጅግ መሀሪና እጅግ አዛኝ ነህና።"87

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ بِأَنَّ لَكَ الحَمْدَ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ وَحْدَكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، المَنَّانُ، يَا بَدِيعَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ يَا ذَا الجَلَالِ وَالإِكْرَامِ، يَا حَيُّ يَا قَيُّومُ إِنِّي أَسْأَلُكَ الجَنَّةَ وَأَعُوذُ بِكَ مِنَ النَّارِ».

«አላህ ሆይ! እኔ እጠይቅሀለሁ ላንተ ምስጋና የተገባህ ነህ፤ ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም። ብቸኛ ነህ ላንተም አጋር የለህም። ለጋሽ የሆንክ፤ የሰማያትና የምድር ፈጣሪ የሆነከው ሆይ፤ የግርማና ክብር ባለቤት የሆንከው ሆይ! ፤ ህያውና በራሱ የቆመ የሆንከው ሆይ! እኔ ጀነትን እጠይቅሀለሁ። ከእሳትም ባንተ እጠበቃለሁ።»88

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ بِأَنَّي أَشْهَدُ أَنَّكَ أَنْتَ اللَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ الأَحَدُ الصَّمَدُ الَّذِي لَمْ يَلِدْ وَلَمْ يُولَدْ وَلَمْ يَكُنْ لَهُ كُفُوًا أَحَدٌ».

«አላህ ሆይ! እነሆ አንተ አላህ መሆንክንና ከአንተም በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለ፣ ብቸኛ፣ መጠጊያ፣ ያ ያልወለደና ያልተወለደ ፣ ለርሱ አንድም ቢጤ የሌለው መሆንክን እመሰክራለሁ።»89

25. ሶላትን ከማጠናቀቅ በኋላ የሚባሉ አዝካሮች

«أَسْتَغْفِرُ اللَّهَ

«አላህ ሆይ ምህረትህን እጠይቅሃለሁ)

(ሦስት ጊዜ)

اللَّهُمَّ أَنْتَ السَّلَامُ، وَمِنْكَ السَّلَامُ، تَبَارَكْتَ يَا ذَا الجَلَالِ وَالإِكْرَامِ».

«አላህ ሆይ! አንተ "አስ-ሰላም" ነህ። ሰላምም ከአንተው ነው የሚመጣው። የግርማና የልቅና ባለቤት የሆንከው ጌታዬ ሆይ ክብርህ ይስፋ።»90

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።»

[ሦስት ጊዜ]

اللَّهُمَّ لَا مَانِعَ لِمَا أَعْطَيْتَ، وَلَا مُعْطِيَ لِمَا مَنَعْتَ، وَلَا يَنْفَعُ ذَا الجَدِّ مِنْكَ الجَدُّ».

«አላህ ሆይ! አንተ ለሰጠኸው ከልካይ የለውም። አንተ ለከለከልከውም ሰጪ የለውም። የልቅና ባለቤትም ልቅናው ካንተ አይጠቅመውም።»91.

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ، وَلَهُ الحَمدُ، وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ، لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَلَا نَعْبُدُ إِلَّا إِيَّاهُ لَهُ النِّعْمَةُ وَلَهُ الفَضْلُ وَلَهُ الثَّنَاءُ الحَسَنُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ وَلَوْ كَرِهَ الكَافِرُونَ».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ አጋር የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው። በአላህ ካልሆነ በስተቀር ብልሃትም ሆነ ሃይል የለም። ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም። ከርሱም ሌላ አንገዛም። ፀጋው የርሱ ብቻ ነው። ችሮታውም የርሱ ብቻ ነው። መልካም ውዳሴም የሚገባው ለእርሱ ብቻ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም። ከሓዲዎች ቢጠሉም (እኛ) ሃይማኖታችንን ለርሱ ያጠራን ነን።»92.

«سُبْحَانَ اللَّهِ، وَالحَمْدُ لِلَّهِ، وَاللَّهُ أَكْبَرُ

«ለአላህ ጥራት ይገባው፤ ምስጋናም ለአላህ ነው፤ አላህም ታላቅ ነው።»

(ሰላሳ ሦስት ጊዜ)

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ አጋር የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።»93.

﴿قُلۡ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ1 ٱللَّهُ ٱلصَّمَدُ2 لَمۡ يَلِدۡ وَلَمۡ يُولَدۡ3 وَلَمۡ يَكُن لَّهُۥ كُفُوًا أَحَدُۢ4﴾

{ቁል ሁወሏሁ አሐድ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -እርሱ አላህ አንድ ብቻ ነው:: (1)

{አላሁስ-ሶመድ} አላህ የሁሉ ነገር መጠጊያ ነው:: (2)

{ለምየሊድ ወለምዩለድ} አልወለደም፤ አልተወለደምም::(3)

{ወለም የኩን ለሁ ኩፉወን አሐድ} ለእርሱም አንድም ብጤ የለዉም።(4) [አል-ኢኽላስ: 1-4]

﴿قُلۡ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلۡفَلَقِ1 مِن شَرِّ مَا خَلَقَ2 وَمِن شَرِّ غَاسِقٍ إِذَا وَقَبَ3 وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِي ٱلۡعُقَدِ4 وَمِن شَرِّ حَاسِدٍ إِذَا حَسَدَ5﴾

{ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -በተፈልቃቂው ጎህ (በአል-ፈለቅ) ጌታ እጠበቃለሁ (1)

{ሚን ሸርሪ ማ ኸለቅ} ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት::(2)

{ወሚን ሸርሪ ጋሲቂን ኢዛ ወቀብ} ከሌሊትም ክፋት በጨለመ ጊዜ (3)

{ወሚን ሸርሪን-ነፋሣቲ ፊል ዑቀድ} በቋጠሮዎች ላይ ተፊዎች ከሆኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት (4)

{ወሚን ሸርሪ ሓሲዲን ኢዛ ሐሰድ} ከምቀኛም ክፋት፤ በተመቀኘ ጊዜ (በአሏህ) -እጠበቃለሁ- በል:: (5)}

[አል'ፈለቅ፡ 1-5]

﴿قُلۡ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلنَّاسِ1 مَلِكِ ٱلنَّاسِ2 إِلَٰهِ ٱلنَّاسِ3 مِن شَرِّ ٱلۡوَسۡوَاسِ ٱلۡخَنَّاسِ4 ٱلَّذِي يُوَسۡوِسُ فِي صُدُورِ ٱلنَّاسِ5 مِنَ ٱلۡجِنَّةِ وَٱلنَّاسِ6﴾

{ቁል አዑዙ ቢረብቢ-ን-ናስ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -የሰዎች ሁሉ ፈጣሪ በሆነው ጌታ እጠበቃለሁ (1)

{መሊኪን-ናስ} የሰዎች ሁሉ ንጉስ በሆነው ጌታ (2)

{ኢላሂን-ናስ} የሰዎች ሁሉ አምላክ በሆነው ጌታ (3)

{ሚን ሸርሪል ወስዋሲ-ልኸናስ} ከዚያ ብቅ እልም ባይ ከሆነው ጎትጓች ክፋት (4)

{አልለዚ ዩወስዊሱ ፊ ሱዱሪን-ናስ} ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከሆነው (5)

{ሚነል-ጂንነቲ ወንናስ} ከጂንም ይሁን ከሰው ሰይጣን ክፋት (እጠበቃለሁ)።(6)} [አን-ናስ: 1-6]

ከእያንዳንዱ ሶላት በኋላ94

﴿ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ٱلۡحَيُّ ٱلۡقَيُّومُۚ لَا تَأۡخُذُهُۥ سِنَةٞ وَلَا نَوۡمٞۚ لَّهُۥ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِۗ مَن ذَا ٱلَّذِي يَشۡفَعُ عِندَهُۥٓ إِلَّا بِإِذۡنِهِۦۚ يَعۡلَمُ مَا بَيۡنَ أَيۡدِيهِمۡ وَمَا خَلۡفَهُمۡۖ وَلَا يُحِيطُونَ بِشَيۡءٖ مِّنۡ عِلۡمِهِۦٓ إِلَّا بِمَا شَآءَۚ وَسِعَ كُرۡسِيُّهُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَۖ وَلَا يَـُٔودُهُۥ حِفۡظُهُمَاۚ وَهُوَ ٱلۡعَلِيُّ ٱلۡعَظِيمُ255﴾

"አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ እውነተኛ አምላክ የለም:: አላህ ምንግዜም ሕያው፤ በራሱ የተብቃቃ ነው:: ማንገላጀትም ሆነ እንቅልፍ አትይዘዉም:: በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው:: ያ እርሱ ዘንድ በፍቃዱ ቢሆን እንጂ የሚያማልድ ማን ነው? (ከፍጡራን) ሁሉ በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ጠንቅቆ ያውቃል:: በሻው ነገር እንጂ ከእውቀቱ (ፍጡራን) በምንም ነገር አያካብቡም:: መንበሩ የሰማያትንና የምድርን ስፋት ይበልጣል:: ጥበቃቸዉም አያቅተዉም:: እርሱ የሁሉ የበላይና ታላቅ ነው::"

[አል-በቀራህ: 255] ከእያንዳንዱ ሶላት በኋላ95

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ يُحْيِي وَيُمِيتُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ»

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። ሕያው ያደርጋል፤ ይገድላልም። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።»

ከመግሪብ እና ከሱብሒ ሶላት በኋላ አስር ጊዜ96

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ عِلْمًا نافِعًا، وَرِزْقًا طَيِّبًا، وَعَمَلًا مُتَقَبَّلًا».

«አላህ ሆይ! ጠቃሚ ዕውቀትን፣ መልካም ሲሳይን፣ ተቀባይነት ያለው ሥራን እጠይቅሀለሁ።»

بَعْدَ السَّلامِ مِنْ صَلَاةِ الفَجْرِ.

«ከፈጅር ሶላት ሰላምታ በኋላ97»

26 - የኢስቲኻራ ሶላት ዱዓእ

ጃቢር ቢን ዐብደሏህ ረዲየሏሁ ዐንሁማ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፡ «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የቁርአን ምዕራፍ እንደሚያስተምሩን ለሁሉም ጉዳያችን ኢስቲኻራን (አላህን የማማረጥን ዱዓ) እንዴት እንደምናደርግም ያስተምሩን ነበር። እንዲህም ይሉን ነበር:"

«إِذَا هَمَّ أَحَدُكُمْ بِالأَمْرِ فَلْيَرْكَعْ رَكْعَتَيْنِ مِنْ غَيْرِ الفَرِيضَةِ، ثُمَّ لْيَقُلْ:

«አንዳችሁ አንድን ጉዳይ ባሰበ ጊዜ ከግዴታ ውጭ ሁለት ረከዓ ይስገድ፤ ከዚያም እንዲህ ይበል፦

اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْتَخِيرُكَ بِعِلْمِكَ، وَأَسْتَقْدِرُكَ بِقُدْرَتِكَ، وَأَسْأَلُكَ مِنْ فَضْلِكَ العَظِيمِ؛ فَإِنَّكَ تَقْدِرُ وَلَا أَقْدِرُ، وَتَعْلَمُ وَلَا أَعْلَمُ، وَأَنْتَ عَلَّامُ الغُيُوبِ، اللَّهُمَّ إِنْ كُنْتَ تَعْلَمُ أَنَّ هَذَا الأمْرَ - وَيُسَمِّي حَاجَتَهُ - خَيْرٌ لِي فِي دِينِي وَمَعَاشِي وَعَاقِبَةِ أَمْرِي – أَوْ قَالَ: عَاجِلِهِ وَآجِلِهِ - فَاقْدُرْهُ لِي وَيَسِّرْهُ لِي ثمَّ بَارِكْ لِي فِيهِ، وَإِنْ كُنْتَ تَعْلَمُ أَنَّ هَذَا الْأَمْرَ شَرٌّ لِي فِي دِينِي وَمَعَاشِي وَعَاقِبَةِ أَمْرِي – أَوْ قَالَ: عَاجِلِهِ وَآجِلِهِ – فَاصْرِفْهُ عَنِّي وَاصْرِفْنِي عَنْهُ وَاقْدُرْ لِيَ الْخَيْرَ حَيْثُ كَانَ، ثُمَّ أَرْضِنِي بِهِ».

«አላህ ሆይ! በእውቀትህ የተሻለውን እንድትገጥመኝ እፈልጋለሁ፤ በችሎታህ ቻይ እንድታደርገኝ እጠይቅሃለሁ፤ ከታላቁ ችሮታህም እጠይቅሃለሁ፤ አንተ ቻይ ነህና እኔ ደግሞ አልችልም፤ አንተ ታውቃለህ እኔ ደግሞ አላውቅም፤ አንተ የሩቅን አዋቂ ነህ። አላህ ሆይ! ይህ ጉዳይ – (ጉዳዩንም ይጠቅሳል) – ለሃይማኖቴ፣ ለኑሮዬና ለጉዳዬ መዳረሻ – ወይም እርሳቸው ያሉት፡ ለቅርቡም ለወደፊቱም ጉዳዬ – ለኔ የሚበጅ መሆኑን የምታውቅ ከሆነ ለኔ ወስንልኝ፣ አግራልኝም፣ ከዚያም በርሱ ውስጥ ባርክልኝ። ይህ ጉዳይ ለሃይማኖቴ፣ ለኑሮዬና ለጉዳዬ መዳረሻ – ወይም እርሳቸው ያሉት፡ ለቅርቡም ለወደፊቱም ጉዳዬ – ለኔ መጥፎ መሆኑን የምታውቅ ከሆነ ደግሞ ከኔ ዞር አድርግልኝም፣ እኔንም ከርሱ ዞር አድርገኝ። መልካሙንም ካለበት ቦታ ወስንልኝ፣ ከዚያም እንድወደው አድርገኝ።»98

ፈጣሪውን (በጎ ምርጫን) የጠየቀ (ኢስቲኻራ ያደረገ)፣ አማኝ ፍጡራንን ያማከረ እና በጉዳዩ ላይ ያረጋገጠ (የተረጋጋ) ሰው አይጸጸትም። ጥራት የተገባውና የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦

﴿...وَشَاوِرۡهُمۡ فِي ٱلۡأَمۡرِۖ فَإِذَا عَزَمۡتَ فَتَوَكَّلۡ عَلَى ٱللَّهِ...﴾

{...በሁሉም ነገር ላይ አማክራቸው:: ከዚያ ቁርጥ ሀሳብ ባደረገክ ጊዜ በአላህ ላይ ብቻ ተመካ...}99

27. የንጋትና ምሽት ዚክሮች

«ምስጋና ብቸኛ ለሆነው ለአላህ የተገባ ነው፤ የአላህ ሰላትና ሰላም ከርሳቸው በኋላ ነቢይ በሌለው ላይ ይስፈን።»100.

«አዑዙ ቢላሂ ሚነሽ-ሸይጧኒር-ረጂም» ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ

﴿ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ٱلۡحَيُّ ٱلۡقَيُّومُۚ لَا تَأۡخُذُهُۥ سِنَةٞ وَلَا نَوۡمٞۚ لَّهُۥ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِۗ مَن ذَا ٱلَّذِي يَشۡفَعُ عِندَهُۥٓ إِلَّا بِإِذۡنِهِۦۚ يَعۡلَمُ مَا بَيۡنَ أَيۡدِيهِمۡ وَمَا خَلۡفَهُمۡۖ وَلَا يُحِيطُونَ بِشَيۡءٖ مِّنۡ عِلۡمِهِۦٓ إِلَّا بِمَا شَآءَۚ وَسِعَ كُرۡسِيُّهُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَۖ وَلَا يَـُٔودُهُۥ حِفۡظُهُمَاۚ وَهُوَ ٱلۡعَلِيُّ ٱلۡعَظِيمُ255﴾

«አላሁ ላ ኢላሀ ኢላ ሁወል ሐዩል ቀዩም፤ ላ ተእኹዙሁ ሲነቱን ወላ ነውም፤ ለሁ ማ ፊስ-ሰማዋቲ ወማ ፊል አርድ፤ መን ዘልለዚ የሽፈዑ ዒንደሁ ኢላ ቢኢዝኒህ፤ የዕለሙ ማ በይነ አይዲሂም ወማ ኸልፈሁም፤ ወላ ዩሒጡነ ቢሸይኢን ሚን ዒልሚሂ ኢላ ቢማ ሻእ፤ ወሲዐ ኩርሲዩሁስ-ሰማዋቲ ወል አርድ፤ ወላ የኡዱሁ ሒፍዙሁማ፤ ወሁወል ዐሊዩል ዐዚም፡፡»

አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ እውነተኛ አምላክ የለም:: ሕያው፤ በራሱ የተብቃቃ ነው:: ማንገላጀትም ሆነ እንቅልፍ አትይዘዉም:: በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው:: ያ እርሱ ዘንድ በፍቃዱ ቢሆን እንጂ የሚያማልድ ማን ነው? (ከፍጡራን) ሁሉ በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ጠንቅቆ ያውቃል:: በሻው ነገር እንጂ ከእውቀቱ (ፍጡራን) በምንም ነገር አያካብቡም:: መንበሩ የሰማያትንና የምድርን ስፋት ይበልጣል:: ጥበቃቸዉም አያቅተዉም:: እርሱ የሁሉ የበላይና ታላቅ ነው:: [አል-በቀራህ: 255]101

﴿قُلۡ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ1 ٱللَّهُ ٱلصَّمَدُ2 لَمۡ يَلِدۡ وَلَمۡ يُولَدۡ3 وَلَمۡ يَكُن لَّهُۥ كُفُوًا أَحَدُۢ4﴾

{ቁል ሁወሏሁ አሐድ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -እርሱ አላህ አንድ ብቻ ነው:: (1)

{አላሁስ-ሶመድ} አላህ የሁሉ ነገር መጠጊያ ነው:: (2)

{ለምየሊድ ወለምዩለድ} አልወለደም፤ አልተወለደምም::(3)

{ወለምየኩን ለሁ ኩፉወን አሐድ} ለእርሱም አንድም ብጤ የለዉም። (4)} [አል-ኢኽላስ: 1-4]

﴿قُلۡ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلۡفَلَقِ1 مِن شَرِّ مَا خَلَقَ2 وَمِن شَرِّ غَاسِقٍ إِذَا وَقَبَ3 وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِي ٱلۡعُقَدِ4 وَمِن شَرِّ حَاسِدٍ إِذَا حَسَدَ5﴾

{ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -በተፈልቃቂው ጎህ (በአል-ፈለቅ) ጌታ እጠበቃለሁ፤- (1)

{ሚን ሸርሪ ማ ኸለቅ} ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት:: (2)

{ወሚን ሸርሪ ጋሲቂን ኢዛ ወቀብ} ከሌሊትም ክፋት በጨለመ ጊዜ፤ (3)

{ወሚን ሸርሪን-ነፋሣቲ ፊልዑቀድ} በቋጠሮዎች ላይ ተፊዎች ከሆኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፤ (4)

{ወሚን ሸርሪ ሓሲዲን ኢዛ ሐሰድ} ከምቀኛም ክፋት፤ በተመቀኘ ጊዜ (በአሏህ) -እጠበቃለሁ- በል:: (5)}

[አል-ፈለቅ፡ 1-5]

﴿قُلۡ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلنَّاسِ1 مَلِكِ ٱلنَّاسِ2 إِلَٰهِ ٱلنَّاسِ3 مِن شَرِّ ٱلۡوَسۡوَاسِ ٱلۡخَنَّاسِ4 ٱلَّذِي يُوَسۡوِسُ فِي صُدُورِ ٱلنَّاسِ5 مِنَ ٱلۡجِنَّةِ وَٱلنَّاسِ6﴾

{ቁል አዑዙ ቢረቢን-ናስ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -የሰዎች ሁሉ ፈጣሪ በሆነው ጌታ እጠበቃለሁ፤ (1)

{መሊኪን-ናስ} የሰዎች ሁሉ ንጉስ በሆነው ጌታ፤ (2)

{ኢላሂን-ናስ} የሰዎች ሁሉ አምላክ በሆነው ጌታ፤ (3)

{ሚን ሸርሪል-ወስዋሲል-ኸናስ} ከዚያ ብቅ እልም ባይ ከሆነው ጎትጓች ክፋት፤ (4)

{አልለዚ ዩወስዊሱ ፊ ሱዱሪን-ናስ} ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከሆነው፤ (5)

{ሚነል ጂን-ነቲ ወንናስ} ከጂንም ይሁን ከሰው ሰይጣን ክፋት (እጠበቃለሁ)። (6)}

[አን-ናስ: 1-6] (ሦስት ጊዜ)102

«أَصْبَحْنَا وَأَصْبَحَ المُلْكُ لِلَّهِ، وَالحَمْدُ لِلَّهِ، لَا إِلَهَ إلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ، رَبِّ أَسْأَلُكَ خَيْرَ مَا فِي هَذَا اليَوْمِ وَخَيرَ مَا بَعْدَهُ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا فِي هَذَا اليَوْمِ وَشَرِّ مَا بَعْدَهُ، رَبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنَ الكَسَلِ وَسُوءِ الكِبَرِ، رَبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنْ عَذَابٍ فِي النَّارِ وَعَذَابٍ فِي القَبْرِ».

«እኛም አነጋን፤ ንግስናም የአላህ ሆኖ አነጋ። ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው። ከአላህ ውጭ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም ፤ ብቸኛና አጋር የሌለው ነው ፤ ንግስና እና ምስጋና ለርሱ ነው ፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። ጌታዬ ሆይ! በዚህ ቀን ውስጥም ከዚህ ቀንም በኋላ ያለን መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። በዚህ ቀን ውስጥም ከዚህ ቀንም በኋላ ካለው ክፉ ነገርም በአንተ እጠበቃለሁ። ጌታዬ ሆይ! ከስንፍና እና ከመጥፎ እርጅና በአንተ እጠበቃለሁ። ጌታዬ ሆይ! በእሳት ውስጥ ካለ ቅጣት እና በቀብር ውስጥ ካለ ቅጣት በአንተ እጠበቃለሁ።»103

ሲመሽም እንዲህ ይሉ ነበር፡

«أَمْسَيْنَا وَأَمْسَى الْمُلْكُ لِلَّهِ، وَالحَمْدُ لِلَّهِ، لَا إِلَهَ إلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ، رَبِّ أَسْأَلُكَ خَيْرَ مَا فِي هَذِهِ اللَّيْلَةِ، وَخَيْرَ مَا بَعْدَهَا، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا فِي هَذِهِ اللَّيْلَةِ، وَشَرِّ مَا بَعْدَهَا، رَبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنَ الكَسَلِ وَسُوءِ الكِبَرِ، رَبِّ أَعُوذُ بِكَ مِنْ عَذَابٍ فِي النَّارِ وَعَذَابٍ فِي القَبْرِ».

«እኛም ንግስናም የአላህ ሆነን አመሸን። ምስጋና ለአላህ የተገባ ነው። ከአላህ ውጭ (በእውነት) የሚመለክ አምላክ የለም ፤ ብቸኛና አጋር የሌለው ነው ፤ ንግስና እና ምስጋና ለርሱ ነው ፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። ጌታዬ ሆይ! በዚህች ሌሊት ውስጥም ከዚህች ሌሊትም በኋላ ያለን መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። በዚህች ሌሊት ውስጥም ከዚህች ሌሊትም በኋላ ካለው ክፉ ነገርም በአንተ እጠበቃለሁ። ጌታዬ ሆይ! ከስንፍና እና ከመጥፎ እርጅና በአንተ እጠበቃለሁ። ጌታዬ ሆይ! ከእሳት ቅጣት እና ከቀብር ቅጣት በአንተ እጠበቃለሁ።)104

«اللَّهُمَّ بِكَ أَصْبَحْنَا، وَبِكَ أَمْسَيْنَا، وَبِكَ نَحْيَا، وَبِكَ نَمُوتُ وَإِلَيْكَ النُّشُورُ».

«ጌታዬ ሆይ! በአንተ (ጥበቃ) አነጋን ፤ በአንተ (ጥበቃም) አመሸን ፤ በአንተ (ስም) ህያው እንሆናለን ፤ በአንተ (ስምም) እንሞታለን ፤ መቀስቀስም ወደ አንተ ብቻ ነው።»105.

ሲመሽም እንዲህ ይሉ ነበር፦

«اللَّهُمَّ بِكَ أَمْسَيْنَا، وَبِكَ أَصْبَحْنَا، وَبِكَ نَحْيَا، وَبِكَ نَمُوتُ، وَإِلَيْكَ الْمَصِيرُ».

«ጌታዬ ሆይ! በአንተ (ጥበቃ) አመሸን ፤ በአንተ (ጥበቃም) አነጋን ፤ በአንተ (ስም) ህያው እንሆናለን ፤ በአንተ (ስምም) እንሞታለን ፤ መመለሻም ወደ አንተ ብቻ ነው።)106.

«اللَّهُمَّ أَنْتَ رَبِّي لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، خَلَقْتَنِي وَأَنَا عَبْدُكَ، وَأَنَا عَلَى عَهْدِكَ وَوَعْدِكَ مَا اسْتَطَعْتُ، أَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا صَنَعْتُ، أَبُوءُ لَكَ بِنِعْمَتِكَ عَلَيَّ، وَأَبُوءُ بِذَنْبِي فَاغْفِرْ لِي فَإِنَّهُ لَا يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إِلَّا أَنْتَ».

«አላህ ሆይ! አንተ ጌታዬ ነህ፤ ከአንተ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም፤ ፈጥረኸኛል እኔም ባሪያህ ነኝ፣ እኔም በቻልኩት መጠን በቃል ኪዳንህና በተስፋ ቃልህ ላይ እገኛለሁ፤ ከሰራሁት ክፋት በአንተ እጠበቃለሁ፣ በእኔ ላይ የዋልከውን ፀጋ አረጋግጣለሁ107፣ ኃጢአቴንም አምናለሁና ማረኝ! እነሆ ከአንተ በቀር ኃጢአቶችን የሚምር ማንም የለምና።»108

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَصْبَحْتُ أُشْهِدُكَ، وَأُشْهِدُ حَمَلَةَ عَرْشِكَ، وَمَلَائِكَتِكَ، وَجَمِيعَ خَلْقِكَ، أَنَّكَ أَنْتَ اللَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ وَحْدَكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، وَأَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُكَ وَرَسُولُكَ».

«አላህ ሆይ! አንተ አምላክ መሆንህን ከአንተ በስተቀርም በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩንና ተጋሪ የሌለህ ብቸኛ መሆንህን እና ሙሐመድም ባርያህና መልዕክተኛህ መሆናቸውን አንተን፣ የዐርሽህን ተሸካሚዎች፣ መላእክትህን፣ እንዲሁም ሁሉንም ፍጡራኖችህን ምስክር አድርጌ አነጋሁ።»

አራት ጊዜ109

ሲመሽ እንዲህ ይሉ ነበር፡

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَمْسَيْتُ أُشْهِدُكَ، وَأُشْهِدُ حَمَلَةَ عَرْشِكَ، وَمَلَائِكَتِكَ، وَجَمِيعَ خَلْقِكَ، أَنَّكَ أَنْتَ اللَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ وَحْدَكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، وَأَنَّ مُحَمَّدًا عَبْدُكَ وَرَسُولُكَ»

«አላህ ሆይ! አንተ አምላክ መሆንህን ከአንተ በስተቀርም በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩንና አጋር የሌለህ ብቸኛ መሆንህን፣ ሙሐመድም ባርያህና መልዕክተኛህ መሆናቸውን አንተን፣ የዐርሽህን ተሸካሚዎች፣ መላእክትህን እንዲሁም ሁሉንም ፍጡራኖችህን ምስክር አድርጌ አመሸሁ።»

አራት ጊዜ110

«اللَّهُمَّ مَا أَصْبَحَ بِي مِنْ نِعْمَةٍ أَوْ بِأَحَدٍ مِنْ خَلْقِكَ فَمِنْكَ وَحْدَكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، فَلَكَ الحَمْدُ وَلَكَ الشُّكْرُ».

«አላህ ሆይ! በኔ ወይም ከፍጡራንህ በአንዱ ላይ ያነጋው ፀጋ ከአንተው ብቻና ብቻ ነው። ለአንተ አጋር የለህም ምስጋናና ውዳሴም ይገባሀል።»111

ሲመሽም እንዲህ ይሉ ነበር፡

«اللَّهُمَّ مَا أَمْسَى بِي مِنْ نِعْمَةٍ أَوْ بِأَحَدٍ مِنْ خَلْقِكَ فَمِنْكَ وَحْدَكَ لَا شَرِيكَ لَكَ، فَلَكَ الحَمْدُ وَلَكَ الشُّكْرُ».

«አላህ ሆይ! በኔ ወይም ከፍጡራንህ በአንዱ ላይ ያመሸው ፀጋ ከአንተው ብቻና ብቻ ነው። ለአንተ አጋር የለህም ምስጋናና ውዳሴም ይገባሀል።"112

«اللَّهُمَّ عَافِنِي فِي بَدَنِي، اللَّهُمَّ عَافِنِي فِي سَمْعِي، اللَّهُمَّ عَافِنِي فِي بَصَرِي، لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ الكُفْرِ، وَالفَقْرِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ عَذَابِ القَبْرِ، لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ».

«አላህ ሆይ በአካሌ ጤናን ስጠኝ፣ አላህ ሆይ በመስሚያዬ ጤናን ስጠኝ፣ አላህ ሆይ በዕይታዬ ጤናን ስጠኝ፣ ከአንተ ውጭ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፣ አላህ ሆይ ከክህደት እና ከድህነት በአንተ እጠበቃለሁ፣ ከቀብር ቅጣትም በአንተ እጠበቃለሁ፣ ከአንተ ውጭ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም»

ሦስት ጊዜ113

«حَسْبِيَ اللَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ عَلَيهِ تَوَكَّلتُ وَهُوَ رَبُّ العَرْشِ العَظِيمِ».

«አላህ በቂዬ ነው። ከእርሱ ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። በእርሱ ላይ ተጠጋሁ እርሱም የታላቁ ዐርሽ ጌታ ነው።»

ሰባት ጊዜ114

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ العَفْوَ وَالعَافِيَةَ فِي الدُّنْيَا وَالآخِرَةِ، اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ العَفْوَ وَالعَافِيَةَ: فِي دِينِي وَدُنْيَايَ وَأَهْلِي، وَمَالِي، اللَّهُمَّ اسْتُرْ عَوْرَاتِي، وَآمِنْ رَوْعَاتِي، اللَّهُمَّ احْفَظْنِي مِنْ بَينِ يَدَيَّ، وَمِنْ خَلْفِي، وَعَنْ يَمِينِي، وَعَنْ شِمَالِي، وَمِنْ فَوْقِي، وَأَعُوذُ بِعَظَمَتِكَ أَنْ أُغْتَالَ مِنْ تَحْتِي».

«አላህ ሆይ! በዚህችም ሆነ በቀጣዩ ዓለም ይቅርታህንና ጤናን እጠይቅሃለሁ። አላህ ሆይ! በሃይማኖቴ፣ በቅርቢቱ ዓለም ህይወቴ፣ በቤተሰቦቼና በንብረቴም ይቅርታህንና ጤናን እጠይቅሃለሁ። አላህ ሆይ! ነውሬን ሸፍንልኝ፤ ለስጋቴም (ለፍርሃቴም) ደህንነትን ለግሰኝ። አላህ ሆይ! ከፊት ለፊቴ፣ ከኋላዬም፣ ከበስተቀኜም፣ ከበስተግራዬም እንዲሁም ከበላዬም ጠብቀኝ፤ ከበታቼም እንዳልጠቃ በልቅናህ እጠበቃለሁ።)115

«اللَّهُمَّ عَالِمَ الغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ فَاطِرَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ، رَبَّ كُلِّ شَيْءٍ وَمَلِيكَهُ، أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، أَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ نَفْسِي، وَمِنْ شَرِّ الشَّيْطانِ وَشَرَكِهِ، وَأَنْ أَقْتَرِفَ عَلَى نَفْسِي سُوءًا، أَوْ أَجُرَّهُ إِلَى مُسْلِمٍ».

«የሩቁን እና የቅርቡን አዋቂ፣ የሰማያትና የምድሩ ፈጣሪ የሆንከው ፤ የሁሉም ነገር ጌታ እና ባለቤት የሆንከው አላህ ሆይ! ከአንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እመሰክራለሁ። ከነፍሴ ተንኮል እንዲሁም ከሸይጧን ተንኮል እና የሽርክ ጥሪው (ውትወታው)፣ በነፍሴ ላይ መጥፎ ከመስራትም ይሁን ሙስሊም በሆነ ሰው ላይ መጥፎን ከመፈፀም በአንተ እጠበቃለሁ።)116

«بِسْمِ اللَّهِ الَّذِي لَا يَضُرُّ مَعَ اسْمِهِ شَيْءٌ فِي الأَرْضِ وَلَا فِي السَّمَاءِ وَهُوَ السَّمِيعُ العَلِيمُ».

«በዚያ ከስሙ ጋር በምድርም ይሁን በሰማይ ምንም ነገር የማይጎዳ በሆነው እንዲሁም ሰሚና ዐዋቂ በሆነው አላህ ስም።)

ሦስት ጊዜ117

«رَضِيتُ بِاللَّهِ رَبًَّا، وَبِالإِسْلَامِ دِينًا، وَبِمُحَمَّدٍ ﷺ نَبِيًّا».

«በአላህ ጌትነት፣ በእስልምና ሃይማኖትነትና በሙሐመድ ነቢይነት ወደድኩ።"

ሦስት ጊዜ118

«يَا حَيُّ يَا قَيُّومُ بِرَحْمَتِكَ أَسْتَغيثُ أَصْلِحْ لِي شَأْنِيَ كُلَّهُ وَلَا تَكِلْنِي إِلَى نَفْسِي طَرْفَةَ عَيْنٍ».

«ሕያውና ሁሉን አስተናባሪ የሆንክ ጌታ ሆይ! በእዝነትህ እርዳታን እጠይቃለሁ ፤ ጉዳዬንም ሁሉ አስተካክልልኝ ፤ የአይን መርገብገብን ያህል እንኳ ቢሆን ለራሴ አትተወኝ።"119

«أَصْبَحْنَا وَأَصْبَحَ المُلْكُ لِلَّهِ رَبِّ العَالَمِينَ، اللَّهُـمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ خَيْرَ هَذَا اليَوْمِ: فَتْحَهُ، وَنَصْرَهُ، وَنورَهُ، وَبَرَكَتَهُ، وَهُدَاهُ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا فِيهِ وَشَرِّ مَا بَعْدَهُ».

«እኛም አነጋን፤ ንግስናም የዓለማት ጌታ ለሆነው አላህ ሆኖ አነጋ። አላህ ሆይ! እኔ የዚህን ቀን መልካም ነገር፡ ስኬቱን፣ ድሉን፣ ብርሃኑን፣ በረከቱንና ቅናቻውን እጠይቅሃለሁ። በውስጡ ካለው ክፉ ነገርና ከርሱ በኋላ ካለውም ክፉ ነገር በአንተ እጠበቃለሁ።»120.

ሲመሽም እንዲህ ይሉ ነበር፡

«أَمْسَيْنَا وَأَمْسَى المُلْكُ لِلَّهِ رَبِّ العَالَمِينَ، اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ خَيْرَ هَذِهِ اللَّيْلَةِ: فَتْحَهَا، وَنَصْرَهَا، وَنُورَهَا، وَبَرَكَتَهَا، وَهُدَاهَا، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ مَا فِيهَا، وَشَرِّ مَا بَعْدَهَا».

«ለማምሸት በቅተናል፤ በዚህ ሰዓት ልዕልና የዓለማት ጌታ ለሆነው አላህ ነው። አላህ ሆይ! እኔ የዚህችን ሌሊት መልካም ነገር፣ ስኬቷን፣ ድሏንና ብርሃኗን እንዲሁም ረድኤቷንና በዚህች ሌሊት ትክክለኛ ፍኖትን መጨበጥን እጠይቅሀለሁ። ከርሷና ከርሷ ቀጥሎ ከሚመጣው ጊዜ ክፉ ነገር ባንተ እጠበቃለሁ።»121

«أَصْبَحْنا عَلَى فِطْرَةِ الإِسْلَامِ، وَعَلَى كَلِمَةِ الإِخْلاَصِ، وَعَلَى دِينِ نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ، وَعَلَى مِلَّةِ أَبِينَا إِبْرَاهِيمَ، حَنِيفًا مُسْلِمًا وَمَا كَانَ مِنَ المُشرِكِينَ».

«በኢስላም ተፈጥሯችን፣ በመልካም ንግግር (ከሊመተል ኢኽላስ)፣ በነቢያችን በሙሐመድ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሃይማኖት፣ ቀጥ ያለ ሙስሊም በነበረውና ከሙሽሪኮች ባልነበረው በአባታችን በኢብራሂም ጎዳና ላይ እንደጸናን አነጋን።»122.

ሲመሽም እንዲህ ይሉ ነበር፡

«أَمْسَيْنَا عَلَى فِطْرَةِ الإِسْلَامِ، وَعَلَى كَلِمَةِ الإِخْلاَصِ، وَعَلَى دِينِ نَبِيِّنَا مُحَمَّدٍ ﷺ، وَعَلَى مِلَّةِ أَبِينَا إِبْرَاهِيمَ، حَنِيفًا مُسْلِمًا وَمَا كَانَ مِنَ المُشرِكِينَ».

«በኢስላም ተፈጥሯችን፡ በመልካም ንግግር (ከሊመተል ኢኽላስ)በነቢያችን በሙሐመድ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሃይማኖት ቀጥ ያለ ሙስሊም በነበረዉና ከሙሽሪኮች ባልነበረዉ በአባታችን በኢብራሂም ጎዳና ላይ እንደጸናን አመሸን»123.

«سُبْحَانَ اللَّهِ وَبِحَمْدِهِ».

«ለአላህ ጥራትና ምስጋና ተገባው።)

መቶ ጊዜ124

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ، وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።)

አስር ጊዜ125፣ ወይም ድካም ላይ ሲሆኑ አንድ ጊዜ126

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።)

መቶ ጊዜ ሲነጋ127

«سُبْحَانَ اللَّهِ وَبِحَمْدِهِ: عَدَدَ خَلْقِهِ، وَرِضَا نَفْسِهِ، وَزِنَةَ عَرْشِهِ، وَمِدَادَ كَلِمَاتِهِ».

«ለአላህ የፍጡራኑን ቁጥር ያህል፣ የነፍሱን ውዴታ ያህል፣ የዐርሹን ክብደት ያህል እና የንግግሮቹን ያህል ጥራትና ምስጋና ተገባው።)

ሦስት ጊዜ ሲነጋ128

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ عِلْمًا نَافِعًا، وَرِزْقًا طَيِّبًا، وَعَمَلًا مُتَقَبَّلًا».

«አላህ ሆይ! ጠቃሚ ዕውቀትን፣ መልካም ሲሳይን፣ ተቀባይነት ያለው ስራን እጠይቅሀለሁ።"

በነጋ ጊዜ129፡፡

«أَسْتَغْفِرُ اللَّهَ وَأَتُوبُ إِلَيْهِ»

«አላህን ምህረቱን እጠይቀዋለሁ፤ ወደ እርሱም በፀፀት እመለሳለሁ።)

በቀን መቶ ጊዜ130

«أَعُوذُ بِكَلِمَاتِ اللَّهِ التَّامَّاتِ مِنْ شَرِّ مَا خَلَقَ».

«ከፍጡራኑ ክፋት ሙሉ በሆኑ የአላህ ቃላት እጠበቃለሁ።)

ሦስት ጊዜ ምሽት ላይ131

«اللَّهُمَّ صَلِّ وَسَلِّمْ عَلَى نَبَيِّنَا مُحَمَّدٍ».

«አላህ ሆይ! በነቢይህ ሙሐመድ ላይ ሶላትህንና ሰላምህን አስፍን»

ዐሥር ጊዜ132

28. የመኝታ አዝካር (ውዳሴዎች)

(ሁለቱን መዳፎቹን ያገጣጥማል፤ ከዚያም በውስጣቸው እፍ ይልና በነሱ ውስጥ የሚከተለውን ይቀራል፡

﴿قُلۡ هُوَ ٱللَّهُ أَحَدٌ1 ٱللَّهُ ٱلصَّمَدُ2 لَمۡ يَلِدۡ وَلَمۡ يُولَدۡ3 وَلَمۡ يَكُن لَّهُۥ كُفُوًا أَحَدُۢ4﴾

{ቁልሁወሏሁ አሐድ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -እርሱ አላህ አንድ ብቻ ነው:: (1)

{አላሁስ-ሶመድ} አላህ የሁሉ ነገር መጠጊያ ነው:: (2)

{ለምየሊድ ወለምዩለድ} አልወለደም፤ አልተወለደምም::(3)

{ወለምየኩን ለሁ ኩፉወን አሐድ} ለእርሱም አንድም ብጤ የለዉም። (4)} [አል-ኢኽላስ: 1-4]

﴿قُلۡ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلۡفَلَقِ1 مِن شَرِّ مَا خَلَقَ2 وَمِن شَرِّ غَاسِقٍ إِذَا وَقَبَ3 وَمِن شَرِّ ٱلنَّفَّٰثَٰتِ فِي ٱلۡعُقَدِ4 وَمِن شَرِّ حَاسِدٍ إِذَا حَسَدَ5﴾

{ቁል አዑዙ ቢረቢል ፈለቅ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -በተፈልቃቂው ጎህ (በአል-ፈለቅ) ጌታ እጠበቃለሁ፤- (1)

{ሚን ሸርሪ ማ ኸለቅ} ከፈጠረው ፍጡር ሁሉ ክፋት::(2)

{ወሚን ሸርሪ ጋሲቂን ኢዛ ወቀብ} ከሌሊትም ክፋት በጨለመ ጊዜ፤ (3)

{ወሚን ሸርሪን-ነፋሣቲ ፊልዑቀድ} በቋጠሮዎች ላይ ተፊዎች ከሆኑት ደጋሚ ሴቶችም ክፋት፤ (4)

{ወሚንሸርሪ ሐሲዲን ኢዛ ሐሰድ} ከምቀኛም ክፋት፤ በተመቀኘ ጊዜ (በአሏህ) -እጠበቃለሁ- በል:: (5)}

[አል_ፈለቅ፡ 1-5]

﴿قُلۡ أَعُوذُ بِرَبِّ ٱلنَّاسِ1 مَلِكِ ٱلنَّاسِ2 إِلَٰهِ ٱلنَّاسِ3 مِن شَرِّ ٱلۡوَسۡوَاسِ ٱلۡخَنَّاسِ4 ٱلَّذِي يُوَسۡوِسُ فِي صُدُورِ ٱلنَّاسِ5 مِنَ ٱلۡجِنَّةِ وَٱلنَّاسِ6﴾

{ቁል አዑዙ ቢረብቢን-ናስ} {(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ! እንዲህ) በል፡ -የሰዎች ሁሉ ፈጣሪ በሆነው ጌታ እጠበቃለሁ፤ (1)

{መሊኪን-ናስ} የሰዎች ሁሉ ንጉስ በሆነው ጌታ፤ (2)

{ኢላሂን-ናስ} የሰዎች ሁሉ አምላክ በሆነው ጌታ፤ (3)

{ሚን ሸርሪል ወስዋሲል-ኸናስ} ከዚያ ብቅ እልም ባይ ከሆነው ጎትጓች ክፋት፤ (4)

{አልለዚ ዩወስዊሱ ፊ ሱዱሪን-ናስ} ከዚያ በሰዎች ልቦች ውስጥ የሚጎተጉት ከሆነው፤ (5)

{ሚነል ጂንነቲ ወንናስ} ከጂንም ይሁን ከሰው ሰይጣን ክፋት (እጠበቃለሁ)። (6)} [አን-ናስ: 1-6]

ቀጥሎም በሁለት እጆቻቸው ከሰውነታቸው የቻሉትን ያህል ያብሳሉ። በእነርሱም ጭንቅላታቸውን፣ ፊታቸውንና የሰውነታቸውን የፊት ለፊት ክፍል በማበስ ይጀምራሉ። (ይህንንም ሶስት ጊዜ ያደርጋሉ)133

﴿ٱللَّهُ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ ٱلۡحَيُّ ٱلۡقَيُّومُۚ لَا تَأۡخُذُهُۥ سِنَةٞ وَلَا نَوۡمٞۚ لَّهُۥ مَا فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَمَا فِي ٱلۡأَرۡضِۗ مَن ذَا ٱلَّذِي يَشۡفَعُ عِندَهُۥٓ إِلَّا بِإِذۡنِهِۦۚ يَعۡلَمُ مَا بَيۡنَ أَيۡدِيهِمۡ وَمَا خَلۡفَهُمۡۖ وَلَا يُحِيطُونَ بِشَيۡءٖ مِّنۡ عِلۡمِهِۦٓ إِلَّا بِمَا شَآءَۚ وَسِعَ كُرۡسِيُّهُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضَۖ وَلَا يَـُٔودُهُۥ حِفۡظُهُمَاۚ وَهُوَ ٱلۡعَلِيُّ ٱلۡعَظِيمُ255﴾

"አላህ ከእርሱ በስተቀር ሌላ እውነተኛ አምላክ የለም:: አላህ ምንግዜም ሕያው፤ በራሱ የተብቃቃ ነው:: ማንገላጀትም ሆነ እንቅልፍ አትይዘዉም:: በሰማያት ውስጥና በምድር ውስጥ ያለው ሁሉ የእርሱ ብቻ ነው:: ያ እርሱ ዘንድ በፍቃዱ ቢሆን እንጂ የሚያማልድ ማን ነው? (ከፍጡራን) ሁሉ በፊታቸው ያለውንና ከኋላቸው ያለውን ሁሉ ጠንቅቆ ያውቃል:: በሻው ነገር እንጂ ከእውቀቱ (ፍጡራን) በምንም ነገር አያካብቡም:: መንበሩ የሰማያትንና የምድርን ስፋት ይበልጣል:: ጥበቃቸዉም አያቅተዉም:: እርሱ የሁሉ የበላይና ታላቅ ነው።"

[አል-በቀራህ: 255]134

﴿ءَامَنَ ٱلرَّسُولُ بِمَآ أُنزِلَ إِلَيۡهِ مِن رَّبِّهِۦ وَٱلۡمُؤۡمِنُونَۚ كُلٌّ ءَامَنَ بِٱللَّهِ وَمَلَٰٓئِكَتِهِۦ وَكُتُبِهِۦ وَرُسُلِهِۦ لَا نُفَرِّقُ بَيۡنَ أَحَدٖ مِّن رُّسُلِهِۦۚ وَقَالُواْ سَمِعۡنَا وَأَطَعۡنَاۖ غُفۡرَانَكَ رَبَّنَا وَإِلَيۡكَ ٱلۡمَصِيرُ285 لَا يُكَلِّفُ ٱللَّهُ نَفۡسًا إِلَّا وُسۡعَهَاۚ لَهَا مَا كَسَبَتۡ وَعَلَيۡهَا مَا ٱكۡتَسَبَتۡۗ رَبَّنَا لَا تُؤَاخِذۡنَآ إِن نَّسِينَآ أَوۡ أَخۡطَأۡنَاۚ رَبَّنَا وَلَا تَحۡمِلۡ عَلَيۡنَآ إِصۡرٗا كَمَا حَمَلۡتَهُۥ عَلَى ٱلَّذِينَ مِن قَبۡلِنَاۚ رَبَّنَا وَلَا تُحَمِّلۡنَا مَا لَا طَاقَةَ لَنَا بِهِۦۖ وَٱعۡفُ عَنَّا وَٱغۡفِرۡ لَنَا وَٱرۡحَمۡنَآۚ أَنتَ مَوۡلَىٰنَا فَٱنصُرۡنَا عَلَى ٱلۡقَوۡمِ ٱلۡكَٰفِرِينَ286﴾

«አመነ ረሱሉ ቢማ ኡንዚለ ኢለይሂ ሚን ረቢሂ ወልሙእሚኑን፤ ኩሉን አመነ ቢላሂ ወመላኢከቲሂ ወኩቱቢሂ ወሩሱሊህ፤ ላ ኑፈሪቁ በይነ አሐዲን ሚን ሩሱሊህ፤ ወቃሉ ሰሚዕና ወአጠዕና ጉፍራነከ ረበና ወኢለይከል መሲር።» "መልዕክተኛው (ሙሐመድ) ከጌታው ወደ እርሱ በተወረደለት (ቁርኣን) አምኗል:: አማኞችም እንደዚሁ አመኑ:: ሁሉም በአላህ፣ በመላዕክቱ፣ በመጽሐፉና በመልዕክተኞቹ «ከእነርሱ በአንዱም መካከል አንለይም (አንክድም)» የሚሉ ሲሆኑ አመኑ:: «የአላህን ትዕዛዛትንም ሰማን ታዘዝንም። ጌታችን ሆይ! ምህረትህን እንሻለን :: የሁሉም መመለሻ ወደ አንተው ብቻ ነው። አሉም::" (285)

«ላ ዩከሊፉላሁ ነፍሰን ኢላ ዉስዐሃ፤ ለሃ ማከሰበት ወዐለይሃ መክተሰበት፤ ረበና ላ ቱአኺዝና ኢንነሲና አው አኽጠእና፤ ረበና ወላ ተሕሚል ዐለይና ኢስረን ከማ ሐመልተሁ ዐለለዚነ ሚን ቀብሊና፤ ረበና ወላ ቱሐሚልና ማ ላ ጧቀተ ለና ቢህ፤ ወዕፉ ዐና፣ ወግፊር ለና፣ ወርሃምና፤ አንተ መውላና ፈንሱርና ዐለል ቀውሚል ካፊሪን።» አላህ የትኛዋንም ነፍስ ከችሎታዋ በላይ አያስገድዳትም:: ነፍስ ሁሉ ለሰራችው መልካም ስራ ሁሉ ተገቢው ምንዳ አላት:: በእርሷም ላይ ባፈራችው (ኃጢአት) ተገቢው ቅጣት አለባት:: (ሙስሊሞች) «ጌታችን ሆይ! ብንረሳ ወይም ብንሳሳት (አትቅጣን):: ጌታችን ሆይ! ከባድ ሸክምን ከእኛ በፊት በነበሩት ህዝቦች ላይ እንደጫንከው ሁሉ በእኛ ላይ አትጫንብን:: ጌታችን ሆይ! ለእኛ ችሎታ የሌለንን ነገር አታሸክመን:: ለእኛም ይቅርታ አድርግልን:: ለእኛም ምህረትን አድርግልን:: እዘንልንም:: ረዳታችን አንተ ብቻ ነህና:: በከሓዲ ሕዝቦች ላይም ድልን አጎናጽፈን። (286)»

[አል-በቀራህ: 285-286]135

«بِاسْمِكَ رَبِّي وَضَعْتُ جَنْبِي، وَبِكَ أَرْفَعُهُ، فَإِنْ أَمْسَكْتَ نَفْسِي فَارْحَمْهَا، وَإِنْ أَرْسَلْتَهَا فَاحْفَظْهَا، بِمَا تَحْفَظُ بِهِ عِبَادَكَ الصَّالِحِينَ».

«ጌታዬ ሆይ! በስምህ136 ጎኔን አሳረፍኩ፤ ባንተውም አነሳዋለሁ። ነፍሴን ከያዝካት እዘንላት፤ ከለቀቅካትም መልካሞቹን ባሮችህን በምትጠብቅበት ጠብቃት።»137"

«اللَّهُمَّ إِنَّكَ خَلَقْتَ نَفْسِي وَأَنْتَ تَوَفَّاهَا، لَكَ مَمَاتُهَا وَمَحْياهَا، إِنْ أَحْيَيْتَهَا فَاحْفَظْهَا، وَإِنْ أَمَتَّهَا فَاغْفِرْ لَهَا، اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ العَافِيَةَ».

«አላህ ሆይ! አንተ ነፍሴን ፈጠርካት፤ አንተው ትገድላታለህ። ሞቷም ህይወቷም ለአንተ ነው። ካኖርካት ጠብቃት፤ ከገደልካትም ማራት። አላህ ሆይ! እኔ ጤናን እጠይቅሀለሁ።)138

«اللَّهُمَّ قِنِي عَذَابَكَ يَوْمَ تَبْعَثُ عِبَادَكَ».

«አላህ ሆይ! ባሮችህን በምትቀሰቅስበት ቀን ከቅጣትህ ጠብቀኝ139።"140

«بِاسْمِكَ اللَّهُمَّ أَمُوتُ وَأَحْيَا».

«አላህ ሆይ! የምኖረውም የምሞተውም በስምህ ነው።"141

«سُبْحَانَ اللَّهِ

«አላህ ጥራት ተገባው

(ثَلَاثًا وَثَلاثِينَ)،

(ሰላሳ ሶስት ጊዜ።)

وَالحَمْدُ لِلَّهِ

ምስጋናም ሁሉ ለአላህ ይሁን

(ثَلَاثًا وَثَلاثِينَ)،

(ሰላሳ ሦስት ጊዜ።)

وَاللَّهُ أَكْبَرُ

አላህ ታላቅ ነው

(أَرْبَعًا وَثَلَاثِينَ)».

(ሠላሳ አራት)» ጊዜ142

«اللَّهُمَّ رَبَّ السَّمَوَاتِ السَّبْعِ وَرَبَّ الأَرْضِ، وَرَبَّ العَرْشِ العَظِيمِ، رَبَّنَا وَرَبَّ كُلِّ شَيْءٍ، فَالِقَ الحَبِّ وَالنَّوَى، وَمُنْزِلَ التَّوْرَاةِ وَالإِنْجِيلِ، وَالفُرْقَانِ، أَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ كُلِّ شَيْءٍ أَنْتَ آخِذٌ بِنَاصِيَتِهِ، اللَّهُمَّ أَنْتَ الأَوَّلُ فَلَيْسَ قَبْلَكَ شَيْءٌ، وَأَنْتَ الآخِرُ فَلَيسَ بَعْدَكَ شَيْءٌ، وَأَنْتَ الظَّاهِرُ فَلَيْسَ فَوْقَكَ شَيْءٌ، وَأَنْتَ البَاطِنُ فَلَيْسَ دُونَكَ شَيْءٌ، اقْضِ عَنَّا الدَّيْنَ وَأَغْنِنَا مِنَ الفَقْرِ».

«የሰባቱ ሰማያት ጌታ፣ የምድር ጌታ፣ የታላቁ ዐርሽ ጌታ፣ ጌታችን ፣ የሁሉም ነገር ጌታ የሆንከው፣ ቅንጣትንና የቴምር ፍሬን ፈልቃቂ፣ ተውራትን ኢንጂልንና ፉርቃንን ያወረደክ የሆንከው አላህ ሆይ! ከሁሉም አንተ አናቱን የምትይዝ ከሆንከው ነገር ክፋት በአንተ እጠበቃለሁ፤ አላህ ሆይ! አንተ የመጀመሪያ ነህ ከአንተ በፊት አንዳችም የለም፤ አንተ የመጨረሻ ነህ ከአንተ በኋላ አንዳችም የለም፤ አንተ የበላይ ነህ ከአንተ በላይ አንዳችም የለም፤ አንተ (በእውቀትህ) ቅርብ ነህ እንዳንተ ቅርብ አንዳችም የለም እዳችንን ክፈልልን ከድህነትም አብቃቃን።»143

«الحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَطْعَمَنَا وَسَقَانَا، وَكَفَانَا، وَآوَانَا، فَكَمْ مِمَّنْ لَا كَافِيَ لَهُ وَلَا مُؤْوِيَ».

«ለመገበን፣ ላጠጣን፣ ላብቃቃንና መጠለያ ለሰጠን አላህ ምስጋና ይገባው። አብቃቂና መጠለያ ሰጪ የሌላቸው ስንትና ስንት አሉ።»144

«اللَّهُمَّ عَالِمَ الغَيْبِ وَالشَّهَادَةِ فَاطِرَ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ، رَبَّ كُلِّ شَيْءٍ وَمَلِيكَهُ، أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، أَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّ نَفْسِي، وَمِنْ شَرِّ الشَّيْطانِ وَشِرْكِهِ، وَأَنْ أَقْتَرِفَ عَلَى نَفْسِي سُوءًا، أَوْ أَجُرَّهُ إِلَى مُسْلِمٍ».

«የሩቁን እና የቅርቡን አዋቂ፣ የሰማያትና የምድሩ ፈጣሪ የሆንከው፤ የሁሉም ነገር ጌታ እና ባለቤት የሆንከው አላህ ሆይ! ከአንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እመሰክራለሁ። ከነፍሴ ተንኮል እንዲሁም ከሸይጧን ተንኮል እና የሽርክ ጥሪው (ውትወታው)፣ በነፍሴ ላይ መጥፎ ከመስራትም ይሁን ሙስሊም በሆነ ሰው ላይ መጥፎን ከመፈፀም በአንተ እጠበቃለሁ።)145

«يَقْرَأُ ﴿الــم﴾ تَنْزِيلَ السَّجْدَةِ، وَتَبَارَكَ الَّذي بِيَدِهِ المُلْكُ».

«አሊፍ ላም ሚም﴾ ተንዚል አስ-ሰጅዳህን} እና {ተባረከል-ለዚ ቢየዲሂልሙልኩ} ን ይቀራል»146

«اللَّهُمَّ أَسْلَمْتُ نَفْسِي إِلَيْكَ، وَفَوَّضْتُ أَمْرِي إِلَيْكَ، وَوَجَّهْتُ وَجْهِي إِلَيْكَ، وَأَلْجَأْتُ ظَهْرِي إِلَيْكَ، رَغْبَةً وَرَهْبَةً إِلَيْكَ، لَا مَلْجَأَ وَلَا مَنْجَا مِنْكَ إِلَّا إِلَيْكَ، آمَنْتُ بِكِتَابِكَ الَّذِي أَنْزَلْتَ، وَبِنَبِيِّكَ الَّذِي أَرْسَلْتَ».

«አላህ ሆይ!147 ነፍሴን ላንተ እጅ ሰጥቻለሁ፤ ጉዳዬንም ላንተ አሳልፌ ሰጥቻለሁ፤ ፊቴንም ወዳንተ አዙሬያለሁ፤ ጀርባዬንም ወዳንተ አስጠግቻለሁ፤ እዝነትህን በመከጀልና ቅጣትህን በመፍራት፤ ከአንተ መሸሸጊያም ሆነ ማምለጫ ወዳንተው እንጂ የለም፤ ባወረድከው መጽሐፍህ አምኛለሁ፤ በላከውም ነቢይህ አምኛለሁ።" ማለት ነው።148

29 - በሌሊት በተገላበጡ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ፤

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ الوَاحِدُ القَهّارُ، رَبُّ السَّمَوَاتِ وَالأَرْضِ وَمَا بَيْنَهُمَا العَزيزُ الغَفَّارُ».

(አንዱና ሁሉን አሸናፊ፣ የሰማያት፣ የምድርና በመካከላቸውም ላለው ሁሉ ጌታ፣ ኃያልና እጅግ መሓሪ ከሆነው አላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም።)149

30. በእንቅልፍ ውስጥ የደነገጠና በብቸኝነት የተቸገረ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ

«أَعُوذُ بِكَلِمَاتِ اللَّهِ التَّامَّاتِ مِنْ غَضَبِهِ وَعِقَابِهِ، وَشَرِّ عِبَادِهِ، وَمِنْ هَمَزَاتِ الشَّياطِينِ وَأَنْ يَحْضُرُونِ».

«ከአላህ ቁጣና ከቅጣቱ፣ ከባሮቹ ክፋት፣ ከሰይጣናት ጉትጎታ እንዲሁም በአጠገቤ ከመገኘት ሙሉ በሆኑ የአላህ ቃላት እጠበቃለሁ።"150

31. ህልም ያየ ሰው ምን ማድረግ እንዳለበት

(ወደ ግራው ቱፍ ቱፍ ይላል) (ሦስት ጊዜ)151

(ከሰይጣንና ካየው ነገር ክፋት በአላህ ይጠበቃል) (ሶስት ጊዜ)152

"ለማንም አይናገራት"153

(ከነበረበት ጎኑ ይዞራል)154

(ያንን ከፈለገ ተነስቶ ይሰግዳል።)155

32 - የዊትር ቁኑት ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اهْدِنِي فِيمَنْ هَدَيْتَ، وَعَافِنِي فِيمَنْ عَافَيْتَ، وَتَوَلَّنِي فِيمَنْ تَوَلَّيْتَ، وَبَارِكْ لِي فِيمَا أَعْطَيْتَ، وَقِنِي شَرَّ مَا قَضَيْتَ؛ فَإِنَّكَ تَقْضِي وَلَا يُقْضَى عَلَيْكَ، إِنَّهُ لَا يَذِلُّ مَنْ وَالَيْتَ، [وَلاَ يَعِزُّ مَنْ عَادَيْتَ]، تَبارَكْتَ رَبَّنا وَتَعَالَيْتَ».

«አላህ ሆይ! ከመራሃቸው ጋር ምራኝ፣ ጤና ከለገስካቸው ጋር ጤና ለግሰኝ፣ ከተንከባከብካቸው ጋር ተንከባከበኝ፣ በሰጠኸኝ ነገር ላይ በረካ አድርግልኝ፣ ከወሰንከው ነገር ክፋት ጠብቀኝ፤ አንተ ትፈርዳለህ እንጂ በአንተ ላይ አይፈረድብህምና፣ አንተ ወዳጅ ያደረግከው አይዋረድም፣ [አንተ ጠላት ያደረግከውም አይከብርም]፣ ጌታችን ሆይ ተባረክህ፣ ላቅህም።»156

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِرِضَاكَ مِنْ سَخَطِكَ، وَبِمُعَافَاتِكَ مِنْ عُقُوبَتِكَ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْكَ، لَا أُحْصِي ثَنَاءً عَلَيْكَ، أَنْتَ كَمَا أَثْنَيْتَ عَلَى نَفْسِكَ».

«አላህ ሆይ! እኔ በአንተ ውዴታ ከአንተ ቁጣ እጠበቃለሁ፤ በይቅር ባይነትህም ከቅጣትህ እጠበቃለሁ፤ ከአንተም በአንተው እጠበቃለሁ፤ በአንተ ላይ ምስጋናን መቁጠር አልችልም፣ አንተ ራስህን እንዳመሰገንከው ነህ።"157

«اللَّهُمَّ إِيَّاكَ نعْبُدُ، وَلَكَ نُصَلِّي وَنَسْجُدُ، وَإِلَيْكَ نَسْعَى وَنَحْفِدُ، نَرْجُو رَحْمَتَكَ، وَنَخْشَى عَذَابَكَ، إِنَّ عَذَابَكَ بِالكَافِرِينَ مُلْحِقٌ، اللَّهُمَّ إِنَّا نَسْتَعِينُكَ، وَنَسْتَغْفِرُكَ، وَنُثْنِي عَلَيْكَ الخَيْرَ، وَلَا نَكْفُرُكَ، وَنُؤْمِنُ بِكَ، وَنَخْضَعُ لَكَ، وَنَخْلَعُ مَنْ يَكْفرُكَ».

«አላህ ሆይ! አንተን ብቻ እንገዛለን፣ ላንተም እንሰግዳለን፣ ሱጁድም እናደርጋለን፣ ወዳንተም እንተጋለን እንገሰግሳለንም፣ እዝነትህንም ተስፋ እናደርጋለን፣ ቅጣትህንም እንፈራለን፤ ቅጣትህ በከሀዲዎች ላይ በእርግጥ አግኚ ነውና። አላህ ሆይ! እኛ እርዳታህን እንለምንሃለን፣ ምህረትህንም እንጠይቅሃለን፣ በመልካምም እናወድስሃለን፣ አንክድህም፣ ባንተም እናምናለን፣ ላንተም እጅ እንሰጣለን፣ የሚክድህንም እንተዋለን።"158

33. ከዊትር ሶላት ካሰላመቱ በኋላ የሚባል ዚክር

«سُبْحَانَ المَلِكِ القُدُّوسِ».

«ቅዱሱ ንጉሥ ጥራት ተገባው።

ثَلَاثَ مرَّاتٍ

ሦስት ጊዜ

والثَّالِثَةُ يَجْهَرُ بها ويَمُدُّ بِهَا صَوتَهُ يَقُولُ:

ሶስተኛውን ድምፁን ከፍ በማድረግና ጎተት በማድረግ እንዲህ ይላል፡

«رَبِّ المَلَائِكَةِ وَالرُّوحِ».

«የመላእክትና የጂብሪል ጌታ»159."

34 - በጭንቀትና በሀዘን ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ إِنِّي عَبْدُكَ، ابْنُ عَبْدِكَ، ابْنُ أَمَتِكَ، نَاصِيَتِي بِيَدِكَ، مَاضٍ فِيَّ حُكْمُكَ، عَدْلٌ فِيَّ قَضَاؤُكَ، أَسْأَلُكَ بِكُلِّ اسْمٍ هُوَ لَكَ، سَمَّيْتَ بِهِ نَفْسَكَ، أَوْ أَنْزَلْتَهُ فِي كِتَابِكَ، أَوْ عَلَّمْتَهُ أَحَدًا مِنْ خَلْقِكَ، أَوِ اسْتَأْثَرْتَ بِهِ فِي عِلْمِ الغَيْبِ عِنْدَكَ، أَنْ تَجْعَلَ القُرْآنَ رَبِيعَ قَلْبِي، وَنُورَ صَدْرِي، وَجَلَاءَ حُزْنِي، وَذَهَابَ هَمِّي».

«አላህ ሆይ! እኔ ባሪያህ ነኝ። የወንድ ባሪያህና የሴት ባሪያህ ልጅ ነኝ። አናቴ በእጅህ ነው፣ ፍርድህ በኔ ላይ ተፈፃሚ ነው ፣ በኔ ላይ የምትወስነው ውሳኔህ ፍትሃዊ ነው። ነፍስህን በሰየምክበት ስሞችህ፣ ወይም በመፅሀፍህ ውስጥ ባወረድከው ስሞችህ፣ ወይም ከፍጥረታትህ አንዱን ባሳወቅከውም ስሞችህ፣ ወይም አንተ ዘንድ በሩቅ እውቀትህ በተለየህበት ስሞችህ፣ በሁሉም ላንተ ባሉህ ስሞች ቁርአንን የልቤ ፀደይ፣ የልቤ ብርሀን፣ የሀዘኔ ማንሻ፣ የጭንከቴ ማስወገጃ እንድታደርግልኝ እጠይቅሃለሁ።"160

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ الهَمِّ وَالحَزَنِ، وَالعَجْزِ وَالكَسَلِ، وَالبُخْلِ وَالجُبْنِ، وَضَلَعِ الدَّيْنِ وَغَلَبَةِ الرِّجَالِ».

«አላህ ሆይ! እኔ ከጭንቀትና ከሀዘን፣ ከአቅም ማነስና ከስንፍና፣ ከስስትና ከፈሪነት፣ ከከባድ እዳና በሰዎች ከመሸነፍ በአንተ እጠበቃለሁ።"161

35 - በችግር ወቅት የሚደረግ ዱዓእ

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ العَظِيمُ الحَلِيمُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ رَبُّ العَرْشِ العَظِيمِ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ رَبُّ السَّمَوَاتِ وَرَبُّ الأَرْضِ وَرَبُّ العَرْشِ الكَرِيمِ».

«ከታላቁና ቻይ ከሆነው አላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። የታላቁ ዐርሽ ጌታ ከሆነው አላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። የሰማያት ጌታ ፣ የምድር ጌታ ፣ የተከበረው ዐርሽ ጌታ ከሆነው አላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም።"162

«اللَّهُمَّ رَحْمَتَكَ أَرْجُو، فَلَا تَكِلْنِي إِلَى نَفْسِي طَرْفَةَ عَيْنٍ، وَأَصْلِحْ لِي شَأْنِي كُلَّهُ، لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ».

«አላህ ሆይ! እዝነትህን እከጅላለሁና የዓይን መርገብገብን ያህል እንኳ ቢሆን ለራሴ አትተወኝ ፤ ጉዳዬንም ሁሉ አስተካክልልኝ። ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የለም።"163

«لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ سُبْحَانَكَ إِنِّي كُنْتُ مِنَ الظَّالِمِينَ».

«ከአንተ በቀር ሌላ እውነተኛ አምላክ የለም። ጥራት ይገባህ። እኔ በእርግጥ ከበዳዮች ነበርኩ።»164

«اللَّهُ اللَّهُ رَبِّي لَا أُشْرِكُ بِهِ شَيْئًا».

«አላህ አላህ ጌታዬ ነው፤ በእርሱ ምንንም አላጋራም።»165.

36 - ጠላትንና ባለስልጣንን ሲገናኙ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ إِنَّا نَجْعَلُكَ فِي نُحُورِهِم، وَنَعُوذُ بِكَ مِنْ شُرُورِهِمْ».

«አላህ ሆይ! እኛ በአንገቶቻቸው (በፊታቸው) ላይ እናደርግሃለን፤ ከክፋቶቻቸውም ባንተው እንጠበቃለን።"166"

«اللَّهُمَّ أَنْتَ عَضُدِي، وَأَنْتَ نَصِيرِي، بِكَ أَحُولُ وَبِكَ أَصُولُ، وَبِكَ أُقاتِلُ».

«አላህ ሆይ! አንተ ደጋፊዬ ነህ፤ አንተም ረዳቴ ነህ፤ ባንተ እዘዋወራለሁ፤ ባንተም አጠቃለሁ፤ ባንተም እዋጋለሁ።"167

«حَسْبُنا اللَّهُ وَنِعْمَ الوَكِيلُ».

«አላህ መመኪያችንና በቂያችን ነው።»168

37 - የመሪን በደል የፈራ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ

«اللَّهُمَّ ربَّ السَّمَوَاتِ السَّبْعِ، وَرَبَّ العَرْشِ العَظِيمِ، كُنْ لِي جَارًا مِنْ فُلَانِ بْنِ فُلَانٍ، وَأَحْزَابِهِ مِنْ خَلَائِقِكَ، أَنْ يَفْرُطَ عَلَيَّ أَحَدٌ مِنْهُمْ أَوْ يَطْغَى، عَزَّ جَارُكَ، وَجَلَّ ثَنَاؤُكَ، وَلَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ».

«የሰባቱ ሰማያት ጌታ፣ የታላቁ ዐርሽ ጌታ የሆንከው አላህ ሆይ! ከእገሌ የእገሌ ልጅ እና ከፍጡራንህ መካከል ከሆኑት ጭፍሮቹ፤ አንዳቸውም በእኔ ላይ ጥቃት እንዳያደርሱብኝ ወይም ግፍ እንዳይፈጽሙብኝ ከለላ ሁነኝ፤ ጥበቃህ ላቀ፤ ምስጋናህም ከፍ አለ፤ ከአንተ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም።"169

«اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَعَزُّ مِنْ خَلْقِهِ جَمِيعًا، اللَّهُ أَعَزُّ مِمَّا أَخَافُ وَأَحْذَرُ، أَعُوذُ بِاللَّهِ الَّذِي لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ، المُمْسِكِ السَّمَوَاتِ السَّبْعِ أَنْ يَقَعْنَ عَلَى الأَرْضِ إِلَّا بِإِذْنِهِ، مِنْ شَرِّ عَبْدِكَ فُلَانٍ، وَجُنُودِهِ وَأَتْبَاعِهِ وَأَشْيَاعِهِ، مِنَ الجِنِّ وَالإِنْسِ، اللَّهُمَّ كُنْ لِي جَارًا مِنْ شَرِّهِمْ، جَلَّ ثَنَاؤُكَ وَعَزَّ جَارُكَ، وَتَبَارَكَ اسْمُكَ، وَلَا إِلَهَ غَيْرُكَ».

«አላህ ታላቅ ነው፤ አላህ ከፍጡራኑ ሁሉ የላቀ ሀያል ነው፤ አላህ ከምፈራውና ከምጠነቀቀው ነገር ሁሉ የላቀ ሀያል ነው። ከእርሱ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ በሌለው፣ ሰባቱን ሰማያት ያለ እርሱ ፈቃድ በምድር ላይ እንዳይወድቁ አግዶ በያዘው አላህ፤ ከባሪያህ ከእገሌ ክፋት፣ ከጭፍሮቹ፣ ከተከታዮቹና ከደጋፊዎቹ፣ ከጋኔንም ሆነ ከሰው ክፋት እጠበቃለሁ። አላህ ሆይ! ከክፋታቸው ለእኔ ጠባቂ ሁነኝ። ምስጋናህ ላቀ፤ ጥበቃህም ከበረ፤ ስምህም ተብራራ፤ ከአንተ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም።)

ثَلَاثَ مَرَّاتٍ.

ሦስት ጊዜ170

38 - በጠላት ላይ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ مُنْزِلَ الكِتَابِ، سَرِيعَ الحِسَابِ، اهْزِمِ الأَحْزَابَ، اللَّهُمَّ اهزِمْهُمْ وَزَلْزِلْهُمْ».

«መጽሐፍን ያወረድክ፣ ምርመራህ ፈጣን የሆንክ አላህ ሆይ! የተሰባሰቡትን (የጠላት) ኃይሎች ድል ንሳቸው። አላህ ሆይ! ድል ንሳቸው፤ አናውጣቸው።)171

39. ሕዝብን የፈራ ሰው የሚለው

«اللَّهُمَّ اكْفِنِيهِمْ بِمَا شِئْتَ».

«አላህ ሆይ! በሻኸው መንገድ ከእነርሱ ጠብቀኝ።»172

40 - በእምነት ውስጥ ወስዋስ የደረሰበት ሰው የሚያደርገው ዱዓእ

(በአላህ ይጠበቅ)173፡፡ እንዲህም ይላል: ((ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ))"

(ወስዋስ ከገባበት ነገር ይቆጠብ)174

(እንዲህም ይበል:

(آمَنْتُ بِاللَّهِ وَرُسُلِهِ).

"በአላህና በመልክተኞቹ አምናለሁ"175

(የሚከተለውን የአላህ ቃል ይቀራል፦

﴿هُوَ ٱلۡأَوَّلُ وَٱلۡأٓخِرُ وَٱلظَّٰهِرُ وَٱلۡبَاطِنُۖ وَهُوَ بِكُلِّ شَيۡءٍ عَلِيمٌ 3﴾

{እርሱ ( ከበፊቱ ምንም ያልቀደመው) የመጀመሪያ! (ፊት ያለ) (ከኋላው ምንም የሌለ የመጨረሻ) ብቻዉን ቀሪ፤ ከበላዩ ማንም የሌለ (ግልጽና የበላይ) ስውርም (ድብቅ) ነው:: እርሱ (በምድርም ሆነ በሰማይ ያለን) ሁሉ ነገር አዋቂ ነው::} [አል-ሓዲድ: 3 ]176.

41 - የዕዳ መክፈያ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اكْفِنِي بِحَلَالِكَ عَنْ حَرَامِكَ، وَأَغْنِنِي بِفَضْلِكِ عَمَّنْ سِوَاكَ».

«አላህ ሆይ! በሐላልህ ከሐራምህ ጠብቀኝ፤ በችሮታህም ከአንተ ውጪ ካሉ አብቃቃኝ።"177.

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنَ الهَمِّ وَالحَزَنِ، وَالعَجْزِ وَالكَسَلِ، وَالبُخْلِ وَالجُبْنِ، وَضَلَعِ الدَّيْنِ وَغَلَبَةِ الرِّجَالِ».

«አላህ ሆይ! እኔ ከጭንቀትና ከሀዘን፣ ከመልፈስፈስና ከስንፍና፣ ከስስትና ከፈሪነት፣ ከከባድ እዳና በሰዎች ከመሸነፍ ባንተ እጠበቃለሁ።"178

42 - በሶላትና በቂራአት ውስጥ ወስዋስ ሲያጋጥም የሚደረግ ዱዓእ

«أَعُوذُ بِاللَّهِ مِنَ الشَّيطَانِ الرَّجِيمِ،

«ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ፣

وَاتْفُلْ عَلَى يَسَارِكَ (ثَلَاثًا)».

«ወደ ግራህም (ሶስት ጊዜ) ትፋ!»179

43 - ጉዳይ የከበደበት ሰው የሚያደርገው ዱዓእ፤

«اللَّهُمَّ لَا سَهْلَ إِلَّا مَا جَعَلْتَهُ سَهْلاً، وَأَنْتَ تَجْعَلُ الحَزْنَ إِذَا شِئْتَ سَهْلاً».

«አላህ ሆይ! አንተ ቀላል ያደረግከው ቢሆን እንጂ ቀላል የለም። አንተም ስትሻ አስቸጋሪውን ነገር ቀላል ታደርጋለህ።"180"

44. ወንጀል የሠራ ሰው የሚለውና የሚያደርገው

«مَا مِنْ عَبْدٍ يُذنِبُ ذَنْبًا فَيُحْسِنُ الطُّهُورَ، ثُمَّ يَقُومُ فَيُصَلِّي رَكْعَتَيْنِ، ثُمَّ يَسْتَغْفِرُ اللَّهَ إِلَّا غَفَرَ اللَّهُ لَهُ».

«ኃጢዓትን የሠራ፣ ዉዱእን አሳምሮ፣ ከዚያም ተነስቶ ሁለት ረከዓ የሚሰግድ፣ ከዚያም አላህን ምህረት የሚጠይቅ አንድም ባሪያ የለም፤ አላህ ለርሱ የሚምረው ቢሆን እንጂ።»181.

45. ሰይጣንንና ጉትጎታውን ማባረሪያ ዱዓ

(ከርሱ በአላህ መጠበቅ)182.

(አዛን)183.

(አዝካር (ውዳሴዎች) እና ቁርኣንን መቅራት)።

«لَا تَجْعَلُوا بُيُوتَكُمْ مَقَابِرَ، إِنَّ الشَّيْطَانَ يَنْفِرُ مِنَ الْبَيْتِ الَّذِي تُقْرَأُ فِيهِ سُورَةُ الْبَقَرَةِ».

«ቤቶቻችሁን መቃብር አታድርጉ። ሰይጣን የበቀራህ ምእራፍ የሚቀራበት ቤትን ይሸሻል።»184

ሸይጧንን ከሚያባርሩ ነገሮች መካከል የጧትና የማታ፣ የመኝታና ከእንቅልፍ የመነሻ ዚክሮች፣ ቤት በሚገቡበትና በሚወጡበት ወቅት የሚባሉ ዚክሮች፣ መስጂድ በሚገቡበትና በሚወጡበት ወቅት የሚባሉ ዚክሮች፣ እና ሌሎችም የተደነገጉ ውዳሴዎች ይገኙበታል። ለምሳሌ፦ በመኝታ ሰአት አየተል ኩርሲይን መቅራት፣ የሱረቱል በቀራህን የመጨረሻ ሁለት አንቀፆች መቅራት፤ እንዲሁም እንዲህ ያለ ሰው፦

لَا إِلٰهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ الْمُلْكُ وَلَهُ الْحَمْدُ، وَهُوَ عَلَىٰ كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ብቸኛ ነው፣ ተጋሪም የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።)

مِائَةَ مَرَّةٍ، كَانَت لَهُ حِرْزًا مِنَ الشَّيْطَانِ يَومِهِ كُلِّهِ،

መቶ ጊዜ፣ ቀኑን ሙሉ ከሸይጧን መከለያ ትሆንለታለች185 እንዲሁም አዛን ሸይጣንን ያባርራል።

46 - የማይወደው ነገር ሲያጋጥመው ወይም ከአቅሙ በላይ ሲሆንበት የሚያደርገው ዱዓእ

«قَدَرُ اللَّهُ وَمَا شَاءَ فَعَلَ».

«የአላህ ውሳኔ ነው፤ የሻውንም ሠራ።»186

47 - ልጅ ለተወለደለት ሰው የሚባል የእንኳን ደስ አለህ ቃልና ምላሹ

«بَارَكَ اللَّهُ لَكَ فِي المَوْهُوبِ لَكَ، وَشَكَرْتَ الوَاهِبَ، وَبَلَغَ أَشُدَّهُ، وَرُزِقْتَ بِرَّهُ».

«አላህ በተለገሰልህ (ልጅ) በረካን ያድርግልህ፣ ለጋሹንም የምታመሰግን ያድርግህ፣ ለአቅመ-አዳም ይድረስልህ፣ ታዛዥነቱንም ይለግስህ።»187

ተደሳቹም ሲመልስለት እንዲህ ይበል፦

«بَارَكَ اللَّهُ لَكَ وَبَارَكَ عَلَيْكَ، وَجَزَاكَ اللَّهُ خَيْرًا، وَرَزَقَكَ اللَّهُ مِثْلَهُ، وَأَجْزَلَ ثَوَابَكَ».

«አላህ ይባርክልህ፤ በአንተም ላይ ይባርክ፤ አላህም መልካምን ይመንዳህ፤ አላህም አምሳያውን ይስጥህ፤ ምንዳህንም ያብዛልህ።»188

48 - ለልጆች ጥበቃ የሚደረግበት ዱዓእ

የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሐሰንና ሑሰይንን (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በአላህ ያስጠብቋቸው ነበር።

«أُعِيذُكُمَا بِكَلِمَاتِ اللَّهِ التَّامَّةِ مِنْ كُلِّ شَيْطَانٍ وَهَامَّةٍ، وَمِنْ كُلِّ عَيْنٍ لَامَّةٍ».

"ሁለታችሁንም ከማንኛውም ሰይጣንና መርዛማ ፍጡር፣ እንዲሁም ከማንኛውም ክፉ ዓይን ምሉዕ በሆኑት የአላህ ቃላት አስጠብቃለሁ።"189

49 - በሽተኛን በሚጠይቁ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ፤

«لَا بأْسَ طَهُورٌ إِنْ شَاءَ اللَّهُ».

«ምንም አይደለም ኣጽጂ ነው፤ በአላህ ፍቃድ»190

«أَسْأَلُ اللَّهَ العَظِيمَ رَبَّ العَرْشِ العَظِيمِ أَنْ يَشْفيَكَ».

«ታላቁ አላህን የታላቁን ዐርሽ ጌታ እንዲፈውስህ እጠይቃለሁ።»

ሰባት ጊዜ191

50. ህመምተኛን የመጠየቅ ትሩፋት

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ ብለዋል፦

«إِذَا عَادَ الرَّجُلُ أَخَاهُ الْمُسْلِمَ مَشَى فِي خِرَافَةِ الجَنَّةِ حَتَّى يَجْلِسَ، فَإِذَا جَلَسَ غَمَرَتْهُ الرَّحْمَةُ، فَإِنْ كَانَ غُدْوَةً صَلَّى عَلَيْهِ سَبْعُونَ أَلْفَ مَلَكٍ حَتَّى يُمْسِيَ، وَإِنْ كَانَ مَسَاءً صَلَّى عَلَيْهِ سَبْعُونَ أَلْفَ مَلَكٍ حَتَّى يُصْبِحَ».

«አንድ ሰው (የታመመ) ሙስሊም ወንድሙን በጠየቀ ጊዜ እስኪቀመጥ ድረስ በጀነት ፍሬዎች ውስጥ ይራመዳል። ከተቀመጠም እዝነት ትሸፍነዋለች። ጧት ከሆነ እስኪያመሽ ድረስ ሰባ ሺህ መላእክቶች ለርሱ ዱዓ ያደርጉለታል። ማታ ከሆነም እስኪያነጋ ድረስ ሰባ ሺህ መላእክቶች ለርሱ ዱዓ ያደርጉለታል።»192.

51 - በህይወቱ ተስፋ የቆረጠ በሽተኛ የሚያደርገው ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي، وَارْحَمْنِي، وَأَلْحِقْنِي بِالرَّفِيقِ الأَعْلَى».

«አላህ ሆይ! ማረኝ፤ እዘንልኝም፤ ከከፍተኛው ወዳጅ ጋር አገናኘኝ፡፡»193

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሞታቸው ጊዜ ሁለት እጃቸውን ውሃ ውስጥ እያስገቡ ፊታቸውን ይጠርጉና እንዲህ ይሉ ነበር፡

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ

«ከአላህ በቀር በእዉነት የሚገዙት አምላክ የለም»

إِنَّ لِلْمَوْتِ سَكَرَاتٍ».

«በእርግጥም ለሞት መከራዎች አሉት»194

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَاللَّهُ أَكْبَرُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ».

ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ አላህም ታላቅ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው፤ አጋር የለውም። ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ በአላህ ካልሆነ በስተቀር ብልሃትም ሆነ ሃይል የለም።195

 

52. ሞት አፋፍ ላይ ያለን ሰው "ላ ኢላሃ ኢለሏህን" ተልቂን ማስደረግ (ማስባል)

«مَنْ كَانَ آخِرُ كَلَامِهِ

«ከዱኒያ የመሰናበቻ ቃሉ የሆነ ሰው

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ

ከአላህ በቀር በእዉነት የሚገዙት አምላክ የለም።

دَخَلَ الجَنَّة».

ጀነት ገባ።»196.

53 - መከራ የደረሰበት ሰው የሚያደርገው ዱዓእ

«إِنَّا لِلَّهِ وَإِنَّا إِلَيْهِ رَاجِعُونَ، اللَّهُمَّ أْجُرْنِي فِي مُصِيبَتِي، وَأَخْلِفْ لِي خَيْرًَا مِنْهَا».

«እኛ ለአላህ ነን ወደርሱም ተመላሾች ነን፤ አላህ ሆይ በመከራዬ ምንዳን ስጠኝ፤ ከርሱ የተሻለንም ለኔ ተካልኝ»197

54. የሟችን ዓይን ሲከድኑ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِفُلَانٍ (بِاسْمِهِ) وَارْفَعْ دَرَجَتَهُ فِي المَهْدِيِّينَ، وَاخْلُفْهُ فِي عَقِبِهِ فِي الغَابِرِينَ، وَاغْفِرْ لَنَا وَلَهُ يَا رَبَّ العَالَمِينَ، وَافْسَحْ لَهُ فِي قَبْرِهِ، وَنَوِّرْ لَهُ فِيهِ».

«አላህ ሆይ! እገሌን (ስሙን በመጥቀስ) ማረው፤ ደረጃውንም ቅን መንገድ በተመሩት ሰዎች ውስጥ ከፍ አድርግለት፤ ወደኋላ በቀሩት ዘሮቹም ውስጥ ተካው፤ የዓለማት ጌታ ሆይ! ለእኛም ለእርሱም ማርልን፤ ቀብሩንም አስፋለት አብራለትም።»198

55. በሟች ላይ በሚሰገድ ሰላት ውስጥ ለሟቹ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لَهُ وَارْحَمْهُ، وَعَافِهِ، وَاعْفُ عَنْهُ، وَأَكْرِمْ نُزُلَهُ، وَوَسِّعْ مُدْخَلَهُ، وَاغْسِلْهُ بِالمَاءِ وَالثَّلْجِ وَالبَرَدِ، وَنَقِّهِ مِنَ الخَطَايَا كَمَا نَقَّيْتَ الثَّوْبَ الأَبْيَضَ مِنَ الدَّنَسِ، وَأَبْدِلْهُ دَارًا خَيْرًا مِنْ دَارِهِ، وَأَهْلاً خَيْرًا مِنْ أَهْلِهِ، وَزَوْجًَا خَيًْرا مِنْ زَوْجِهِ، وَأَدْخِلْهُ الجَنَّةَ، وَأَعِذْهُ مِنْ عَذَابِ القَبْرِ [وَعَذَابِ النَّارِ]».

«አላህ ሆይ ማረው፣ እዘንለትም፣ ሰላምም አድርገው፣ ይቅርም በለው፣ ማረፊያውንም አክብርለት፣ መግቢያውንም አስፋለት፣ በውሃ፣ በበረዶና በጤዛም እጠበው፣ ነጭ ልብስ ከእድፍ እንደሚጠራ ከኃጢአት አጥራው፣ ከቤቱም የተሻለ ቤትን፣ ከቤተሰቡም የተሻለ ቤተሰብን፣ ከሚስቱም የተሻለች ሚስትን ቀይርለት፣ ጀነትንም አስገባው፣ ከቀብር ቅጣት [እና ከእሳት ቅጣትም] ጠብቀው»199

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِحَيِّنَا وَمَيِّتِنَا، وَشَاهِدِنَا وَغَائِبِنَا، وَصَغِيرِنَا وَكَبِيرِنَا، وَذَكَرِنَا وَأُنْثَانَا، اللَّهُمَّ مَنْ أَحْيَيْتَهُ مِنَّا فَأَحْيِهِ عَلَى الإِسْلَامِ، وَمَنْ تَوَفَّيْتَهُ مِنَّا فَتَوَفَّهُ عَلَى الإِيمَانِ، اللَّهُمَّ لَا تَحْرِمْنَا أَجْرَهُ، وَلَا تُضِلَّنَا بَعْدَهُ».

«አላህ ሆይ! በህይወት ያለነውንም፣ የሞቱብንም፣ በቅርብ ያለነውንም ሩቅ ያሉትንም፣ ትልልቆቻችንንም፣ ትንንሾቻችንንም፣ ወንዶቻችንንም፣ ሴቶቻችንንም ማርልን። አላህ ሆይ! ከመካከላችን የምታኖረውንም ኑሮውን በኢስላም አድርግለት፤ የምትገለውንም በእምነት ላይ እንዲሞት አድርገው። አላህ ሆይ! ምንዳውን አትንፈገን ከእርሱም በኋላ እጣችንን ጥመት አታድርግብን።»200

«اللَّهُمَّ إِنَّ فُلَانَ بْنَ فُلَانٍ فِي ذِمَّتِكَ، وَحَبْلِ جِوَارِكَ، فَقِهِ مِنْ فِتْنَةِ القَبْرِ، وَعَذَابِ النَّارِ، وَأَنْتَ أَهْلُ الوَفَاءِ وَالحَقِّ، فَاغْفِرْ لَهُ وَارْحَمْهُ إِنَّكَ أَنْتَ الغَفُورُ الرَّحيمُ».

«አላህ ሆይ! እገሌ የእገሌ ልጅ በአንተ አደራና በጥበቃህ ስር ነው፤ ከቀብር ፈተናና ከእሳት ቅጣትም ጠብቀው። አንተ የቃል ኪዳንና የእውነት ባለቤት ነህ፤ ምህረት አድርግለት፤ እዘንለትም፤ አንተ መሓሪ አዛኝ ነህና።»201

«اللَّهُمَّ عَبْدُكَ وَابْنُ أَمَتِكَ احْتَاجَ إِلَى رَحْمَتِكَ، وَأَنْتَ غَنِيٌّ عَنْ عَذَابِهِ، إِنْ كَانَ مُحْسِنًا فَزِدْ فِي حَسَنَاتِهِ، وَإِنْ كَانَ مُسِيئًا فَتَجَاوَزْ عَنْهُ».

«አላህ ሆይ! ባሪያህና የሴት ባሪያህ ልጅ ወደ እዝነትህ ፈላጊ ሆኗል፤ አንተ እርሱን ከመቅጣት የተብቃቃህ ነህ። መልካም ሠሪ ከነበረ በመልካም ሥራው ላይ ጨምርለት፤ አጥፊም ከነበረ ይቅር በለው።»202

56 - ለሟች ህፃን በጀናዛ ሶላት ላይ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ أَعِذْهُ مِنْ عَذَابِ القَبْرِ».

«አሏህ ሆይ! ከቀብር ቅጣት ጠብቀው።»203

እንዲህም ቢሉ፦

«اللَّهُمَّ اجْعَلْهُ فَرَطًا وَذُخْرًا لِوَالِدَيْهِ، وَشَفِيعًا مُجَابًا، اللَّهُمَّ ثَقِّلْ بِهِ مَوَازِينَهُمَا، وَأَعْظِمْ بِهِ أُجورَهُمَا، وَأَلْحِقْهُ بِصَالِحِ المُؤْمِنِينَ، وَاجْعَلْهُ فِي كَفَالَةِ إِبْرَاهِيمَ، وَقِهِ بِرَحْمَتِكَ عَذَابَ الجَحِيمِ، وَأَبْدِلْهُ دَارًا خَيْرًا مِنْ دَارِهِ، وَأَهْلًا خَيْرًا مِنْ أَهْلِهِ، اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِأَسْلَافِنَا، وَأَفْرَاطِنَا، وَمَنْ سَبَقَنَا بِالإِيمَانِ».

«አላህ ሆይ! ለወላጆቹ ቀዳሚ ምንዳና ተቀማጭ ሀብት፣ ተቀባይነት ያለው አማላጅም አድርገው። አላህ ሆይ! በእርሱ ሰበብ ሚዛኖቻቸውን አክብድላቸው፣ ምንዳቸውንም በእርሱ አብዛላቸው፣ ከደጋግ ምእመናንም ጋር አስጠጋው፣ በኢብራሂም እንክብካቤ ስርም አድርገው፣ በእዝነትህም ከእሳት ቅጣት ጠብቀው፣ ከቤቱ የተሻለ ቤትን፣ ከቤተሰቡም የተሻለ ቤተሰብን ቀይርለት። አላህ ሆይ! ላለፉት አባቶቻችን፣ ለቀደሙት ህፃናቶቻችን እና በእምነት ለቀደሙን ሁሉ ማርልን።»

መልካም ነው።204

«اللَّهُمَّ اجْعَلْهُ لَنَا فَرَطًا، وَسَلَفًا، وَأَجْرًا».

«አላህ ሆይ! ለእኛ ቀዳሚ፣ ተቀማጭና ምንዳ አድርግልን።»205

57. የሟችን ቤተሰብ ለማፅናናት የሚደረግ ዱዓእ

«إِنَّ للَّهِ مَا أَخَذَ، وَلَهُ مَا أَعْطَى، وَكُلُّ شَيْءٍ عِنْدَهُ بِأَجَلٍ مُسَمَّى... فَلْتَصْبِرْ وَلْتَحْتَسِبْ».

«በርግጥም የወሰደው የአላህ ነው፣ የሰጠውም የርሱ ነው፤ ሁሉም ነገር እርሱ ዘንድ የተወሰነ ጊዜ አለው... ስለዚህ ትታገስ፤ ምንዳውንም (ከአላህ) ትጠብቅ።»206

እንዲህም ቢሉ፦

«أَعْظَمَ اللَّهُ أَجْرَكَ، وَأَحْسَنَ عَزَاءَكَ، وَغَفَرَ لِمَيِّتِكَ»

«አላህ ምንዳህን ያብዛልህ፤ መጽናናትህንም ያሳምርልህ፤ ለሟችህም ምህረት ያድርግለት።»

መልካም ነው207

58 - ሟችን ቀብር ውስጥ ሲያስገቡ የሚደረግ ዱዓእ

«بِسْمِ اللَّهِ وَعَلَى سُنَّةِ رَسُولِ اللَّهِ».

«በአላህ ስም እና በአላህ መልዕክተኛ ሱና ላይ።››208

59. ሟችን ከቀበሩ በኋላ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ اغْفِرْ لَهُ، اللَّهُمَّ ثَبِّتْهُ».

«አላህ ሆይ! ማረው፣ አላህ ሆይ! አፅናው፡፡»209

60. ቀብርን ሲዘይሩ የሚደረግ ዱዓእ፤

«السَّلاَمُ عَلَيْكُمْ أَهْلَ الدِّيَارِ، مِنَ المُؤْمِنِينَ وَالمُسْلِمِينَ، وَإِنَّا إِنْ شَاءَ اللَّهُ بِكُمْ لَاحِقُونَ، [وَيَرْحَمُ اللَّهُ المُسْتَقدِمِينَ مِنَّا وَالمُسْتأْخِرِينَ] أَسْاَلُ اللَّهَ لَنَا وَلَكُمُ العَافِيَةَ».

«ከአማኞችና ከሙስሊሞች የሆናችሁ የዚህ ስፍራ ነዋሪዎች ሰላም በእናንተ ላይ ይሁን፣ እኛም አላህ ካለ እናንተን የምንቀላቀል ነን፣ [አላህ ከእኛ ቀድመው የሄዱትንም ሆነ ወደ ኋላ የሚቀሩትን ይዘንላቸው] ለእኛም ለእናንተም ደህንነትን ከአላህ እጠይቃለሁ»210.

61. በንፋስ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ፤

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ خَيْرَهَا، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّهَا».

«አላህ ሆይ! እኔ ኸይሯን እማፀንሃለሁ፤ ከክፋቷም በአንተው እጠበቃለሁ።"211

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ خَيْرَهَا، وَخَيْرَ مَا فِيهَا، وَخَيْرَ مَا أُرْسِلَتْ بِهِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّهَا، وَشَرِّ مَا فِيهَا، وَشَرِّ مَا أُرْسِلَتْ بِهِ».

«አላህ ሆይ! እኔ መልካሟን፣ በውስጧ ያለውን መልካም ነገርና የተላከችበትን መልካም ነገር እጠይቅሀለሁ። ከክፋቷ፣ በውስጧ ካለው ክፋትና ከተላከችበት ክፋትም ባንተ እጠበቃለሁ።»212

62. ነጎድጓድ ሲሰማ የሚደረግ ዱዓእ፤

«سُبْحَانَ الَّذِي يُسَبِّحُ الرَّعْدُ بِحَمْدِهِ وَالمَلَائِكَةُ مِنْ خِيفَتِهِ».

«ነጎድጓድም እያመሰገነ መላእክትም እርሱን ፈርተው የሚያወድሱት አላህ ጥራት ይገባው።»213

63 - ዝናብን ለመፈለግ ከሚደረጉ ዱዓዎች

«اللَّهُمَّ اسْقِنَا غَيْثًا مُغِيثًا مَرِيئًا مَرِيعًا، نَافِعًا غَيْرَ ضَارٍّ، عَاجِلًا غَيْرَ آجِلٍ».

«አምላኬ ሆይ ራስ ረጠብ የሚያደርግ ዝናብን አጠጣን አደጋ ያላዘለ አብቃይ ጠቃሚ ጎጂ ያልሆነ ዝናብ በአስቸኳይ የማይዘገይ ሲሆን አዝንብልን።»214

«اللَّهُمَّ أَغِثْنَا، اللَّهُمَّ أَغِثْنَا، اللَّهُمَّ أَغِثْنَا».

«አላህ ሆይ! ዝናብ አዝንብልን፣ አላህ ሆይ! ዝናብ አዝንብልን፣ አላህ ሆይ! ዝናብ አዝንብልን።»215

«اللَّهُمَّ اسْقِ عِبَادَكَ، وَبَهَائِمَكَ، وَانْشُرْ رَحْمَتَكَ، وَأَحْيِي بَلَدَكَ المَيِّتَ».

«አምላኬ ሆይ ባሮችህንና እንሰሳቶችህን አጠጣቸው፤ እዝነትህን አሰራጭ፤ የሞተውን ሀገርህን ህያው አድርግ፡፡››216

64. ዝናብ ሲታይ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ صَيِّبًا نَافِعًا».

«አላህ ሆይ! የሚንቧቧና ጠቃሚ አድርገው።»217

65. ዝናብ ከወረደ በኋላ የሚደረግ ዚክር

«مُطِرْنَا بِفَضْلِ اللَّهِ وَرَحْمَتِهِ».

«በአላህ እዝነትና ችሮታ ዝናብ አገኘን።»218

66 - ዝናብ እንዲያባራ ከሚደረጉ ዱዓዎች

«اللَّهُمَّ حَوَالَيْنَا وَلَا عَلَيْنَا، اللَّهُمَّ عَلَى الآكَامِ وَالظِّرَابِ، وَبُطُونِ الأَوْدِيَةِ، وَمَنَابِتِ الشَّجَرِ».

«አምላካችን ሆይ በኛ ላይ ሳይሆን በዙሪያችን ላይ በኮረብታና በጉብታ በሸለቆዎች እምብርት በዛፍ መብቂያ ስፍራ (አዝንብልን»219

67. ጨረቃ ሲታይ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُمَّ أَهِلَّهُ عَلَيْنَا بِالأَمْنِ وَالإِيمَانِ، وَالسَّلَامَةِ وَالإِسْلَامِ، وَالتَّوْفِيقِ لِمَا تُحِبُّ رَبَّنَا وَتَرْضَى، رَبُّنَا وَرَبُّكَ اللَّهُ».

«አላህ ታላቅ ነው። አላህ ሆይ! በፀጥታና በእምነት፣ በሰላምና በእስልምና፣ ጌታችን ሆይ! አንተ ወደምትወደውና ወደሚያስደስትህ ነገር በመግጠም (ጨረቃዋን) አውጣብን። ጌታችንም ጌታሽም አላህ ነው።220»

68. ፆመኛ በሚያፈጥር ጊዜ የሚያደርገው ዱዓእ

«ذَهَبَ الظَّمَأُ وَابْتَلَّتِ العُرُوقُ، وَثَبَتَ الأَجْرُ إِنْ شَاءَ اللَّهُ».

«ጥም ተወገደ፤ የደም ሥሮችም ረጠቡ፤ ምንዳውም በአላህ ፈቃድ የተረጋገጠ ሆነ ማለት ነው።221.

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ بِرَحْمَتِكَ الَّتِي وَسِعَتْ كُلَّ شَيْءٍ أَنْ تَغْفِرَ لِي».

«አላህ ሆይ! ሁሉን ነገር ባካለለችው እዝነትህ ትምረኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡»222

69. ምግብ ከመብላት በፊት የሚደረግ ዱዓእ

«إِذَا أَكَلَ أَحَدُكُمْ طَعَامًا فَلْيَقُلْ:

«አንዳችሁ ምግብ ሲበላ እንዲህ ይበል፦

بِسْمِ اللَّهِ،

በአላህ ስም፣

فَإِنْ نَسِيَ فِي أَوَّلِهِ فَلْيَقُلْ:

መጀመሪያ ላይ ከረሳ እንዲህ ይበል፡-

بِسْمِ اللَّهِ فِي أَوَّلِهِ وَآخِرِهِ».

«ቢስሚላህ ለመጀመርያው ለመጨረሻውም።»223.

«مَنْ أَطْعَمَهُ اللَّهُ الطَّعَامَ فَلْيَقُلْ:

«አላህ ምግብ ያበላው ሰው እንዲህ ይበል፡-

اللَّهُمَّ بَارِكْ لَنَا فِيهِ وَأَطْعِمْنَا خَيْرًا مِنْهُ،

አላህ ሆይ በእሱ ባርክልን፤ ከእሱ የተሻለውንም አብላን፣

وَمَنْ سَقَاهُ اللَّهُ لَبَنًا فَلْيَقُلْ:

አላህ ወተት ያጠጣው ሰው እንዲህ ይበል፦

اللَّهُمَّ بَارِكْ لَنَا فِيهِ وَزِدْنَا مِنْهُ».

«አላህ ሆይ! በርሱ ባርክልን፤ ከርሱም ጨምርልን።»224

70. ምግብ በልቶ ሲጨረስ የሚደረግ ዱዓእ

«الحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي أَطْعَمَنِي هَذَا، وَرَزَقَنِيهِ، مِنْ غَيْرِ حَوْلٍ مِنِّي وَلَا قُوَّةٍ».

«የኔ ሀይልም ብልሀትም ሳይኖር ይህንን ምግብ ለመገበኝና ለለገሰኝ አላህ ምስጋና ይገባው።»225.

«الْحَمْدُ لِلَّهِ حَمْدًا كَثِيرًا طَيِّبًا مُبَارَكًا فِيهِ، غَيْرَ [مَكْفِيٍّ وَلَا] مُوَدَّعٍ، وَلَا مُسْتَغْنَىً عَنْهُ رَبَّنَا».

«ለአላህ ምስጋና የተገባው ነው። የበዛ፣ ምርጥ የሆነ፣ የተባረከ፣ [ያልተብቃቃንበትም ሆነ] ያልተተወ፣ ጌታችን ሆይ! ከሱ መብቃቃት የማይቻል የሆነ ምስጋና የተገባው ነው።»226

71. እንግዳው ለጋባዡ የሚያደርግለት ዱዓእ

«اللَّهُمَّ بَارِكْ لَهُمْ فِيمَا رَزَقْتَهُم، وَاغْفِرْ لَهُمْ وَارْحَمْهُمْ».

«አላህ ሆይ! በሰጠሃቸው ነገር በረካ አድርግላቸው። ይቅር በላቸው እዘንላቸውም።»227

72 - ምግብን ወይም መጠጥን ለመጠየቅ በዱዓእ በተዘዋዋሪ ማመልከት

«اللَّهُمَّ أَطْعِمْ مَنْ أَطْعَمَنِي، وَاسْقِ مَنْ سَقَانِي».

«አላህ ሆይ! ያበላኝን አብላው፤ ያጠጣኝንም አጠጣው፡፡»228

73 - በሰው ቤት በሚያፈጥር ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ

«أَفْطَرَ عِنْدَكُمُ الصَّائِمُونَ، وَأَكَلَ طَعَامَكُمُ الأَبْرَارُ، وَصَلَّتْ عَلَيْكُمُ المَلَائِكَةُ».

«ፆመኞች በእናንተ ዘንድ ያፍጥሩ፣ ምግባችሁንም ደጋጎች ይብሉት፣ መላእክትም ዱዓ ያድርጉላችሁ።»229

74. ፆመኛ ምግብ ቀርቦለት ባያፈጥር የሚያደርገው ዱዓእ

«إِذَا دُعِيَ أَحَدُكُمْ فَلْيُجِبْ، فَإِنْ كَانَ صَائِمًا فَلْيُصَلِّ، وَإِنْ كَانَ مُفْطِرًا فَلْيَطْعَمْ»،

«አንዳችሁ ከተጋበዘ ጥሪውን ይቀበል፤ ፆመኛ ከሆነ ዱዓ ያድርግ፣ ፆመኛ ካልሆነ ደግሞ ይብላ።»230

{ፈልዩሰሊ} ሲል፦ ዱዓ ያድርግ ማለት ነው።

75. ፆመኛ ሰው አንድ ሰው ከተሰዳደበው የሚለው

«إِنِّي صَائِمٌ، إِنِّي صَائِمٌ».

«እኔ ፆመኛ ነኝ፣ እኔ ፆመኛ ነኝ።»231.

76 - የመጀመሪያ ፍሬ በሚታይ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ بَارِكْ لَنَا فِي ثَمَرِنَا، وَبَارِكْ لَنَا فِي مَدِينَتِنَا، وَبَارِكْ لَنَا فِي صَاعِنَا، وَبَارِكْ لَنَا فِي مُدِّنَا».

"አላህ ሆይ! በፍሬያችን ለኛ ባርክልን፤ በከተማችንም ለኛ ባርክልን፤ በቁናችን ለኛ ባርክልን፤ በእፍኛችንም ለኛ ባርክልን።»232

77 - በሚያስነጥስ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ

«إِذَا عَطَسَ أَحَدُكُم فَلْيَقُلِ:

«ከእናንተ አንዱ ሲያስነጥሰው እንዲህ ይበል፡-

الحَمْدُ لِلَّهِ،

ምስጋና ሁሉ ለአላህ ይሁን፣

وَلْيَقُلْ لَهُ أَخُوهُ أَوْ صَاحِبُهُ:

ወንድሙ ወይም ባልንጀራው እንዲህ ይበለው፦

يَرْحَمُكَ اللَّهُ،

አላህ ይዘንልህ፣

فَإِذَا قَالَ لَهُ: يَرحَمُكَ اللَّهُ، فَلْيَقُلْ:

“የርሐሙከላህ” ካለው እርሱም እንዲህ ይበል፦

يَهْدِيكُمُ اللَّهُ وَيُصْلِحُ بَالَكُم».

«አላህ ይምራህ ጉዳይህንም ያስተካክልልህ።»233.

78. ካፊር አስነጥሶ አላህን ባመሰገነ ጊዜ የሚባለው

«يَهْدِيكُمُ اللَّهُ وَيُصْلِحُ بَالَكُمْ».

«አላህ ይምራህ ጉዳይህንም ያስተካክልልህ።)234.

79. አዲስ ላገባ ሰው ዱዓእ ማድረግ

«بَارَكَ اللَّهُ لَكَ، وَبَارَكَ عَلَيْكَ، وَجَمَعَ بَيْنَكُمَا فِي خَيْرٍ».

«አላህ ይባርክልህ፤ በአንተም ላይ ይባርክ፤ ሁለታችሁንም በመልካም ያሰባስባችሁ።»235

80 - አዲስ ያገባና እንስሳ የገዛ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ

ከእናንተ አንዳችሁ ሴትን ባገባ፣ ወይም አገልጋይን በገዛ ጊዜ እንዲህ ይበል፦

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَسْأَلُكَ خَيْرَهَا، وَخَيْرَ مَا جَبَلْتَهَا عَلَيْهِ، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّهَا، وَشَرِّ مَا جَبَلْتَهَا عَلَيْهِ،

«አላህ ሆይ! እኔ ኸይሯንና የፈጠርካትን ተፈጥሮ ኸይር እጠይቅሀለሁ፤ ከክፋትና ከፈጠርካት ተፈጥሮ ክፋትም በአንተ እጠበቃለሁ።»

وَإِذَا اشْتَرَى بَعِيرًا فَلْيَأْخُذْ بِذِرْوَةِ سَنَامِهِ وَلْيَقُلْ مِثْلَ ذَلِكَ».

«ግመልንም በገዛ ጊዜ የሻኛዋን ጫፍ ይያዝና እንደዛው ይበል።"236

81. ከሚስት ጋር ግንኙነት ከማድረግ በፊት የሚደረግ ዱዓእ፤

«بِسْمِ اللَّهِ، اللَّهُمَّ جَنِّبْنَا الشَّيْطَانَ، وَجَنِّبِ الشَّيْطَانَ مَا رَزَقْتَنَا».

«በአላህ ስም፤ አላህ ሆይ! ሰይጣንን ከእኛ አርቅልን፣ ከሰጠኸንም ነገር ሰይጣንን አርቅልን።»237

82. በቁጣ ጊዜ የሚባል ዱዓእ

«أَعُوذُ بِاللَّهِ مِنَ الشَّيْطَانِ الرَّجِيمِ».

«ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ።»238

83 - ፊትና ላይ የወደቀን ሰው ያየ የሚያደርገው ዱዓእ

«الحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي عَافَانِي مِمَّا ابْتَلَاكَ بِهِ، وَفَضَّلَنِي عَلَى كَثِيرٍ مِمَّنْ خَلَقَ تَفْضِيلًا».

«በአንተ ላይ ካደረሰብህ ፈተና ያተረፈኝ አላህ ምስጋና ይገባው፤ ከብዙሀኑ ፍጡራኑም በርግጥ አስበለጠኝ።»239

84. በስብሰባ (መጅሊስ) ላይ የሚባል

ከኢብኑ ዑመር (አላህ ይውደድላቸውና) ተይዞ እንዲህ አሉ፡- ለአላህ መልእክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በአንድ መቀመጫ ከመነሳታቸው በፊት መቶ ጊዜ ይቆጠርላቸው ነበር፡-

«رَبِّ اغْفِرْ لِي، وَتُبْ عَلَيَّ، إِنَّكَ أَنْتَ التَّوَّابُ الغَفُورُ».

«ጌታዬ ማረኝ! ተውባዬን ተቀበለኝ፤ እነሆ አንተ ተመላሾችን የምትቀበልና መሀሪ ነህና።»240

85. የመቀማመጥ ከፋራ

«سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ وَبِحَمْدِكَ، أَشْهَدُ أَنْ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنْتَ، أَسْتَغْفِرُكَ وَأَتُوبُ إِلَيْكَ».

«አላህ ሆይ! ጥራት ላንተ ተገባ፤ ምስጋናም ላንተ ይሁን፤ ካንተ በስተቀር ሌላ በእውነት የሚመለክ አምላክ አለመኖሩን እመሰክራለሁ፤ ምሕረትህንም እለምነሃለሁ፤ ከኃጢኣቴ ተጸጽቼ ወደ አንተ እመለሳለሁ፡፡»241

86 - "ገፈረሏሁ ለከ" ላለ ሰው የሚደረግ ዱዓእ

«وَلَكَ».

«ላንተም»242

87 - ውለታ ለዋለልህ ሰው የሚደረግ ዱዓእ

«جَزَاكَ اللَّهُ خَيْرًا».

«መልካም ምንዳህን አላህ ይክፈልህ።»243.

88. አላህ ከደጃል የሚጠብቅበት መጠበቂያ

«مَنْ حَفِظَ عَشْرَ آيَاتٍ مِنْ أَوَّلِ سُورَةِ الكَهْفِ عُصِمَ مِنَ الدَّجَّالِ».

«የሱረቱል ከህፍ መጀመሪያ አስር አንቀጾችን የሸመደደ ሰው ከደጃል ይጠበቃል።»244

በእያንዳንዱ ሶላት ከመጨረሻው ተሸሁድ በኋላ ከፈተናው በአላህ መጠበቅ245

89 - «እኔ ለአላህ ብዬ እወድሃለሁ» ላለ ሰው የሚደረግ ዱዓእ

«أَحَبَّكَ الَّذِي أَحْبَبْتَنِي لَهُ».

«ያ ለእርሱ ብለህ የወደድከኝ (አላህ) ይውደድህ።»246

90. ገንዘቡን ላቀረበልህ ሰው የሚደረግ ዱዓእ

«بَارَكَ اللَّهُ لَكَ فِي أَهْلِكَ وَمَالِكَ».

( አላህ በቤተሰብህና በገንዘብህ ይባርክልህ።)247.

91 - ብድር ላበደረ ሰው ብድሩን ሲመልሱ የሚደረግ ዱዓእ

«بارَكَ اللَّهُ لَكَ فِي أَهْلِكَ وَمَالِكَ، إِنَّمَا جَزَاءُ السَّلَفِ الحَمْدُ وَالأَدَاءُ».

«አላህ በቤተሰብህና በገንዘብህ በረከት ያድርግልህ፤ የብድር ምንዳው ምስጋናና መክፈል ብቻ ነው።»248

92 - ሺርክን በመፍራት የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ أَنْ أُشْرِكَ بِكَ وَأَنَا أَعْلَمُ، وَأَسْتَغْفِرُكَ لِمَا لَا أَعْلَمُ».

«አላህ ሆይ! እያወቅኩኝ ባንተ ላይ ከማጋራት ባንተ እጠበቃለሁ፤ ለማላውቀው ደግሞ ምህረትህን እጠይቅሀለሁ።»249

93. "አላህ ይባርክህ" ላለ ሰው የሚደረግ ዱዓ

«وَفِيكَ بَارَكَ اللَّهُ».

«አላህ አንተንም ይባርክህ።»250.

94 - መጥፎ ገድን (ጢየራን) ሲጠሉ የሚደረግ ዱዓእ

«اللَّهُمَّ لَا طَيْرَ إِلَّا طَيْرُكَ، وَلَا خَيْرَ إِلَّا خَيْرُكَ، وَلَا إِلَهَ غَيْرُكَ».

«አላህ ሆይ! ከአንተ ውሳኔ ውጭ ምንም ገድ የለም፤ ከአንተም በጎ ነገር ውጭ ሌላ በጎ ነገር የለም፤ ካንተ በቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው የለም።"251

95 - መጓጓዣ ላይ ሲወጣ የሚባለው ዱዓእ

«بِسْمِ اللَّهِ، وَالحَمْدُ للَّهِ

«በአላህ ስም፤ ምስጋናም ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው።

﴿سُبْحَانَ الَّذِي سَخَّرَ لَنَا هَذَا وَمَا كُنَّا لَهُ مُقْرِنِينَ

{«ያ ይህንን የማንችለው ስንኾን ለእኛ ያገራለን ጌታ ጥራት ተገባው፡፡

وَإِنَّا إِلَى رَبِّنَا لَمُنقَلِبُونَ﴾،

እኛም በእርግጥ ወደ ጌታችን ተመላሾች፤ነን» (እንድትሉ)፣

الحَمْدُ لِلَّهِ، الحَمْدُ لِلَّهِ، الحَمْدُ لِلَّهِ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، سُبْحَانَكَ اللَّهُمَّ إِنِّي ظَلَمْتُ نَفْسِي فَاغْفِرْ لِي؛ فَإِنَّهُ لَا يَغْفِرُ الذُّنُوبَ إِلَّا أَنْتَ».

ምስጋና ለአላህ ይሁን፣ ምስጋና ለአላህ ይሁን፣ ምስጋና ለአላህ ይሁን፣ አላህ ታላቅ ነው፣ አላህ ታላቅ ነው፣ አላህ ታላቅ ነው፣ አላህ ሆይ ጥራት ይገባህ እኔ ነፍሴን በድያለሁና ማረኝ፤ ከአንተ ውጭ ኃጢአቶችን የሚምር ማንም የለምና»252

96. የጉዞ ዱዓ

«اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ، اللَّهُ أَكْبَرُ،

(አላህ ታላቅ ነው፤ አላህ ታላቅ ነው፤ አላህ ታላቅ ነው፤)

سُبْحَانَ الَّذِي سَخَّرَ لَنَا هَذَا وَمَا كُنَّا لَهُ مُقْرِنِينَ

ያ ይህንን የማንችለው ስንኾን ለእኛ ያገራለን ጌታ ጥራት ይገባው፡፡

وَإِنَّا إِلَى رَبِّنَا لَمُنقَلِبُونَ،

እኛም በእርግጥ ወደ ጌታችን ተመላሾች ነን፣

اللَّهُمَّ إِنّا نَسْأَلُكَ فِي سَفَرِنَا هَذَا البِرَّ وَالتَّقْوَى، وَمِنَ العَمَلِ مَا تَرْضَى، اللَّهُمَّ هَوِّنْ عَلَيْنَا سَفَرَنَا هَذَا وَاطْوِ عَنَّا بُعْدَهُ، اللَّهُمَّ أَنْتَ الصَّاحِبُ فِي السَّفَرِ، وَالخَليفَةُ فِي الأَهْلِ، اللَّهُمَّ إِنِّي أَعُوذُ بِكَ مِنْ وَعْثَاءِ السَّفَرِ، وَكَآبَةِ المَنْظَرِ، وَسُوءِ المُنْقَلَبِ فِي المَالِ وَالأَهْلِ»،

አላህ ሆይ! በዚህ ጉዟችን ላይ መልካምነትንና አላህን መፍራትን፣ ከስራም አንተ የምትወደውን እንጠይቅሃለን። አላህ ሆይ! ይህንን ጉዟችንን አግራልን፤ ርቀቱንም አሳጥርልን። አላህ ሆይ! አንተ በጉዞ ላይ ጓደኛ ነህ፤ በቤተሰብም ውስጥ ተተኪ ነህ። አላህ ሆይ! ከጉዞ ድካም፣ ከሚያሳዝን እይታ፣ በገንዘብና በቤተሰብ ላይ ከሚመጣ መጥፎ መመለስ በአንተ እጠበቃለሁ።

ተመልሶም ሲመጣም እንዲሁ ካለ በኋላ ተከታዩንም ያክላል፦

«آيِبُونَ، تائِبُونَ، عَابِدُونَ، لِرَبِّنَا حَامِدُونَ».

(ተመላሾች፣ ተፀፃቾች፣ አምላኪዎች፣ ለጌታችን አመስጋኞች ነን።)253

 

 

97 - መንደር ወይም ከተማ ሲገባ የሚባል ዱዓእ

«اللَّهُمَّ رَبَّ السَّمَوَاتِ السَّبْعِ وَمَا أَظْلَلْنَ، وَرَبَّ الأَرَضِينَ السَّبْعِ وَمَا أَقْلَلْنَ، وَرَبَّ الشَّياطِينِ وَمَا أَضْلَلْنَ، وَرَبَّ الرِّيَاحِ وَمَا ذَرَيْنَ، أَسْأَلُكَ خَيْرَ هَذِهِ القَرْيَةِ، وَخَيْرَ أَهْلِهَا، وَخَيْرَ مَا فِيهَا، وَأَعُوذُ بِكَ مِنْ شَرِّهَا، وَشَرِّ أَهْلِهَا، وَشَرِّ مَا فِيهَا».

«የሰባቱ ሰማያትና ያጠለሉት ነገር ጌታ፣ የሰባቱ ምድሮችና የተሸከሙት ነገር ጌታ፣ የሸይጧኖችና ያጠመሙት ነገር ጌታ፣ የንፋሶችና የበተኑት ነገር ጌታ የሆንከው አላህ ሆይ! የዚህችን ከተማ መልካም ነገር፣ የነዋሪዎቿን መልካም ነገር፣ እንዲሁም በውስጧ ያለውን መልካም ነገር እጠይቅሃለሁ። ከክፋቷ፣ ከነዋሪዎቿ ክፋትና በውስጧ ካለው ነገር ክፋትም በአንተ እጠበቃለሁ።»254

98. ወደ ገበያ ሲገባ የሚባለው ዱዓእ

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ، وَلَهُ الحَمْدُ، يُحْيِي وَيُمِيتُ، وَهُوَ حَيٌّ لَا يَمُوتُ، بِيَدِهِ الخَيْرُ، وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው፤ አጋር የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። ህያው ያደርጋልም ይገላልም። እርሱ ህያው ነው አይሞትም። መልካም ነገር ሁሉ በእጁ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።»255

99 - መጓጓዣ ሲዳከም የሚባለው ዱዓእ

«بِسْمِ اللَّهِ».

"በአላህ ስም"256

100. መንገደኛ የሆነ ሰው ነዋሪ ለሆነ የሚያደርግለት ዱዓእ

«أَسْتَوْدِعُكُمُ اللَّهَ الَّذِي لَا تَضِيعُ وَدَائِعُهُ».

(እናንተን (እንዲጠብቃችሁ) አደራውን ለማያጠፋው አላህ አደራ እሰጠዋለሁ።»257

101. ነዋሪ የሆነ ለመንገደኛው የሚያደርግለት ዱዓእ

«أَسْتَوْدِعُ اللَّهَ دِينَكَ، وَأَمَانَتَكَ، وَخَوَاتِيمَ عَمَلِكَ».

(ሃይማኖትህን፣ እምነትህንና የስራህን ፍፃሜ ለአላህ አደራ እሰጠዋለሁ።)258.

«زَوَّدَكَ اللَّهُ التَّقْوَى، وَغَفَرَ ذَنْبَكَ، وَيَسَّرَ لَكَ الخَيْرَ حَيْثُ ما كُنْتَ».

«አላህ ፍራቻውን ያስሰንቅህ፤ ወንጀልህንም ይማርልህ፤ የትም ሆነህ መልካምን ያግራልህ።»259.

102 - በጉዞ ወቅት የሚደረግ ተክቢርና ተስቢሕ

ጃቢር - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ አሉ፦ «ከፍ ወዳሉ ቦታዎች ስንወጣ ተክቢራ እንል ነበር፣ እንዲህ ይላል: (አላህ ታላቅ ነው) ስንወርድ ደሞ ተስቢሕ እንል ነበር።»260

እንዲህ ይላል: (አላህ ጥራት ተገባው)

103 - ጉዞ የወጣ ሰው የሰሐር ጊዜ ሲገባ የሚያደርገው ዱዓእ

«سَمَّعَ سَامِعٌ بِحَمْدِ اللَّهِ، وَحُسْنِ بَلَائِهِ عَلَيْنَا، رَبَّنَا صاحِبْنَا، وَأَفْضِلْ عَلَيْنَا، عَائِذًا بِاللَّهِ مِنَ النَّارِ».

«አንድ ሰሚ አላህን በማመስገናችን እና በእኛ ላይ ባዋለው መልካም ጸጋ ሰማ። ጌታችን ሆይ! አብረኸን ሁን፤ ጸጋህንም ለግሰን። ከእሳት በአላህ እጠበቃለሁ።»261

104 - ከጉዞም ይሁን ከሌላ ቦታ ወደ አንድ ስፍራ በሚያርፍ ወቅት የሚደረግ ዱዓእ

«أَعُوذُ بِكَلِمَاتِ اللَّهِ التَّامَّاتِ مِنْ شَرِّ مَا خَلَقَ».

«ከፍጡራኑ ክፋት ሙሉ በሆኑ የአላህ ቃላት እጠበቃለሁ።»262

105. ከጉዞ ሲመለስ የሚደረግ ዚክር

«يُكَبِّرُ عَلَى كُلِّ شَرَفٍ ثَلَاثَ تَكْبِيرَاتٍ ثُمَّ يَقُولُ:

«በእያንዳንዱ ከፍታ ላይ ሶስት ጊዜ ተክቢራ ያደርጋል፤ ከዚያም ይላል፡-

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ، وَلَهُ الحَمْدُ، وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ، آيِبُونَ، تَائِبُونَ، عَابِدُونَ، لِرَبِّنا حَامِدُونَ، صَدَقَ اللَّهُ وَعْدَهُ، وَنَصَرَ عَبْدَهُ، وَهَزَمَ الأَحْزابَ وَحْدَهُ».

«ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም፤ ብቸኛና አጋር የለውም። ንግስና ለርሱ የተገባ ነው። ምስጋናም ለርሱ የተገባ ነው። እርሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው። ተመላሾች፣ ተፀፃቾች፣ አምላኪዎች፣ ለጌታችን አመስጋኞች ነን። አላህ ቃሉን በእውነት ሞላ፣ ባሪያውንም ረዳ፣ የጥመት ጭፍራንም ብቻውን አሸነፈ።»263

106. የሚያስደስተው ወይም የሚያስከፋው ነገር ያጋጠመው ሰው የሚለው

ነቢዩ ﷺ የሚያስደስታቸው ነገር ሲያጋጥማቸው እንዲህ ይሉ ነበር፦

«الحَمْدُ لِلَّهِ الَّذِي بِنِعْمَتِهِ تَتِمُّ الصَّالِحَاتُ».

«ያ በጎዎችም በጸጋው የሚሞሉት አላህ ምስጋና ተገባው።»

የሚጠሉት ነገር ሲያጋጥመው እንዲህ ይበል፦

«الحَمْدُ لِلَّهِ عَلَى كُلِّ حَالٍ».

«በሁሉም ሁኔታ ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው።»264

107. በነቢዩ ﷺ ላይ ሶላት የማውረድ ትሩፋት

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«مَنْ صَلَّى عَلَيَّ صَلَاةً صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ بِهَا عَشْرًا».

«በኔ ላይ አንዲት ሶላት ያወረደ አላህ በርሷ ምክንያት በርሱ ላይ አስር ሶለዋት ያወርድለታል።»265 ለምሳሌ እንዲህ ማለቱ፦ (አላህ ሆይ! በነቢያችን ሙሐመድ ላይ ሶላትና ሰላምን አውርድ)።

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«لَا تَجْعَلُوا قَبْرِي عِيدًا وَصَلُّوا عَلَيَّ؛ فَإِنَّ صَلَاتَكُم تَبْلُغُنِي حَيْثُ كُنْتُمْ».

«ቀብሬን የሚጎበኝ የበአል ስፍራ አታድርጉት፤ በኔ ላይ ሶለዋት አውርዱ፤ የትም ብትሆኑ ሶለዋታችሁ ትደርሰኛለችና።»266.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«البَخِيلُ مَنْ ذُكِرْتُ عِنْدَهُ فَلَمْ يُصَلِّ عَلَيَّ».

«ስስታም ማለት እርሱ ዘንድ ተወስቼ በኔ ላይ ሶላት ያላወረደ ነው።»267.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«إِنَّ لِلَّهِ مَلَائِكَةً سَيَّاحِينَ فِي الأَرْضِ يُبَلِّغُونِي مِنْ أُمَّتِي السَّلَامَ».

«ለአላህ በምድር ውስጥ የሚዞሩ መላእክቶች አሉት። የኡመቴን ሰላምታ ያደርሱኛል።»268.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«مَا مِنْ أَحَدٍ يُسَلِّمُ عَلَيَّ إِلَّا رَدَّ اللَّهُ عَلَيَّ رُوحِيَ حَتَّى أَرُدَّ عَلَيْهِ السَّلَامَ».

«አንድም በኔ ላይ ሰላምታን የሚያቀርብ የለም ለርሱ ሰላምታን እስክመልስ ድረስ አላህ ለኔ ነፍሴን የሚመልስልኝ ቢሆን እንጂ።»269

108. ሰላምታን ማብዛት

የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«لَا تَدْخُلُوا الجَنَّةَ حَتَّى تُؤْمِنُوا، وَلَا تُؤْمِنُوا حَتَّى تَحَابُّوا، أَوَلَا أَدُلُّكُم عَلَى شَيْءٍ إِذَا فَعَلْتُمُوهُ تَحَابَبْتُم، أَفْشُوا السَّلَامَ بَيْنَكُمْ».

«እስክታምኑ ድረስ ጀነት አትገቡም። እስክትዋደዱ ድረስም አታምኑም። የፈፀማችሁት ጊዜ የምትዋደዱበትን አንዳች ነገር ልጠቁማችሁን? በመካከላችሁ ሰላምታን አሰራጩ።»270

«ثَلَاثٌ مَنْ جَمَعَهُنَّ فَقَدْ جَمَعَ الإِيمَانَ: الإِنْصَافُ مِنْ نَفْسِكَ، وَبَذْلُ السَّلَامِ لِلْعَالَمِ، وَالإِنْفَاقُ مِنَ الإِقْتَارِ».

«ሶስት ነገሮችን ያሰባሰበ ሰው በእርግጥም ኢማንን አሰባስቧል፦ በራስህ ላይ ፍትሃዊ መሆን፣ ለዓለም ሰላምታን መስጠት፣ እና በችግር ጊዜም ምፅዋት መስጠት።»271.

ዐብደሏህ ኢብኑ ዑመር ረዲየሏሁ ዐንሁማ ባስተላለፈው ሐዲሥ አንድ ሰው ነብዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁን) እንዲህ ሲል ጠየቃቸው: "የትኛው እስልምና ይበልጣል?" እርሳቸውም፦

«تُطْعِمُ الطَّعَامَ، وَتَقْرأُ السَّلَامَ عَلَى مَنْ عَرَفْتَ وَمَنْ لَمْ تَعْرِفْ».

«ምግብ መመገብህ፣ ሰላምታን ባወቅከውም ባላወቅከውም ሰው ላይ ማቅረብህ ነው።»272.

 

 

109. ከሀዲ ሰላምታ በሰጠ ጊዜ እንዴት ሰላምታ ይመለስለታል?

«إذَا سَلَّمَ عَلَيْكُمْ أَهْلُ الكِتَابِ فَقُولُوا: وَعَلَيْكُمْ».

«የመጽሐፉ ሰዎች ሰላምታ ባቀረቡላችሁ ጊዜ እንዲህ በሉ: “ወዐለይኩም”።»273

110 - የአውራ ዶሮ ጩኸት እና የአህያ ጩኸት ሲሰማ የሚደረግ ዱዓእ

«إِذَا سَمِعْتُمْ صِيَاحَ الدِّيَكَةِ فَاسْأَلُوا اللَّهَ مِنْ فَضْلِهِ؛ فَإِنَّهَا رَأَتْ مَلَكًا،

«የአውራ ዶሮዎችን ጩኸት በሰማችሁ ጊዜ አላህን ከችሮታው ለምኑት፤ መልአክን አይተዋልና፣»

ለምሳሌ እንዲህ ማለት፦ (አላህ ሆይ! ከችሮታህ እንድትለግሰኝ እማፀንሀለሁ።)

وَإِذَا سَمِعْتُمْ نَهِيقَ الحِمَارِ فَتَعَوَّذُوا بِاللَّهِ مِنَ الشَّيطَانِ؛ فَإِنَّهُ رَأَى شَيْطَانًا».

«የአህያን ጩኸት በሰማችሁ ጊዜ ከሰይጣን በአላህ ተጠበቁ፤ እርሱ ሰይጣንን አይቷልና፡፡»274 እንዲህ እንደሚለው፦ (ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ)

 

111 - በምሽት የውሾች ጩኸት ሲሰማ የሚደረግ ዱዓእ፤

«إِذَا سَمِعْتُمْ نُبَاحَ الكِلَابِ وَنَهِيقَ الحَمِيرِ بِاللَّيْلِ فَتَعَوَّذُوا بِاللَّهِ مِنْهُنَّ؛ فَإِنَّهُنَّ يَرَيْنَ مَا لَا تَرَوْنَ».

«በሌሊት የውሾችን ጩኸትና የአህዮችን ድምጽ በሰማችሁ ጊዜ ከእነርሱ በአላህ ተጠበቁ፤ እናንተ የማታዩትን ያያሉና፡፡»275.

እንዲህ እንደሚለው፦ ((ከተረገመው ሰይጣን በአላህ እጠበቃለሁ))።

112 - ለሰደቡት ሰው የሚደረግ ዱዓእ

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«اللَّهُمَّ فَأَيُّمَا مُؤْمِنٍ سَبَبْتُهُ فَاجْعَلْ ذَلِكَ لَهُ قُرْبَةً إِلَيْكَ يَوْمَ القِيَامَةِ».

«አላህ ሆይ! የሰደብኩት ማንኛውም ምእመን ቢኖር ያንን የትንሳኤ ቀን ወዳንተ መቃረቢያ አድርግለት።)276

 

113. አንድ ሙስሊም ሌላውን ሙስሊም ሲያሞግስ የሚለው

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«إِذَا كَانَ أَحَدُكُم مَادِحًا صَاحِبَهُ لَا مَحَالَةَ فَلْيَقُلْ: أَحْسِبُ فُلَانًا وَاللَّهُ حَسِيبُهُ، وَلَا أُزَكِّي عَلَى اللَّهِ أَحَدًا، أَحْسِبُهُ –إِنْ كَانَ يَعْلَمُ ذَاكَ – كَذَا وَكَذَا».

«ከእናንተ አንዳችሁ ጓደኛውን ማሞገሱ ግድ ከሆነበት፡- እገሌን እንዲህ ብዬ አስባለሁ፤ አላህም ተሳሳቢው ነው፤ በአላህም ላይ ማንንም አላጠራም፤ –ያንን የሚያውቅ ከሆነ– እንዲህ እና እንዲህ ብዬ አስበዋለሁ ይበል።»277.

114. አንድ ሙስሊም ሲወደስ የሚለው

«اللَّهُمَّ لَا تُؤَاخِذْنِي بِمَا يَقُولُونَ، وَاغْفِرْ لِي مَا لَا يَعْلَمُونَ، [وَاجْعَلْنِي خَيْرًا مِمَّا يَظُّنُّونَ]».

«አላህ ሆይ! በሚሉት ነገር አትያዘኝ፤ የማያውቁትንም ወንጀሌን ማረኝ፤ [ከሚገምቱትም የተሻልኩ አድርገኝ]።»278

 

 

115. ለሐጅ ወይም ለዑምራ ኢሕራም ያደረገ ሰው እንዴት ነው ተልቢያ የሚያደርገው?

«لَبَّيْكَ اللَّهُمَّ لَبَّيْكَ، لَبَّيْكَ لَا شَرِيكَ لَكَ لَبَّيْكَ، إِنَّ الحَمْدَ، وَالنِّعْمَةَ، لَكَ وَالمُلْكَ، لَا شَرِيكَ لَكَ».

«አላህ ሆይ! ጥሪህን ተቀብያለሁ፤ አሁንም! ጥሪህን ተቀብያለሁ፤ ላንተ አጋር የለህም፤ ምስጋና ሁሉ፤ ጸጋም ሁሉ፤ ንግስናም ላንተ ብቻ ነው፤ አጋር የለህም።"»279

116. ሐጀረል አስወድ በደረሰ ጊዜ ተክቢራ ማለት

«طَافَ النَّبيُّ ﷺ بِالْبَيْتِ عَلَى بَعِيرٍ كُلَّمَا أَتَى الرُّكْنَ أَشَارَ إِلَيْهِ بِشَيْءٍ عِنْدَهُ وَكَبَّرَ».

«ነቢዩ ﷺ በግመል ላይ ሆነው ካዕባን ጠዋፍ አደረጉ፤ ወደ ሩክኑ (ጥቁሩ ድንጋይ) በመጡ ቁጥርም በእጃቸው በነበረው ነገር ወደ እርሱ እየጠቆሙ ተክቢራ ያደርጉ ነበር።»280

117 - በሩክነል የማኒ እና ሐጀረል አስወድ መካከል የሚደረግ ዱዓእ

﴿...رَبَّنَآ ءَاتِنَا فِي ٱلدُّنۡيَا حَسَنَةٗ وَفِي ٱلۡأٓخِرَةِ حَسَنَةٗ وَقِنَا عَذَابَ ٱلنَّارِ﴾

«ጌታችን ሆይ! በምድር ዓለም ደግን ነገር (ጸጋን) በመጨረሻይቱ ሀገርም ደግን ነገር (ገነትን) ስጠን:: ከእሳትም ቅጣት ጠብቀን።»281

118 - አስ'ሰፋ እና መርዋህ ላይ ተቁሞ የሚደረግ ዱዓእ

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ወደ ሰፋ በቀረቡ ጊዜ ይህን አንቀፅ አነበቡ:

«إِنَّ الصَّفَا وَالْمَرْوَةَ مِنْ شَعَآئِرِ اللَّهِ...، أَبْدَأُ بِمَا بَدَأَ اللَّهُ بِهِ»

«ሰፋና መርዋ ከአላህ /ትዕዛዝ መፈጸሚያ/ ምልክቶች ናቸው...፣ አላህ ከጀመረበት እጀምራለሁ።»

በሰፋ ጀመሩ፤ ካዕባን መመልከት እስኪችሉ ድረስ ወደ ሰፋ ወጡ። ፊታቸውንም ወደ ቂብላ አቅጣጩ፤ አላህንም በመነጠል ተክቢራ አሉ፤ እንዲህም አሉ፡-

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ، لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ، أَنْجَزَ وَعْدَهُ، وَنَصَرَ عَبْدَهُ، وَهَزَمَ الأَحْزَابَ وَحْدَهُ،

«ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ለርሱም ተጋሪ የለውም፤ ንግሥናም የርሱ ብቻ ነው፤ ምስጋናም ለርሱ ብቻ የተገባው ነው፤ እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፤ ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም፤ ብቸኛ አምላክ ነው፤ ቃሉንም ፈፀመ፤ ባርያውንም ድልን አቀዳጀ፤ ብቻውን ሆኖ ስብስቦችን አሸነፈ።»

ثُمَّ دَعَا بَيْنَ ذلكَ، قَالَ مِثْلَ هَذَا ثَلَاثَ مَرَّاتٍ»

ቀጥሎም በዚህ መካከል ዱዓ አደረጉ፤ ይህንኑ አምሳያ ሶስት ጊዜ ደጋገሙ።» ሐዲሱን (እስከ መጨረሻው)። በውስጡም፦ «በሶፋ ላይ እንዳደረጉት በመርዋ ላይም አደረጉ።» የሚል አለ።282

119 - የዐረፋህ ቀን የሚደረግ ዱዓእ

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«خَيْرُ الدُّعَاءِ دُعَاءُ يَوْمِ عَرَفَةَ، وَخَيْرُ مَا قُلْتُ أَنَا وَالنَّبيُّونَ مِنْ قَبْلِي:

«ከዱዓዎች ሁሉ በላጩ የዐረፋ ቀን ዱዓ ሲሆን፤ እኔና ከኔ በፊት የነበሩ ነቢያት ከተናገርነው ሁሉ በላጩ ደግሞ፦

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ وَلَهُ الحَمْدُ وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ».

«ከአላህ በቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።»283 «ነቢዩ ﷺ ቀስዋእን ጋለቡና አል-መሽዐረል ሐራም ዘንድ መጡ። ወደ ቂብላ አቅጣጫ በመዞርም (ዱዓ አደረጉ፣ አላሁ አክበር አሉም፣ ላ ኢላሀ ኢለላህ አሉም፣ አንድነቱንም አወሱ)። ንጋቱ በደንብ ወገግ እስኪል ድረስ ቆመው ቆዩ። ፀሐይ ከመውጣቷ በፊትም ተንቀሳቀሱ።»284 «ሶስቱም ጠጠር መወርወሪያዎች ዘንድ እያንዳንዱን ጠጠር ሲወረውር ተክቢራ ይላል። ከመጀመሪያውና ከሁለተኛው ጠጠር መወርወሪያ በኋላ ትንሽ ቀደም ይልና ወደ ቂብላ አቅጣጫ ዙሮ በመቆም እጆቹን ከፍ አድርጎ ዱዓ ያደርጋል። ጀምረተል ዓቀባ ዘንድ ግን ይወረውራል፤ እያንዳንዱን ጠጠር ሲወረውርም ተክቢራ ይላል፤ ይሄዳል እንጂ እዛ ዘንድ አይቆምም»285

120. መሽዐረል ሐራም ዘንድ (ሙዝደሊፋ ላይ የሚገኝ ተራራ ነው።) የሚባል ዚክር፤

121. ጠጠሮችን በሚወረውሩበት ወቅት ከእያንዳንዱ ጠጠር ጋር ተክቢራ ማለት።

122 - አስገራሚ እና አስደሳች ነገር በሚያጋጥም ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ

«سُبْحَانَ اللَّهِ!»

«ለአላህ ጥራት ይገባው።»286

«اللَّهُ أَكْبَرُ!»

«አላህ ታላቅ ነው።»287.

123. የሚያስደስተው ነገር ያጋጠመው ሰው የሚያደርገው

«كَانَ النَّبيُّ ﷺ إِذَا أَتَاهُ أَمْرٌ يَسُرُّهُ أَوْ يُسَرُّ بِهِ خَرَّ سَاجِدًا شُكْرًا لِلَّهِ تَبَارَكَ وَتَعَالَى».

«ነቢዩ ﷺ የሚያስደስታቸው ወይም በሱ ደስታ የሚያገኙበት ነገር ባጋጠማቸው ጊዜ፣ ለአላህ ተባረከ ወተዓላ ምስጋና ለማቅረብ ለሱጁድ ይወድቁ ነበር።»288.

124. ሰውነቱ ውስጥ ህመም የተሰማው ሰው የሚያደርገውና የሚለው

«ضَعْ يَدَكَ عَلَى الَّذِي تَألَّمَ مِنْ جَسَدِكَ وَقُلْ:

«እጅህን የሚያምህ ሰውነት ላይ አድርግና እንዲህ በል፡

بِسْمِ اللَّهِ،

በአላህ ስም

ثَلَاثًا،

ሦስት ጊዜ

وَقُلْ سَبْعَ مَرَّاتٍ:

ሰባት ጊዜም እንዲህም በል፦

أَعُوذُ بِاللَّهِ وَقُدْرَتِهِ مِنْ شَرِّ مَا أَجِدُ وَأُحَاذِرُ».

"ከማገኘውና ከምጠነቀቀው ነገር ክፋት በአላህና በችሎታው እጠበቃለሁ።"289

125. በሰው ዓይን ምክንያት አንዳች ነገር ይደርስበታል ብሎ የሰጋ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ

«إِذَا رَأَى أَحَدُكُم مِنْ أَخِيهِ، أَوْ مِنْ نَفْسِهِ، أَوْ مِنْ مَالِهِ مَا يُعْجِبُهُ [فَلْيَدْعُ لَهُ بِالْبَرَكَةِ] فَإِنَّ العَيْنَ حَقٌّ».

«ከእናንተ አንዳችሁ ከወንድሙ ወይም ከራሱ፣ ወይም ከገንዘቡ የሚወደድ ነገርን የተመለከተ (አላህ በረካ እንዲያደርግለት ዱዓእ ያድርግ) የሰው ዓይን በትክክል ያለ ነገር ነውና።»290

126. በድንጋጤ ወቅት የሚባል

«لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ!».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም!»291.

127. በእርድ ወቅት የሚባለው

«بِسْمِ اللَّهِ وَاللَّهُ أَكْبَرُ [اللَّهُمَّ مِنْكَ وَلَكَ] اللَّهُمَّ تَقَبَّلْ مِنِّي».

«ቢስሚላሂ ወልላሁ አክበር [አላህ ሆይ! ካንተ ነው፤ ላንተም ነው] አላህ ሆይ! ከኔ ተቀበለኝ።»292

128. የአመፀኛ ሰይጣናትን ተንኮል ለመመከት የሚባል

«أَعُوذُ بكَلِمَاتِ اللَّهِ التَّامَّاتِ الَّتِي لَا يُجَاوِزُهُنَّ بَرٌّ وَلَا فَاجِرٌ: مِنْ شَرِّ مَا خَلَقَ، وَبَرَأَ وَذَرَأَ، وَمِنْ شَرِّ مَا يَنْزِلُ مِنَ السَّمَاءِ، وَمِنْ شَرِّ مَا يَعْرُجُ فيهَا، وَمِنْ شَرِّ مَا ذَرَأَ فِي الأَرْضِ، وَمِنْ شَرِّ مَا يَخْرُجُ مِنْهَا، وَمِنْ شَرِّ فِتَنِ اللَّيْلِ وَالنَّهَارِ، وَمِنْ شَرِّ كُلِّ طَارِقٍ إِلَّا طَارِقًا يَطْرُقُ بِخَيْرٍ يَا رَحْمَنُ».

«አዛኝ የሆንከው ጌታ ሆይ! ደጋግም ሆነ አመፀኛ ፍጡራን ሊያልፏቸው በማይችሉት ምሉዕ በሆኑት የአላህ ቃላት፤ ከፈጠራቸው፣ ካስገገኛቸውና ከበተናቸው ነገሮች ክፋት፣ ከሰማይ ከሚወርደው ነገር ክፋት፣ ወደ እርሷ ከሚያርገው ነገር ክፋት፣ በምድር ላይ ከበተነው ነገር ክፋት፣ ከእርሷ ከሚወጣው ነገር ክፋት፣ ከሌሊትና ከቀን ፈተናዎች ክፋት፣ እንዲሁም በመልካም ነገር ከሚመጣው ሲቀር በሌሊት ድንገት ከሚመጣው ነገር ሁሉ ክፋት እጠበቃለሁ።»293

129. ምህረት መጠየቅ እና ተውበት

የአላህ መልዕክተኛ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«وَاللَّهِ إِنِّي لأَسْتَغفِرُ اللَّهَ وَأَتُوبُ إِلَيْهِ فِي اليَوْمِ أَكْثَرَ مِنْ سَبْعِينَ مَرَّةٍ».

«በአላህ እምላለሁ! እኔ በቀን ከሰባ ጊዜ በላይ አላህን ምህረት እጠይቃለሁ፤ ወደርሱም እመለሳለሁ (ተውበት አደርጋለሁ።»294

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«يَا أَيُّهَا النَّاسُ تُوبُوا إِلَى اللَّهِ فَإِنِّي أَتُوبُ فِي اليَوْمِ إِلَيْهِ مِائَةَ مَرَّةٍ».

«እናንተ ሰዎች ሆይ! ወደ አላህ ተመለሱ (ተውበት አድርጉ)፤ እኔ በቀን መቶ ጊዜ ወደርሱ እመለሳለሁ (ተውበት አደርጋለሁ።»295.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«مَنْ قَالَ:

«እንዲህ ያለ ሰው፦

أَسْتَغْفِرُ اللَّهَ العَظيمَ الَّذِي لَا إِلَهَ إِلَّا هُوَ الحَيُّ القَيُّوُمُ وَأَتُوبُ إِلَيهِ،

ታላቅ የሆነውን፣ ያ ከርሱ በስተቀር በእውነት የሚመለክ የሌለውን፣ ህያውና በራሱ የቆመ የሆነውን አላህ ምህረት እጠይቃለሁ ወደርሱም እመለሳለሁ፣

غَفَرَ اللَّهُ لَهُ وَإِنْ كَانَ فَرَّ مِنَ الزَّحْفِ».

ከጂሀድ ሸሽቶም ቢሆን እንኳ አላህ ይምረዋል።»296.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«أَقْرَبُ مَا يَكُونُ الرَّبُّ مِنَ العَبْدِ فِي جَوْفِ اللَّيْلِ الآخِرِ فَإِنِ اسْتَطَعْتَ أَنْ تَكُونَ مِمَّنْ يَذْكُرُ اللَّهَ فِي تِلْكَ السَّاعَةِ فَكُنْ».

«ጌታ ወደ ባሪያ እጅግ ቅርብ የሚሆነው በመጨረሻው የሌሊቱ አጋማሽ ነው። በዚህ ወቅት አላህን ከሚያወሱ መሆን ከቻልክ ሁን!»297.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«أَقْرَبُ مَا يَكُونُ العَبْدُ مِنْ رَبِّهِ وَهُوَ سَاجِدٌ فَأَكثِرُوا الدُّعَاءَ».

«አንድ ባሪያ ወደ ጌታው እጅግ ቅርብ የሚሆነው ሱጁድ ላይ ሳለ ነው። (ስለዚህም) ዱዓእን አብዙ!»298.

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«إِنَّهُ لَيُغَانُ عَلَى قَلْبِي وَإِنِّي لأَسْتَغْفِرُ اللَّهَ فِي اليَوْمِ مِائَةَ مَرَّةٍ».

«እነሆ በልቤ ላይ ይጋረድበታል፤ እኔም በቀን መቶ ጊዜ አላህን ምህረት እለምነዋለሁ።»299

130. የ"ተስቢሕ"፣ የ"ተሕሚድ"፣ የ"ተህሊል"ና የ"ተክቢር" ትሩፋት

ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«مَنْ قَالَ:

«እንዲህ ያለ ሰው፦

سُبْحَانَ اللَّهِ وَبِحَمْدِهِ

(ጥራት እና ምስጋና ለአላህ ተገባው።)

فِي يَوْمٍ مِائَةَ مَرَّةٍ حُطَّتْ خَطَايَاهُ وَلَوْ كَانَتْ مِثْلَ زَبَدِ البَحْر».

በቀን ውስጥ መቶ ጊዜ (የወንጀሉ ብዛት) የባህር ዓረፋ አምሳያ ቢሆን እንኳ ወንጀሉ ይታበስለታል።»300

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«مَنْ قَالَ:

«እንዲህ ያለ ሰው፦

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، لَهُ المُلْكُ، وَلَهُ الحَمْدُ، وَهُوَ عَلَى كُلِّ شَيْءٍ قَدِيرٌ

ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ ተጋሪ የለውም። ንግሥናም ምስጋናም የእርሱ ብቻ ነው። እርሱም በነገሩ ሁሉ ላይ ቻይ ነው።

عَشْرَ مِرَارٍ، كَانَ كَمَنْ أَعْتَقَ أَرْبَعَةَ أَنْفُسٍ مِنْ وَلَدِ إِسْمَاعِيلَ».

አስር ጊዜ ያለ ሰው፣ ከኢስማዒል ዘሮች የሆኑ አራት ነፍሶችን ነፃ እንዳወጣ ይቆጠርለታል።"301

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«كَلِمَتَانِ خَفِيفَتَانِ عَلَى اللِّسَانِ، ثَقِيلَتَانِ فِي المِيزَانِ، حَبِيبَتَانِ إِلَى الرَّحْمَنِ:

«ለምላስ ቀላል የሆኑ፣ ሚዛን ላይ የሚከብዱ፣ አርራህማን ዘንድ ተወዳጅ የሆኑ ሁለት ቃላቶች አሉ:

سُبْحَانَ اللَّهِ وَبِحَمْدِهِ، سُبْحانَ اللَّهِ العَظِيمِ».

(ለአላህ ጥራትና ምስጋና ተገባው፤ ታላቁ አላህ ጥራት ይገባው።)302

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«لَأَنْ أَقُولَ:

«እንዲህ ማለቴ ፦

سُبْحَانَ اللَّهِ، وَالحَمْدُ لِلَّهِ، وَلَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَاللَّهُ أَكْبَرُ،

(አላህ ጥራት ተገባው። ምስጋናም ለአላህ ነው። ከአላህም በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። አላህም ታላቅ ነው።)

أَحَبُّ إِلَيَّ مِمَّا طَلَعَتْ عَلَيْهِ الشَّمسُ».

"ፀሐይ የወጣችበት ክልል ሁሉ (ከሚሰጠኝ) የበለጠ ወደእኔ እጅግ ተወዳጅ ነው።"303

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«أَيَعْجِزُ أَحَدُكُم أَنْ يَكْسِبَ كُلَّ يَوْمٍ أَلْفَ حَسَنَةٍ»

«አንዳችሁ በየቀኑ አንድ ሺህ ምንዳ መሸመት ይሳነዋልን?» ከተቀመጡት ሰዎች መካከል አንድ ጠያቂ "እንዴት ነው አንዳችን አንድ ሺህ ምንዳ የሚሸምተው?" በማለት ጠየቃቸው። እርሳቸውም:

«يُسَبِّحُ مِائَةَ تَسْبِيحَةٍ، فَيُكتَبُ لَهُ أَلْفُ حَسَنَةٍ أَوْ يُحَطُّ عَنْهُ أَلْفُ خَطِيئَةٍ».

«መቶ ጊዜ ተስቢሕ ካለ ለርሱ አንድ ሺህ ምንዳ ይፃፍለታል ወይም ከርሱ ላይ አንድ ሺህ ወንጀል ይሰረዝለታል።»304

«مَنْ قَالَ:

«እንዲህ ያለ ሰው፦

سُبْحَانَ اللَّهِ العَظِيمِ وَبِحَمْدِهِ

(ለታላቁ አላህ ጥራትና ምስጋና ተገባው።)

غُرِسَتْ لَهُ نَخْلَةٌ فِي الجَنَّةِ».

ጀነት ውስጥ ለርሱ የተምር ዛፍ ይተከልለታል።»305

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፡

«يَا عَبْدَ اللَّهِ بْنَ قَيْسٍ أَلَا أَدُلُّكَ عَلَى كَنْزٍ مِنْ كُنُوزِ الجَنَّةِ؟»

«ዐብዱላህ ቢን ቀይስ ሆይ! ከጀነት ድልቦች መካከል ወደ አንዱ አልጠቁምህምን?» እኔም፦ እንዴታ የአላህ መልዕክተኛ ሆይ አልኳቸው። እርሳቸውም እንዲህ አሉ፦

«قُلْ:

«በል፦

لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ».

በአላህ ካልሆነ በስተቀር ምንም ኃይልና ብልሀት የለም።»306

ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦

«أَحَبُّ الكَلَامِ إِلَى اللَّهِ أَرْبَعٌ:

«አላህ ዘንድ ተወዳጅ የሆኑ ንግግሮች አራት ናቸው:

سُبْحَانَ اللَّهِ، وَالحَمْدُ لِلَّهِ، وَلَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَاللَّهُ أَكْبَرُ،

(አላህ ጥራት ተገባው። ምስጋናም ለአላህ ነው። ከአላህም በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። አላህም ታላቅ ነው።)

لَا يَضُرُّكَ بِأَيِّهِنَّ بَدَأتَ».

«በየትኛውም ብትጀምር አይጎዳህም»307

አንድ የገጠር ሰው ወደ የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በመምጣት እንዲህ አለ: 'የምለውን ቃላት አስተምሩኝ?' እርሳቸውም:

«قُلْ:

«በል፦

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ وَحْدَهُ لَا شَرِيكَ لَهُ، اللَّهُ أَكْبَرُ كَبِيرًا، وَالحَمْدُ لِلَّهِ كَثِيرًا، سُبْحَانَ اللَّهِ رَبِّ العَالَمِينَ، لَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّهِ العَزِيزِ الحَكِيمِ».

(ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው አምላክ የለም፤ እርሱ አንድ ነው፤ አጋር የለውም። አላህ እጅግ ታላቅ ነው። ብዙ ምስጋናም ለአላህ ነው። የዓለማት ጌታ የሆነው አላህ ጥራት ይገባው። አሸናፊና ጥበበኛ በሆነው በአላህ ቢሆን እንጅ ብልሃትም ሆነ ኃይል የለም።)

(እርሱም) አለ፡ «እነዚህ ለጌታዬ ናቸው፤ ታዲያ ለኔስ ምን አለኝ?» አለ፡

«قُلْ:

«እንዲህ በል፦

اللَّهُمَّ اغْفِرْ لِي، وَارْحَمْنِي، وَاهْدِنِي، وَارْزُقْنِي».

‹‹አላህ ሆይ! ኃጢዓቴን ማረኝ፤ እዘንልኝም፤ ምራኝም፤ ሲሳይም ለግሰኝ፡፡››308

አንድ ሰው እስልምናን በተቀበለ ጊዜ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሶላትን ያስተምሩትና ከዚያም በነዚህ ቃላቶች ዱዓ እንዲያደርግ ያዙት ነበር፡

«اللَّهُمَّ اغْفِرِ لِي، وَارْحَمْنِي، وَاهْدِنِي، وَعَافِنِي وَارْزُقْنِي».

"አላህ ሆይ! ማረኝ፣ እዘንልኝ፣ ምራኝ፣ ጤናን ስጠኝ፣ ሲሳይንም ለግሰኝ!"309

«إِنَّ أَفْضَلَ الدُّعَاءِ

"በላጩ ዱዓእ

الحَمْدُ لِلَّهِ،

ምስጋና ለአላህ ይሁን፣

وَأَفْضَلَ الذِّكْرِ

እና በላጩ ዚክር

لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ».

«ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም»310

«البَاقِيَاتُ الصَّالِحَاتُ:

«ቀሪ የሆኑ መልካም ሥራዎች:

سُبْحَانَ اللَّهِ، وَالحَمْدُ لِلَّهِ، وَلَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ، وَاللَّهُ أَكْبَرُ، وَلَا حَوْلَ وَلَا قُوَّةَ إِلَّا بِاللَّه».

(አላህ ጥራት ይገባው። ምስጋናም ለአላህ ነው። ከአላህም በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ የለም። አላህም ታላቅ ነው። በአላህ ቢሆን እንጅ ብልሃትም ሆነ ሃይል የለም።)311.

131. ነቢዩ ﷺ ተስቢሕ የሚያደርጉት እንዴት ነበር?

ከዐብደላህ ቢን ዐምር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ:

«رَأَيْتُ النَّبيَّ ﷺ يَعْقِدُ التَّسْبِيحَ» وفي زيادةٍ: «بِيَمِينِهِ».

«ነቢዩን (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ተስቢሕን ሲቆጥሩ አየኋቸው።» በተጨማሪ ዘገባም ላይ፡ «በቀኝ እጃቸው» ይላል312

132. ከአጠቃላይ የመልካም ተግባራት አይነቶችና ስነ-ስርዓት

ነብዩ የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን እንዲህ ብለዋል፦

«إِذَا كَانَ جُنْحُ اللَّيْلِ – أَوْ أَمْسَيْتُم – فَكُفُّوا صِبْيَانَـكُم، فَإِنَّ الشَّيَاطِينَ تَنْتَشِرُ حِينَئِذٍ، فَإِذَا ذَهَبَ سَاعَةٌ مِنَ اللَّيلِ فَخَلُّوهُمْ، وَأَغْلِقُوا الأَبْوَابَ وَاذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ؛ فَإِنَّ الشَّيطَانَ لَا يَفْتَحُ بَابًا مُغلَقًا، وَأَوْكُوا قِرَبَكُمْ، وَاذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ، وَخَمِّرُوا آنِيَتَكُم، وَاذْكُرُوا اسْمَ اللَّهِ، وَلَوْ أَنْ تَعْرُضُوا عَلَيْهَا شَيْئًا، وَأَطْفِئُوا مَصَابِيحَكُمْ».

«የሌሊት ጨለማ በገባ ጊዜ - ወይም ባመሻችሁ ጊዜ - ህፃናቶቻችሁን ሰብስቡ፤ በዚያን ሰዓት ሰይጣናት ይሰራጫሉና። ከሌሊቱም የተወሰነ ጊዜ ካለፈ በኋላ ልቀቋቸው። በሮችንም ዝጉ፤ የአላህንም ስም አውሱ፤ ሰይጣን የተዘጋን በር አይከፍትምና። የውሃ አቅማዳዎቻችሁንም እሰሩ፤ የአላህንም ስም አውሱ። በላዩ ላይ አንዳች ነገር በአግድም በማድረግም ቢሆን ዕቃዎቻችሁንም ሸፍኑ፤ የአላህንም ስም አውሱ፤ መብራቶቻችሁንም አጥፉ።»313

የአላህ ሰላት፣ ሰላምና በረከት በነቢያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ሁሉ ላይ ይስፈን።

***

ማውጫ

 

መግቢያ 2

የዚክር ትሩፋት 4

1. ከእንቅልፍ ሲነቁ የሚደረጉ ዚክሮች (ውዳሴዎች) 10

2. ልብስ ሲለበስ የሚባል ዱዓእ 14

3. አዲስ ልብስ ሲለበስ የሚባል ዱዓእ 14

4. አዲስ ልብስ ለለበሰ ሰው የሚደረግ ዱዓእ 15

5. ልብስ ሲያወልቁ የሚባል ዱዓእ 15

6. ወደ መፀዳጃ ቤት ሲገባ የሚባል ዱዓእ 16

7 - ከመጸዳጃ ቤት ሲወጣ የሚባለው ዱዓእ 16

8. ከዉዱእ በፊት የሚባል ዚክር 16

9. ዉዱእ ካጠናቀቁ በኋላ የሚባል ዚክር 16

10. ከቤት ሲወጣ የሚባለው ዚክር 17

11. ወደ ቤት ሲገቡ የሚባለው ዚክር 18

12. ወደ መስጂድ ሲኬድ የሚባለው ዱዓእ 19

13. መስጂድ ሲገባ የሚባለው ዱዓእ 20

14. ከመስጂድ ሲወጣ የሚባለው ዱዓእ 21

15. የአዛን አዝካሮች 22

16. የመክፈቻ ዱዓእ 24

17 - የሩኩዕ ዱዓእ 29

18. ከሩኩዕ ቀና ሲባል የሚደረግ ዱዓእ 30

19. የሱጁድ ዱዓእ 31

20. በሁለቱ ሱጁዶች መካከል በምንቀመጥ ወቅት የሚደረግ ዱዓእ፤ 33

21. የቲላዋህ ሱጁድ ዱዓእ 33

22. ተሸሁድ 34

23. ከተሸሁድ በኋላ በነቢዩ ላይ ሶላት ማውረድ 35

24. ከመጨረሻው ተሸሁድ በኋላ ከማሰላመት በፊት ዱዓእ ማድረግ። 36

25. ሶላትን ከማጠናቀቅ በኋላ የሚባሉ አዝካሮች 41

26 - የኢስቲኻራ ሶላት ዱዓእ 47

27. የንጋትና ምሽት ዚክሮች 49

28. የመኝታ አዝካር (ውዳሴዎች) 66

29 - በሌሊት በተገላበጡ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ፤ 75

30. በእንቅልፍ ውስጥ የደነገጠና በብቸኝነት የተቸገረ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ 76

31. ህልም ያየ ሰው ምን ማድረግ እንዳለበት 76

32 - የዊትር ቁኑት ዱዓእ 77

33. ከዊትር ሶላት ካሰላመቱ በኋላ የሚባል ዚክር 79

34 - በጭንቀትና በሀዘን ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ 79

35 - በችግር ወቅት የሚደረግ ዱዓእ 81

36 - ጠላትንና ባለስልጣንን ሲገናኙ የሚደረግ ዱዓእ 82

37 - የመሪን በደል የፈራ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ 83

38 - በጠላት ላይ የሚደረግ ዱዓእ 84

39. ሕዝብን የፈራ ሰው የሚለው 84

40 - በእምነት ውስጥ ወስዋስ የደረሰበት ሰው የሚያደርገው ዱዓእ 85

41 - የዕዳ መክፈያ ዱዓእ 86

42 - በሶላትና በቂራአት ውስጥ ወስዋስ ሲያጋጥም የሚደረግ ዱዓእ 86

43 - ጉዳይ የከበደበት ሰው የሚያደርገው ዱዓእ፤ 87

44. ወንጀል የሠራ ሰው የሚለውና የሚያደርገው 87

45. ሰይጣንንና ጉትጎታውን ማባረሪያ ዱዓ 88

46 - የማይወደው ነገር ሲያጋጥመው ወይም ከአቅሙ በላይ ሲሆንበት የሚያደርገው ዱዓእ 89

47 - ልጅ ለተወለደለት ሰው የሚባል የእንኳን ደስ አለህ ቃልና ምላሹ 89

48 - ለልጆች ጥበቃ የሚደረግበት ዱዓእ 90

49 - በሽተኛን በሚጠይቁ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ፤ 91

50. ህመምተኛን የመጠየቅ ትሩፋት 91

51 - በህይወቱ ተስፋ የቆረጠ በሽተኛ የሚያደርገው ዱዓእ 92

52. ሞት አፋፍ ላይ ያለን ሰው "ላ ኢላሃ ኢለሏህን" ተልቂን ማስደረግ (ማስባል) 94

53 - መከራ የደረሰበት ሰው የሚያደርገው ዱዓእ 94

54. የሟችን ዓይን ሲከድኑ የሚደረግ ዱዓእ 94

55. በሟች ላይ በሚሰገድ ሰላት ውስጥ ለሟቹ የሚደረግ ዱዓእ 95

56 - ለሟች ህፃን በጀናዛ ሶላት ላይ የሚደረግ ዱዓእ 97

57. የሟችን ቤተሰብ ለማፅናናት የሚደረግ ዱዓእ 99

58 - ሟችን ቀብር ውስጥ ሲያስገቡ የሚደረግ ዱዓእ 99

59. ሟችን ከቀበሩ በኋላ የሚደረግ ዱዓእ 100

60. ቀብርን ሲዘይሩ የሚደረግ ዱዓእ፤ 100

61. በንፋስ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ፤ 101

62. ነጎድጓድ ሲሰማ የሚደረግ ዱዓእ፤ 101

63 - ዝናብን ለመፈለግ ከሚደረጉ ዱዓዎች 102

64. ዝናብ ሲታይ የሚደረግ ዱዓእ 102

65. ዝናብ ከወረደ በኋላ የሚደረግ ዚክር 103

66 - ዝናብ እንዲያባራ ከሚደረጉ ዱዓዎች 103

67. ጨረቃ ሲታይ የሚደረግ ዱዓእ 103

68. ፆመኛ በሚያፈጥር ጊዜ የሚያደርገው ዱዓእ 104

69. ምግብ ከመብላት በፊት የሚደረግ ዱዓእ 104

70. ምግብ በልቶ ሲጨረስ የሚደረግ ዱዓእ 105

71. እንግዳው ለጋባዡ የሚያደርግለት ዱዓእ 106

72 - ምግብን ወይም መጠጥን ለመጠየቅ በዱዓእ በተዘዋዋሪ ማመልከት 106

73 - በሰው ቤት በሚያፈጥር ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ 106

74. ፆመኛ ምግብ ቀርቦለት ባያፈጥር የሚያደርገው ዱዓእ 107

75. ፆመኛ ሰው አንድ ሰው ከተሰዳደበው የሚለው 107

76 - የመጀመሪያ ፍሬ በሚታይ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ 107

77 - በሚያስነጥስ ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ 108

78. ካፊር አስነጥሶ አላህን ባመሰገነ ጊዜ የሚባለው 109

79. አዲስ ላገባ ሰው ዱዓእ ማድረግ 109

80 - አዲስ ያገባና እንስሳ የገዛ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ 109

81. ከሚስት ጋር ግንኙነት ከማድረግ በፊት የሚደረግ ዱዓእ፤ 110

82. በቁጣ ጊዜ የሚባል ዱዓእ 110

83 - ፊትና ላይ የወደቀን ሰው ያየ የሚያደርገው ዱዓእ 111

84. በስብሰባ (መጅሊስ) ላይ የሚባል 111

85. የመቀማመጥ ከፋራ 111

86 - "ገፈረሏሁ ለከ" ላለ ሰው የሚደረግ ዱዓእ 112

87 - ውለታ ለዋለልህ ሰው የሚደረግ ዱዓእ 112

88. አላህ ከደጃል የሚጠብቅበት መጠበቂያ 113

89 - «እኔ ለአላህ ብዬ እወድሃለሁ» ላለ ሰው የሚደረግ ዱዓእ 113

90. ገንዘቡን ላቀረበልህ ሰው የሚደረግ ዱዓእ 113

91 - ብድር ላበደረ ሰው ብድሩን ሲመልሱ የሚደረግ ዱዓእ 114

92 - ሺርክን በመፍራት የሚደረግ ዱዓእ 114

93. "አላህ ይባርክህ" ላለ ሰው የሚደረግ ዱዓ 114

94 - መጥፎ ገድን (ጢየራን) ሲጠሉ የሚደረግ ዱዓእ 115

95 - መጓጓዣ ላይ ሲወጣ የሚባለው ዱዓእ 115

96. የጉዞ ዱዓ 116

97 - መንደር ወይም ከተማ ሲገባ የሚባል ዱዓእ 118

98. ወደ ገበያ ሲገባ የሚባለው ዱዓእ 118

99 - መጓጓዣ ሲዳከም የሚባለው ዱዓእ 119

100. መንገደኛ የሆነ ሰው ነዋሪ ለሆነ የሚያደርግለት ዱዓእ 119

101. ነዋሪ የሆነ ለመንገደኛው የሚያደርግለት ዱዓእ 119

102 - በጉዞ ወቅት የሚደረግ ተክቢርና ተስቢሕ 120

103 - ጉዞ የወጣ ሰው የሰሐር ጊዜ ሲገባ የሚያደርገው ዱዓእ 120

104 - ከጉዞም ይሁን ከሌላ ቦታ ወደ አንድ ስፍራ በሚያርፍ ወቅት የሚደረግ ዱዓእ 121

105. ከጉዞ ሲመለስ የሚደረግ ዚክር 121

106. የሚያስደስተው ወይም የሚያስከፋው ነገር ያጋጠመው ሰው የሚለው 122

107. በነቢዩ ላይ ሶላት የማውረድ ትሩፋት 122

108. ሰላምታን ማብዛት 124

109. ከሀዲ ሰላምታ በሰጠ ጊዜ እንዴት ሰላምታ ይመለስለታል? 126

110 - የአውራ ዶሮ ጩኸት እና የአህያ ጩኸት ሲሰማ የሚደረግ ዱዓእ 126

111 - በምሽት የውሾች ጩኸት ሲሰማ የሚደረግ ዱዓእ፤ 127

112 - ለሰደቡት ሰው የሚደረግ ዱዓእ 127

113. አንድ ሙስሊም ሌላውን ሙስሊም ሲያሞግስ የሚለው 128

114. አንድ ሙስሊም ሲወደስ የሚለው 128

115. ለሐጅ ወይም ለዑምራ ኢሕራም ያደረገ ሰው እንዴት ነው ተልቢያ የሚያደርገው? 129

116. ሐጀረል አስወድ በደረሰ ጊዜ ተክቢራ ማለት 129

117 - በሩክነል የማኒ እና ሐጀረል አስወድ መካከል የሚደረግ ዱዓእ 129

118 - አስ'ሰፋ እና መርዋህ ላይ ተቁሞ የሚደረግ ዱዓእ 130

119 - የዐረፋህ ቀን የሚደረግ ዱዓእ 131

120. መሽዐረል ሐራም ዘንድ (ሙዝደሊፋ ላይ የሚገኝ ተራራ ነው።) የሚባል ዚክር፤ 132

121. ጠጠሮችን በሚወረውሩበት ወቅት ከእያንዳንዱ ጠጠር ጋር ተክቢራ ማለት። 132

122 - አስገራሚ እና አስደሳች ነገር በሚያጋጥም ጊዜ የሚደረግ ዱዓእ 132

123. የሚያስደስተው ነገር ያጋጠመው ሰው የሚያደርገው 133

124. ሰውነቱ ውስጥ ህመም የተሰማው ሰው የሚያደርገውና የሚለው 133

125. በሰው ዓይን ምክንያት አንዳች ነገር ይደርስበታል ብሎ የሰጋ ሰው የሚያደርገው ዱዓእ 134

126. በድንጋጤ ወቅት የሚባል 135

127. በእርድ ወቅት የሚባለው 135

128. የአመፀኛ ሰይጣናትን ተንኮል ለመመከት የሚባል 135

129. ምህረት መጠየቅ እና ተውበት 136

130. የ"ተስቢሕ"፣ የ"ተሕሚድ"፣ የ"ተህሊል"ና የ"ተክቢር" ትሩፋት 139

131. ነቢዩ ተስቢሕ የሚያደርጉት እንዴት ነበር? 146

132. ከአጠቃላይ የመልካም ተግባራት አይነቶችና ስነ-ስርዓት 146

 

***

 

am24v5.0 - 08/09/2026


ሱረቱል በቀራህ፡ 152

ሱረቱል አሕዛብ፡ 41

ሱረቱል አሕዛብ፡ 35.

ሱረቱ አልአዕራፍ፡ 205

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/208) በቁጥር (6407)፤ ሙስሊም (1/539) በቁጥር (779) ላይ በሚከተለው ቃል ዘግበውታል፦ ""በውስጡ አላህ የሚወሳበት ቤትና አላህ የማይወሳበት ቤት ምሳሌ እንደ ህያውና እንደሞተ ሰው ምሳሌ ነው።""

ቲርሚዚይ 5/459 የሐዲስ ቁጥር 3377 ፣ ኢብኑ ማጀህ 2/124 የሐዲስ ቁጥር 3790 ዘግበውታል። ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ 2/316 እና ሶሒሕ አትቲርሚዚ 3/139 ይመልከቱ።

ቡኻሪይ (8/171) በቁጥር (7405)፤ ሙስሊም (4/2061) በቁጥር (2675)፤ ቃሉ የቡኻሪይ ዘገባ ላይ ያለው ነው።

ቲርሚዚይ በ5/458 የሐዲሥ ቁ, 3375 ፣ ኢብኑ ማጀህ በ2/1246 የሐዲሥ ቁ, 3793 ዘግበውታል። አልባኒይ በሶሒሕ አትቲርሚዚይ 3/139 እና በሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ መጽሐፋቸው 2/317 ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ቲርሚዚ በ5/75 የሐዲሥ ቁ, 2910 ዘግበውታል። አልባኒም በ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" 3/9 እና በ "ሶሒሕ አልጃሚዑ አስሶጚር" 5/340 ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ሙስሊም (1/553) በቁጥር (803) ዘግበውታል።

አቡ ዳውድ (4/264) በቁጥር (4856) እና ሌሎችም ዘግበውታል፣ ሶሒሕ አል-ጃሚዕ (5/342)ን ይመልከቱ።

ቲርሚዚይ በ(5/461) በቁጥር (3380)፣ ሶሒሕ አትቲርሚዚይ (3/140) ይመልከቱ።

አቡዳውድ (4/264) በቁጥር (4855)፣ አሕመድ (2/389) በቁጥር (10680) ዘግበውታል። ሶሒሕ አልጃሚዕ (5/176) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/113) በቁጥር (6314) እና ሙስሊም (4/2083) በቁጥር (2711) ዘግበውታል።

«ይህንን ያለ አላህ ይምረዋል፤ ዱዓ ካደረገም ይመለስለታል፤ ተነስቶ ዉዱእ አድርጎ ከዚያም ከሰገደ ሶላቱ ተቀባይነትን ያገኛል።» ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (3/39) በቁጥር (1154) እና ሌሎችም የዘገቡት ሲሆን፣ ቃላቱ የኢብኑ ማጀህ ናቸው፤ ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/335) ይመልከቱ።

ቲርሚዚይ በ(5/473) በቁጥር (3401) ዘግበውታል፣ እንዲሁም "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/144) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (8/337) በቁጥር (4569) ፣ ሙስሊም (1/530) በቁጥር (256) ዘግበውታል።

ከነሳኢ በስተቀር አህሉስ-ሱነን፡ አቡ ዳውድ በቁጥር (4023)፣ ቲርሚዚይም በቁጥር (3458)፣ ኢብኑ ማጀህም በቁጥር (3285) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በ "ኢርዋኡል ጘሊል" (47/7) ውስጥ ሐሰን ብለውታል።

አቡ ዳውድ በቁጥር (4020)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (1767)፣ በገዊ (12/40) ዘግበውታል። "ሙኽተሶር ሸማኢል አትቲርሚዚ" ለአልባኒ (ገጽ 47) ይመልከቱ።

አቡ ዳውድ (4/41) በቁጥር (4020) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አቢ ዳውድ" (2/760) ይመልከቱ።

ኢብኑ ማጀህ (2/1178) በቁጥር (3558)፣ በገዊ (41/12) ዘግበውታል። ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (275/2) ይመልከቱ።

ቲርሚዚይ (2/505) በቁጥር (606) እና ሌሎችም ዘግበውታል፤ "ኢርዋኡል ገሊል" በቁጥር (50) እና "ሶሒሑል ጃሚዕ" (203/ 3) ይመልከቱ።

ቡኻሪይ (1/ 45) በቁጥር (142) እና ሙስሊም (1/ 283) በቁጥር (375) ዘግበውታል። በመጀመሪያው ላይ ያለውን «(ቢስሚልላህ) በአላህ ስም» የሚለውን ጭማሪ ሰዒድ ኢብኑ መንሱር ዘግበውታል። ፈትሑል ባሪ (1/ 244) ይመልከቱ።

የሱነን አዘጋጆች ከነሳኢ በስተቀር የዘገቡት ሲሆን፣ ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር (79)፣ አቡዳውድ በቁጥር (30)፣ ቲርሚዚይ በቁጥር (7)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (300) ዘግበውታል። አልባኒም በ "ሶሒሕ ሱነን አቢ ዳውድ" (1/19) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

አቡዳውድ በቁጥር (101)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (397)፣ አሕመድ በቁጥር (9418) ዘግበውታል። ኢርዋኡል ገሊል (1/122) ይመልከቱ።

ሙስሊም (1/209) በቁጥር (234) ዘግበውታል።

አትቲርሚዚ (1/78) በቁጥር (55)፣ እንዲሁም በሶሒሕ አትቲርሚዚ (1/18) ላይ ይመልከቱ።

ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ (ገፅ 173)፣ እንዲሁም ኢርዋኡል ገሊል (1/135) እና (3/94) ይመልከቱ።

አቡ ዳውድ (4/325) በቁጥር (5095)፣ ቲርሚዚ (5/490) በቁጥር (3426) የዘገቡት ሲሆን፣ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/151) ይመልከቱ።

አህሉስ-ሱነን፡ አቡዳውድ በቁጥር (5094)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3427)፣ ነሳኢ በቁጥር (5501)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3884) የዘገቡት ሲሆን፤ በ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/152) እና በ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/336) ላይ ይመልከቱ።

አቡዳውድ (4/325) በቁጥር (5096) ዘግበውታል፤ ታላቁ ሊቅ ኢብኑ ባዝም በ "ቱሕፈቱል አኽያር" (ገጽ 28) ሰነዱን ሐሰን ብለውታል። በሶሒሕ ውስጥም፡- "አንድ ሰው ወደ ቤቱ ሲገባ በሚገባበት ወቅትም በሚበላበት ወቅትም አላህን ካወሳ ሰይጣን (ለባልደረቦቹ) 'ማደሪያም እራትም የላችሁም።' ይላል።" ሙስሊም በቁጥር (2018) ዘግበውታል።

እነዚህን ሁሉ ቃላቶች ቡኻሪ (11/116) በቁጥር (3166) እና ሙስሊም (1/526) በቁጥር (529)፣ (530) እና (763) ላይ ይመልከቱ።

ቲርሚዚይ (5/483) በቁጥር (3419)።

ቡኻሪይ በአደቡል ሙፍረድ በቁጥር (695) (ገጽ 258) ዘግበውታል። አልባኒይ በሶሒሕ አልአደቡል ሙፍረድ በቁጥር (536) ኢስናዱን ሶሒሕ ብለውታል።

ኢብኑ ሐጀር በ "ፈትሑል ባሪ" ላይ የጠቀሱት ሲሆን፣ "አድዱዓእ" በሚለው መጽሐፍ ለኢብኑ አቢ ዓሲም አስጠግተውታል። አልፈትሕ (11/118) ይመልከቱ። እርሳቸውም፦ "በተለያዩ ዘገባዎቹ ሀያ አምስት ነገሮች ተሰብስበዋል።" ብለዋል።

አነስ ኢብኑ ማሊክ ‐አሏህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና‐ እንዲህ በማለታቸው ነው፦ "መስጂድ ስትገባ ቀኝ እግርህን ማስቀደም፣ ስትወጣም ግራ እግርህን ማስቀደም ከሱና ነው።" አል-ሓኪም (1/218) ዘግበውታል፤ በሙስሊም መስፈርት መሰረት ሶሒሕ ብለውታል። አዝ-ዘሀቢይም ተስማምተውበታል። አል-በይሀቂይም (2/442) ዘግበውታል። አል-አልባኒም ሲልሲለቱል አሓዲሲስ ሶሒሓ ላይ (5/624) በቁጥር (2478) ሐሰን ብለውታል።

አቡዳውድ በቁጥር (466) ዘግበውታል፣ ሶሒሕ አልጃሚዕ በቁጥር (4591) ይመልከቱ።

ኢብኑ አስ-ሱኒ በቁጥር (88) ዘግበውታል፣ አልባኒም በአስ-ሠመር አል-ሙስተጣብ (ገጽ 607) ሀሰን ብለውታል።

አቡ ዳውድ (1/126) በቁጥር (465) ዘግበውታል፤ ሶሒሕ አልጃሚዕ (1/528) ይመልከቱ።

ሙስሊም (1/494) በቁጥር (713) ዘግበውታል። እንዲሁም በ"ሱነን ኢብኑ ማጀህ" ውስጥ ከፋጢማ (ረዺየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - በተላለፈው ሐዲሥ፡- «አልላሁምመ-ግፊርሊ ዙኑቢ፣ ወፍተሕ ሊ አብዋበ ረሕመቲክ» ትርጉሙም፦ ‹‹አላህ ሆይ! ወንጀሎቼን ማረኝ፤ የእዝነት ደጆችህንም ክፈትልኝ።›› ተብሎ ተዘግቧል። አልባኒ በሚያጠናክሩት ዘገባዎች ሶሒሕ ብለውታል። "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/128) በቁጥር (129) ይመልከቱ።

ሐኪም (1/218) እና በይሀቂ (2/442) ዘግበውታል። አልባኒም በ "ሲልሲለቱል አሓዲሢ አስ-ሶሒሐህ" (5/624) ቁጥር (2478) ላይ ሐሰን ብለውታል። የግርጌ ማስታወሻውም ከዚህ በፊት አልፏል።

መስጂድ በሚገቡ ወቅት በሚደረገው ዱዓ ላይ ያለፈውን ሐዲሥ የዘገባ ምንጭ ማውጫ ቁጥር (20) ይመልከቱ፤ እንዲሁም የኢብኑ ማጃህን ጭማሪ፦ «አልላሁምመ-ዕሲምኒ ሚነሽ-ሸይጧኒ-ር-ረጂም» ትርጉሙም፦ "አላህ ሆይ! ከተረገመው ሰይጣን ጠብቀኝ።" ሶሒሕ ኢብኑ ማጃህ (1/129) ይመልከቱ።

ቡኻሪ (1/152) በቁጥር (611) እና (613)፣ ሙስሊም (1/288) በቁጥር (383) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/290) በቁጥር (386) ዘግበውታል።

ኢብኑ ኹዘይማህ (1/220)

ሙስሊም (1/288) በቁጥር (384) ዘግበውታል።

ቡኻሪይ (1/152) በቁጥር (614) የዘገቡት ሲሆን፣ በቅንፉ ውስጥ ያለው ደግሞ በበይሀቂይ (1/410) የተዘገበ ነው፤ ታላቁ ዓሊም ዐብዱልዐዚዝ ቢን ባዝ (ረሒመሁላህ) - አላህ ይዘንላቸውና - በቱሕፈቱል አኽያር (ገጽ 38) ላይ ኢስናዱን (የዘገባ ሰንሰለቱን) ሐሰን አድርገውታል።

ቲርሚዚ በቁጥር (3594) እና (3595)፣ አቡ ዳውድ በቁጥር (525) እና አሕመድ በቁጥር (12200) ዘግበውታል፤ "ኢርዋኡል ጘሊል" (1/262) ይመልከቱ።

ቡኻሪ (1/181) በቁጥር (744) እና ሙስሊም (1/419) በቁጥር (598) ዘግበውታል።

ሙስሊም በቁጥር (399) እና አራቱ የሱነን አዘጋጆች፡ አቡዳውድ በቁጥር (775)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (243)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (806)፣ ነሳኢ በቁጥር (899) የዘገቡት ሲሆን፤ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (1/77) እና "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/135) ይመልከቱ ።

ሙስሊም (1/534) በቁጥር (771) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/534) በቁጥር (770) ዘግበውታል።

አቡዳውድ በ(1/203) ቁጥር (764)፣ ኢብኑ ማጀህ በ(1/265) ቁጥር (807)፣ አሕመድ በ(4/85) ቁጥር (16739) ዘግበውታል። ሹዓይብ አልአርናኡጥ ሙስነድን ተሕቂቅ ባደረጉበት ውስጥ "ሐሰን ሊጘይሪሂ ነው" ብለዋል። ዐብዱልቃዲር አልአርናኡጥ የኢብኑ ተይሚያህን "አልከሊሙ ጠዪብ"ን ተኽሪጅ ባደረጉበት ውስጥ ቁጥር (78) ላይ "በማጠናከሪያዎቹ ሶሒሕ ሐዲስ ነው" ብለዋል። አልባኒም በ "ሶሒሕ አልከሊሙ ጠዪብ" መጽሐፋቸው ቁጥር (62) ላይ ጠቅሰውታል። ሙስሊምም ከኢብኑ ዑመር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) በተመሳሳይ መልኩ ዘግበውታል፤ በውስጡም ታሪክ አለው (1/420) ቁጥር (601)።

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሌሊት ተሀጁድ ለመስገድ የተነሱ ጊዜ ይሉት ነበር።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (3/3)፣ (11/116) እና (13/371) በቁጥር (423)፣ (465)፣ (1120)፣ (6317)፣ (7385)፣ (7442) እና (7499) ሲዘግቡት ፤ ሙስሊም በአጭሩ በተመሳሳይ መልኩ (1/532) በቁጥር (769) ዘግበውታል።

" አህለስ-ሱነን እና አሕመድ ዘግበውታል፦ አቡ ዳውድ በቁጥር (870)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (262)፣ ነሳኢ በቁጥር (1007)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (897) እና አሕመድ በቁጥር (3514)። በ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (1/83) ይመልከቱ።"

ቡኻሪይ (1/ 99) በቁጥር (794) ፣ ሙስሊም (1/ 350) በቁጥር (484) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/353) በቁጥር (487) እና አቡ ዳውድ (1/230) በቁጥር (872) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/ 534) በቁጥር (771)፣ ከኢብኑ ማጀህ ውጭ አራቱ፡ አቡዳውድ በቁጥር (760) እና (761)፣ ቲርሚዚይ በቁጥር (3421)፣ ነሳኢ በቁጥር (1049) የዘገቡት ሲሆን በቅንፍ ውስጥ ያለው ቃል የኢብኑ ኹዘይማህ በቁጥር (607) እና የኢብኑ ሒባን በቁጥር (1901) ዘገባ ነው።

አቡዳውድ (1/230) በቁጥር (873)፣ ነሳኢ በቁጥር (1131)፣ አሕመድ በቁጥር (23980) የዘገቡት ሲሆን ሰነዱ ሐሰን ነው።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (2/282) በቁጥር (796) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (2/284) በቁጥር (796) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/ 346) በቁጥር (477) ዘግበውታል።

አህሉስ-ሱነን እና አሕመድ የዘገቡት ሲሆን፦ አቡ ዳውድ በቁጥር (870) ላይ፣ ቲርሚዚይም በቁጥር (262) ላይ፣ ነሳኢይም በቁጥር (1007) ላይ፣ ኢብኑ ማጀህም በቁጥር (897) ላይ፣ እንዲሁም አሕመድ በቁጥር (3514) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አት-ቲርሚዚ" (1/83) ይመልከቱ።

ቡኻሪ በቁጥር (794) እና ሙስሊም በቁጥር (484) ዘግበውታል፤ ከዚህ ቀደም በቁጥር (34) ተጠቅሷል።

ሙስሊም (1/533) በቁጥር (487) እና አቡ ዳውድ በቁጥር (872) ዘግበውታል። ከዚህ በፊት በቁጥር (35) አልፏል።

ሙስሊም (1/534) በቁጥር (771) እና ሌሎችም ዘግበውታል።

አቡዳውድ (1/230) በቁጥር (873)፣ ነሳኢ በቁጥር (1131)፣ አሕመድ በቁጥር (23980) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በ "ሶሒሕ አቡዳውድ" (1/166) ላይ ሶሒሕ ብለውታል። ከዚህ በፊት በቁጥር (37) ላይ ተጠቅሷል።

ሙስሊም (1/ 230) በቁጥር (483) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/352) በቁጥር (486) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (1/231) በቁጥር (874)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (897) ዘግበውታል። "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/148) ይመልከቱ።

ከነሳኢ በስተቀር የሱነን አዘጋጆች፡ አቡ ዳውድ (1/231) በቁጥር (850)፣ ቲርሚዚይም በቁጥር (284) እና (285)፣ ኢብኑ ማጀህም በቁጥር (898) ዘግበውታል። "ሶሒሕ ቲርሚዚ" (1/90) እና "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/148) ተመልከት።

ቲርሚዚ (2/474) ላይ በቁጥር (3425) ፣ አሕመድ (6/30) ላይ በቁጥር (24022) እንዲሁም ሐኪም ዘግበው ሶሒሕ ሲሉት ዘሀቢም (1/220) ላይ ተስማምተውበታል፤ ጭማሪውም የዘሀቢ ዘገባ ነው።

ቲርሚዚ 2/473 ላይ በቁጥር 579 ፣ ሐኪም 1/219 ላይ ዘግበው ሶሒሕ ሲሉት ዘሀቢም ተስማምተውበታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (2/311) በቁጥር (831) ፣ ሙስሊም (1/301) በቁጥር (402) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/ 408) በቁጥር (3370) እና ሙስሊም በቁጥር (406) ዘግበውታል።

ቡኻሪይ ከፈትሕ ጋር (6/407) በቁጥር (3369)፤ ሙስሊም (1/306) በቁጥር (407)፤ ቃሉ በሙስሊም ዘገባ ላይ ያለው ነው።

ቡኻሪይ (2/102) በቁጥር (1377)፤ ሙስሊም (1/412) በቁጥር (588)፤ ቃሉ በሙስሊም ዘገባ ላይ ያለው ነው።

ቡኻሪ (1/202) በቁጥር (832) እና ሙስሊም (1/412) በቁጥር (587) ዘግበውታል።

ቡኻሪ (8/168) በቁጥር (834) ፣ ሙስሊም (4/2078) በቁጥር (2705) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/534) በቁጥር (771) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (2/86) በቁጥር (1522)፣ ነሳኢ (3/53) በቁጥር (2302) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በ "ሶሒሕ አቡ ዳውድ" (1/284) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/35) በቁጥር (2822) እና (6390) ላይ ዘግበውታል።

አቡዳውድ በቁጥር (792)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (910) ዘግበውታል። ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/328) ተመልከት።

ነሳኢ (3/54) (55) በቁጥር (1304)፣ አሕመድ (4/364) በቁጥር (21666) ሲዘግቡት አልባኒ በ "ሶሒሕ ነሳኢ" (1/281) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ነሳኢ (3/ 52) ላይ በቁጥር (1300) የሐዲሱ ቃላትም የሳቸው ዘገባ ነው፤ አሕመድ (4/338) ላይ በቁጥር (18974) የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በ "ሶሒሕ አን-ነሳኢ" (1/280) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

የሱነን ዘጋቢዎች የሆኑት አቡዳውድ በቁጥር (1495)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3544)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3858)፣ ነሳኢ በቁጥር (1299) የዘገቡት ሲሆን፤ በ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/329) ላይ ይመልከቱ።

አቡዳውድ (2/62) በቁጥር (1493)፣ ቲርሚዚ (5/515) በቁጥር (3475)፣ ኢብኑ ማጀህ (2/1267) በቁጥር (3857)፣ ነሳኢ በቁጥር (1300) በዚሁ ቃል፣ አሕመድ በቁጥር (18974) የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በ "ሶሒሕ አን-ነሳኢ" (1/280) ላይ ሶሒሕ ብለውታል። "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/329) እና "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/163) ይመልከቱ።

ሙስሊም (1/414) በቁጥር (591) ዘግበውታል።

ቡኻሪይ (1/255) በቁጥር (844) ፣ ሙስሊም (1/414) በቁጥር (593) የዘገቡት ሲሆን በቅንፉ ውስጥ ያለው ደግሞ ከቡኻሪይ በቁጥር (6473) የተጨመረ ነው።

ሙስሊም (1/415) በቁጥር (594) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/418) በቁጥር (597) የዘገቡት ሲሆን በውስጡም፦ «ከሁሉም (ግዴታ) ሶላት በኋላ ይህንን ያለ ሰው ወንጀሉ የባህር አረፋ አምሳያ ቢደርስ እንኳ ይማራል።»

አቡዳውድ (2/86) በቁጥር (1523)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (2903)፣ ነሳኢ (3/68) በቁጥር (1335) የዘገቡት ሲሆን "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (2/8) ይመልከቱ። ሦስቱ ሱራዎች "አልሙዐዊዛት" ይባላሉ። "ፈትሑል ባሪ" (9/62) ይመልከቱ።

«ከሁሉም ሶላት በኋላ እርሷን የቀራ ሰው ጀነት ለመግባት ከሞት በቀር ምንም አይከለክለውም።» ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር (100)፣ ኢብኑ አስ-ሱኒ በቁጥር (121) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በሶሒሑል ጃሚዕ (5/339) እና በሲልሲለቱል አሓዲሲስ-ሶሒሐህ (2/697) በቁጥር (972) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ቲርሚዚይ (5/515) በቁጥር (3474) እና አሕመድ (4/227) በቁጥር (17990) ዘግበውታል። ተኽሪጁን በዛዱል መዓድ (1/300) ይመልከቱ።

ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (925)፣ ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ በቁጥር (102) ዘግበውታል። ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (1/152) እና መጅመዑዝ-ዘዋኢድ (10/111) ይመልከቱ፤ እንዲሁም በቁጥር (95) ላይ ይመጣል።

ቡኻሪ (7/ 162) በቁጥር (1162) ዘግበውታል።

ሱረቱ ኣሊ-ዒምራን፡ 159

ከአነስ እንደተላለፈው ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በማስጠጋት እንዲህ አሉ፦ «አላህን ከሚያወሱ ሰዎች ጋር ከንጋት ሶላት ጀምሮ ፀሐይ እስክትወጣ ድረስ መቀመጥ ከኢስማዒል ልጆች አራት ሰዎችን ነፃ ከማውጣት ይበልጥ ለእኔ የተወደደ ነው። እንዲሁም አላህን ከሚያወሱ ሰዎች ጋር ከዐስር ሶላት ጀምሮ ፀሐይ እስክትጠልቅ ድረስ መቀመጥ አራት ሰዎችን ነፃ ከማውጣት ይበልጥ ለእኔ የተወደደ ነው።» አቡ ዳውድ በቁጥር (3667) ዘግበውታል፣ አልባኒም በ‹ሶሒሕ አቢ ዳውድ› (2/698) ሐሰን ብለውታል።

«በሚያነጋ ወቅት የተናገራት እስኪያመሽ ድረስ ከጂን ይጠበቃል። በሚያመሽ ወቅት የተናገራት ደግሞ እስኪያነጋ ድረስ ከነርሱ ይጠበቃል።» ሓኪም (1/562) ዘግበውታል፤ አልባኒይም በ "ሶሒሕ ተርጊብ ወት-ተርሂብ" (1/273) ሶሒሕ ብለውታል። ወደ ነሳኢይ እና ጠበራኒይም አስጠግተውታል፤ "የጠበራኒይ ኢስናድ ጥሩ ነው" ብለዋል።

'ንጋት ላይና ምሽት ላይ ሶስት ጊዜ ያላት ሰው ከሁሉም ነገር ትበቃዋለች።' አቡዳውድ (4/322) በቁጥር (5082)፣ እንዲሁም ቲርሚዚ (5/567) በቁጥር (3575) ዘግበውታል። "ሶሒሕ ቲርሚዚ" (3/182)ን ይመልከቱ።

ሙስሊም (4/2088) በቁጥር (2723) ዘግበውታል።

የቀድሞው ምንጭ።

ቲርሚዚይ (5/466) ላይ በቁጥር (3391)፣ እንዲሁም "ሶሒሕ ቲርሚዚይ" (3/142) ላይ ይመልከቱ።

የቀድሞው ማጣቀሻ።

አረጋግጣለሁ፣ እናዘዛለሁም።

"በሚያመሽ ወቅት በእርግጠኝነት አምኖባት የተናገራትና በዚያው ሌሊት የሞተ ሰው ጀነት ይገባል። በሚያነጋም ወቅት እንደዚሁ።" ቡኻሪ (7/150) በቁጥር (6306) ዘግበውታል።

«ንጋት ላይ ወይም ምሽት ላይ ይህንን አራት ጊዜ ያለ ሰው አላህ ከእሳት ነፃ ያወጣዋል።» አቡ ዳውድ (4/317) በቁጥር (5071)፣ ቡኻሪ በ "አደቡል ሙፍረድ" በቁጥር (1201)፣ ነሳኢ በ "ዐመሉል የውሚ ወልለይላህ" በቁጥር (9)፣ ኢብኑ ሱኒ በቁጥር (70) የዘገቡት ሲሆን ክቡር ሸይኽ ኢብኑ ባዝ (አላህ ይዘንላቸው) በ "ቱሕፈቱል አኽያር" (ገጽ 23) ላይ የነሳኢንና የአቡ ዳውድን ኢስናድ ሐሰን ብለውታል።

የቀድሞው ዋቢ።

«ሲነጋለት ይህንን ያለ ሰው የቀኑን ምስጋና በእርግጥ ተወጥቷል፤ ሲመሽ ደግሞ ይህንን ያለ ሰው የሌሊቱን ምስጋና በእርግጥ ተወጥቷል፡፡» አቡ ዳውድ በ 4/318 በቁጥር 5075 ላይ፣ ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይላ" ውስጥ በቁጥር 7 ላይ፣ ኢብኑ አስ-ሱኒ በቁጥር 41 ላይ፣ እና ኢብኑ ሒባን "መዋሪድ" ውስጥ በቁጥር 2361 ላይ የዘገቡት ሲሆን ኢብኑ ባዝ (አላህ ይዘንላቸውና) "ቱሕፈቱል አኽያር" 24ኛ ገፅ ላይ ሰነዱን ሐሰን ብለውታል።

የቀድሞው ምንጭ።

አቡዳውድ (4/324) በቁጥር (5092)፣ አሕመድ (5/42) በቁጥር (20430)፣ ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይላ" ውስጥ በቁጥር (22)፣ ኢብኑስ ሱኒ በቁጥር (69)፣ ቡኻሪ "አልአደቡል ሙፍረድ" ውስጥ በቁጥር (701) የዘገቡት ሲሆን ታላቁ ሊቅ ኢብኑ ባዝ ረሒመሁላህ በቱሕፈቱል አኽያር (ገፅ 26) ላይ ሰነዱን ሐሰን ብለውታል።

" "ንጋት ላይና ምሽት ላይ ሰባት ጊዜ ይህንን ያለ ሰው አላህ ከዱኒያና ከአኺራ ጉዳይ ያሳሰበውን ነገር ይበቃዋል።" ኢብኑ ሱኒ በቁጥር (71) መርፉዕ አድርገው፣ አቡ ዳውድ ደግሞ መውቁፍ አድርገው (4/ 321) በቁጥር (5081) የዘገቡት ሲሆን ሹዐይብ እና አብዱልቃድር አል-አርናኡጥ ሰነዱን ሶሒሕ ብለውታል። ዛዱል መዓድ (2/376) ይመልከቱ"

አቡዳውድ በቁጥር (5074)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3871) የዘገቡት ሲሆን "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/332) ይመልከቱ።

ቲርሚዚይ በቁጥር (3392) እና አቡዳውድ በቁጥር (5067) ዘግበውታል፣ ሶሒሕ አት-ቲርሚዚ (3/142) ይመልከቱ።

«ንጋት ላይ ሶስት ጊዜ፣ ምሽት ላይም ሶስት ጊዜ ያለ ሰው አንዳችም ነገር አይጎዳውም።» አቡዳውድ (4/ 323) በቁጥር (5088)፣ ቲርሚዚ (5/ 465) በቁጥር (3388)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3869) እና አሕመድ በቁጥር (446) የዘገቡት ሲሆን፤ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/332) ተመልከት። ታላቁ ሊቅ ኢብኑ ባዝ አላህ ይዘንላቸውና በ "ቱሕፈቱል አኽያር" (ገጽ 39) ላይ ሰነዱን ሐሰን ብለውታል።

«ጠዋት ሲነጋ ሶስት ጊዜ፣ ምሽት ሲገባም ሶስት ጊዜ ይህንን ያለ ሰው የትንሳኤ ቀን ሊያስደስተው በአላህ ላይ ሐቅ ይሆንለታል።» አሕመድ 4/337 ላይ በቁጥር 18967፣ ነሳኢ በ "ዐመል አልየውም ወልለይላ" ውስጥ በቁጥር 4፣ ኢብኑ አስሱኒ በቁጥር 68፣ አቡዳውድ 4/318 ላይ በቁጥር 1531፣ ቲርሚዚ 5/465 ላይ በቁጥር 3389 የዘገቡት ሲሆን ኢብኑ ባዝ ረሒመሁላህ በ "ቱሕፈቱል አኽያር" 39ኛ ገፅ ላይ ሐሰን ብለውታል።

ሐኪም ዘግበው ሶሒሕ ያሉት ሲሆን ዘሀቢም (1/545) ተስማምተውበታል። "ሶሒሕ ተርጊብ ወት-ተርሂብ" (1/273) ላይ ይመልከቱ።

አቡዳውድ (4/322) በቁጥር (5084) የዘገቡት ሲሆን ሹዐይብ እና ዐብዱልቃዲር አልአርናኡጥ በዛዱል መዓድ ተሕቂቅ (2/373) ላይ ሰነዱን ሐሰን ብለውታል።

የቀድሞው ምንጭ።

አሕመድ (3/406) እና (407) በቁጥር (15360) እና (15563)፣ ኢብኑ ሱኒ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ በቁጥር (34) የዘገቡት ሲሆን፣ "ሶሒሑል ጃሚዕ" (4/209) ይመልከቱ።

የቀድሞው ምንጭ።

«ሲነጋና ሲመሽ ይህንን መቶ ጊዜ ያለ ሰው፤ የትንሳኤ ቀንም እርሱ ያለውን አምሳያ ያለ ወይም በእርሱ ላይ የጨመረ ሰው ካልሆነ በቀር ማንም በላጭ ስራ ይዞ አይመጣም።» ሙስሊም (4/2071) በቁጥር (2692)።

ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ በቁጥር (24) ዘግበውታል፤ ይመልከቱ፡- ሶሒሕ አት-ተርጊብ ወት-ተርሂብ (1/272) እና የኢብኑ ባዝ (ረሒመሁላህ) "ቱሕፈቱል አኽያር" (ገጽ 44)፣ እንዲሁም ትሩፋቱን በ(ገጽ 146) ሐዲስ ቁጥር (255) ላይ ይመልከቱ።

አቡዳውድ በቁጥር (5077)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3798)፣ አሕመድ በቁጥር (8719) ዘግበውታል። ሶሒሕ አትተርጊብ ወትተርሂብ (1/270)፣ ሶሒሕ አቡዳውድ (3/957)፣ ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/331) እና ዛዱል መዓድ (2/377) ላይ ይመልከቱ።

«ይህንን በቀን ውስጥ መቶ ጊዜ ያለ ሰው ለርሱ አስር ባሪያዎችን ነፃ ከማውጣት ጋር እኩል ትሆንለታለች፤ መቶ ምንዳ ይፃፍለታል፤ መቶ ወንጀሎችም ከርሱ ላይ ይሰረዙለታል፤ ምሽቱ እስኪገባ ድረስም ያንን ቀኑን ከሸይጧን መከለያ ትሆንለታለች፤ እርሱ ከሰራው አብዝቶ የሰራ ሰው ካልሆነ በቀር ማንም በላጭ ስራ ይዞ አይመጣም።» አል-ቡኻሪ (4/ 95) በቁጥር (3293)፣ እና ሙስሊም (4/ 2071) በቁጥር (2691)።

ሙስሊም (4/2090) በቁጥር (2726) ዘግበውታል።

ኢብኑ ሱኒ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር (54)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (925) የዘገቡት ሲሆን ዐብዱልቃዲር እና ሹዐይብ አል-አርናኡጥ በ "ተሕቂቅ ዛዱል መዓድ" ውስጥ በ2/375 ላይ ሰነዱን ሐሰን ብለውታል። ከዚህ በፊት በቁጥር (73) አልፏል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/101) በቁጥር (6307) ፣ ሙስሊም (4/2075) በቁጥር (2702) ዘግበውታል።

«በሚያመሽ ጊዜ ይህንን ሶስት ጊዜ ያለ ሰው በዚያች ሌሊት መርዛማ ነገር አይጎዳውም።» አሕመድ 2/290 ላይ በቁጥር 7898፣ ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር 590 እና ኢብኑ ሱኒ በቁጥር 68 የዘገቡት ሲሆን፤ "ሶሒሕ ቲርሚዚ" 3/187፣ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" 2/266 እና የኢብኑ ባዝን "ቱሕፈቱል አኽያር" ገፅ 45 ይመልከቱ።

«በሚያነጋ ጊዜ በኔ ላይ አስር፣ በሚያመሽም ጊዜ አስር ሶለዋት ያወረደ፤ የቂያማ ቀን ምልጃዬ ትደርሰዋለች።» ጦበራኒ በሁለት ሰነዶች ዘግበውታል፦ ከነሱም አንደኛው ጀይድ (ጥሩ) ነው፣ መጅመዑዝ-ዘዋኢድ (10/120)፣ እና ሰሂህ አት-ተርጊብ ወት-ተርሂብ (1/273) ተመልከት።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (9/62) በቁጥር (5017) እና ሙስሊም በቁጥር (2192) ዘግበውታል።

«ወደ መኝታው በሄደ ጊዜ እርሷን የቀራ ሰው እስኪነጋ ድረስ የአላህ ከለላ አይለየውም፤ ሸይጧንም አይቀርበውም።» ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (4/487) በቁጥር (2311)።

"በምሽት ውስጥ ሁለቱን የቀራ ሰው ይበቁታል።" ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (9/94) በቁጥር (4008) እና ሙስሊም (1/554) በቁጥር (807) ዘግበውታል።

"አንዳችሁ ከፍራሹ የተነሳና ከዚያም ወደርሱ የተመለሰ ጊዜ በሽርጡ (በታችኛው ልብሱ) ጫፍ ሶስት ጊዜ ያራግፈው፣ የአላህንም ስም ይጥራ፤ እርሱ (ከሄደ) በኋላ (በፍራሹ ላይ) ምን እንደተተካ አያውቅምና። በተጋደመም ጊዜ፡-.. ይበል።" ሐዲሡ (እስከ መጨረሻው)። [‹በኢዛሩ ሶኒፋ› የሚለው ትርጉም፡- ከዳር በኩል ቀጥሎ ያለው ጫፉ ማለት ነው።] አን-ኒሃያ ፊ ገሪቢል ሐዲሥ ወል-አሠር (ሶነፈ)።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/126) በቁጥር (6320) እና ሙስሊም (4/2084) በቁጥር (2714) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2083) በቁጥር (2712) ላይ፤ አሕመድ በዚሁ ቃል (2/79) በቁጥር (5502) ላይ ዘግበውታል።

«ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- መተኛት የፈለጉ ጊዜ ቀኝ እጃቸውን ከጉንጫቸው ስር ያኖሩ ነበር። ቀጥለውም እንዲህ ይሉ ነበር: ...» ሐዲሡ።

አቡዳውድ (4/311) በቁጥር (5045)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3398) የዘገቡት ሲሆን ከላይ የተጠቀሰው ቃል የአቡዳውድ ዘገባ ነው። "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/143) እና "ሶሒሕ አቡዳውድ" (3/240) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/113) በቁጥር (6324) ፣ ሙስሊም (4/2083) በቁጥር (2711) ዘግበውታል።

«ወደ መኝታው ሲያመራ ይህንን ያለ ሰው ከአገልጋይ የተሻለ ይሆንለታል።» ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (7/71) በቁጥር (3705) እና ሙስሊም (4/2091) በቁጥር (2726) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2084) በቁጥር (2713) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2085) በቁጥር (2715) ዘግበውታል።

አቡ ዳውድ (4/317) በቁጥር (5067)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3629) ዘግበውታል። በ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/142) ላይ ይመልከቱ።

ቲርሚዚ በቁጥር (3404)፣ ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር (707) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አልጃሚዕ" (4/255) ተመልከት።

«ለመተኛት ስፍራህን በያዝክ ጊዜ ለሰላት እንደምታደርገው ዉዱእ አድርግ፤ ከዚያም በቀኝ ጎንህ ተጋደም፤ ከዚያም እንዲህ በል፦ ...» (እስከ ሐዲሡ መጨረሻ)።

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ይህን ላለው ሰው፡- «ብትሞት በተፈጥሮ (በእስልምና) ላይ ሆነህ ትሞታለህ» አሉት። ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/113) በቁጥር (6313) እና ሙስሊም (4/2081) በቁጥር (2710) ዘግበውታል።

በሌሊት ከጎን ወደ ጎን ሲገላበጥ ይህን ይላል። ሐኪም ዘግበውት ሶሒሕ ሲሉት ዘሀቢም (1/540) ተስማምተውበታል። እንዲሁም ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መጽሐፋቸው ውስጥ በቁጥር (202) እና ኢብኑስ-ሱኒ በቁጥር (757) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አልጃሚዕ" (4/213) ይመልከቱ።

አቡዳውድ (4/12) በቁጥር (3893)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3528) ዘግበውታል፤ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/171) ይመልከቱ።

ሙስሊም (4/1772) በቁጥር (2261) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/1772) (1773) በቁጥር (2261) እና (2262) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/1772) በቁጥር (2261) እና (2263) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/1773) በቁጥር (2261) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/1773) በቁጥር (2263) ዘግበውታል።

አራቱ አስሐቡስ-ሱነን፣ አሕመድ፣ ዳሪሚ እና በይሀቂ የዘገቡት ሲሆን፡ አቡዳውድ በቁጥር (1425)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (464)፣ ነሳኢ በቁጥር (1744)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (1178)፣ አሕመድ በቁጥር (1718)፣ ዳሪሚ በቁጥር (1592)፣ ሐኪም (3/172) እና በይሀቂ (2/209) ዘግበውታል። በቅንፉ መሀል ያለው በይሀቂ ውስጥ ያለ ሲሆን፤ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (1/144)፣ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/194) እና የአልባኒን "ኢርዋኡል ገሊል" (2/172) ተመልከት።

አራቱ የሱነን አዘጋጆች እና አሕመድ የዘገቡት ሲሆን፤ አቡዳውድ በቁጥር (1427)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3566)፣ ነሳኢ በቁጥር (1746)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (1179) እና አሕመድ በቁጥር (751) ዘግበውታል። ይመልከቱ፦ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/180)፣ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/194) እና "አልኢርዋእ" (2/175)።

አል'በይሃቂይ በ«አስ-ሱነኑ አል-ኩብራ» ላይ ዘግበውታል፤ ሰነዱንም (2/211) ላይ ሶሒሕ ብለውታል። ሸይኽ አልባኒም በ "ኢርዋኡል ገሊል" (2/170) ላይ ”ይህ ሰነድ ሶሒሕ ነው።“ ብለዋል። ይህም በዑመር ላይ መውቁፍ ነው።

ነሳኢ (3/244) በቁጥር (1734)፣ ዳረቁጥኒ (2/31) እና ሌሎችም የዘገቡት ሲሆን በቅንፉ መሀል ያለው የዳረቁጥኒ (2/31) በቁጥር (2) ጭማሪ ነው። ኢስናዱም ሶሒሕ ነው። "ዛዱል መዓድ" በሹዓይብ አልአርናኡጥ እና አብዱልቃዲር አልአርናኡጥ (1/337) ተመልከት።

አሕመድ (1/391) በቁጥር (3712) ዘግበውታል፤ አልባኒይም በሲልሲለቱል አሓዲሲስ-ሶሒሓህ (1/337) ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪይ (7/158) በቁጥር (2893) የዘገቡት ሲሆን፣ መልክተኛው (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ይህንን ዱዓ ያበዙ ነበር። ቡኻሪይ ከፈትሕ ጋር (11/173) ይመልከቱ፣ ወደፊትም (ገጽ 89) በቁጥር (137) ይመጣል።

ቡኻሪ (7/154) በቁጥር (6345) እና ሙስሊም (4/2092) በቁጥር (2730) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (4/324) በቁጥር (5090) ፣ አሕመድ (5/42) በቁጥር (20430) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በሶሒሕ አቡዳውድ (3/959) ላይ ሐሰን ብለውታል።

ቲርሚዚ በ5/529 በቁጥር 3505 ፣ ሐኪም በ1/505 ዘግበው ሶሒሕ ሲሉት ዘሀቢም ተስማምተውበታል ፣ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" 3/168 ይመልከቱ።

አቡ ዳውድ (2/87) በቁጥር (1525) ኢብኑ ማጀህም በቁጥር (3882) ዘግበውታል። ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/335) ይመልከቱ።

አቡዳውድ (2/89) በቁጥር (1537) የዘገቡት ሲሆን አልሓኪም ሶሒሕ ብለውታል፣ ዘሀቢም (2/142) ላይ ተስማምተውበታል።

አቡዳውድ (3/42) በቁጥር (2632)፣ ቲርሚዚ (5/572) በቁጥር (3584) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/183) ይመልከቱ።

ቡኻሪ (5/172) በቁጥር (4563)።

ቡኻሪይ በአደቡል ሙፍረድ በቁጥር (707) ዘግበውታል። አልባኒይ በሶሒሕ አደቡል ሙፍረድ በቁጥር (545) ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪይ በአደቡል ሙፍረድ በቁጥር (708) ዘግበውታል። አልባኒይ በሶሒሕ አደቡል ሙፍረድ በቁጥር (546) ሶሒሕ ብለውታል።

ሙስሊም (3/1362) በቁጥር (1742) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2300) በቁጥር (3005) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/336) በቁጥር (3276) እና ሙስሊም (1/120) በቁጥር (134) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/336) በቁጥር (3276) እና ሙስሊም (1/120) በቁጥር (134) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1 /119-120) በቁጥር (134)።

አቡዳውድ (4/329) በቁጥር (5110) የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በሶሒሕ አቡዳውድ (3/962) ላይ ሐሰን ብለውታል።

ቲርሚዚይ (5/560) በቁጥር (3563)፣ ይመልከቱ፦ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/180)።

ቡኻሪ (7/158) በቁጥር (2893) ዘግበውታል፣ ከዚህ ቀደም (ገጽ 83) በቁጥር (121) ተጠቅሷል።

ሙስሊም (4/1729) በቁጥር (2203) ከዑሥማን ቢን አቢል ዓስ (ረ.ዐ) ሐዲሥ ዘግበውታል። በውስጡም፡- «ያንን አደረግኩ፤ አላህም ከእኔ አስወገደልኝ» የሚል ይገኝበታል።

ኢብኑ ሒባን በ "ሶሒሓቸው" በቁጥር (2427)፣ ኢብኑ ሱኒ በቁጥር (351) የዘገቡት ሲሆን ሐፊዝ፡- "ይህ ሐዲስ ሶሒሕ ነው" ብለዋል፤ አብዱልቃዲር አልአርናኡጥም በ "ተኽሪጅ አልአዝካር ሊን-ነወዊ" (ገጽ 106) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

አቡዳውድ (2/86) በቁጥር (1521)፣ ቲርሚዚ (2/257) በቁጥር (406) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በሶሒሕ አቡዳውድ (1/283) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

አቡዳውድ በ(1/203) በቁጥር፣ እና ኢብኑ ማጀህ በ(1/265) በቁጥር (807) የዘገቡት ሲሆን፣ ማጣቀሻው ከዚህ በፊት በቁጥር (31) አልፏል፤ ይመልከቱ፦ ሱረቱል ሙእሚኑን፡ [97-98]።

ሙስሊም (1/291) በቁጥር (389) እና ቡኻሪ (1/151) በቁጥር (608) ዘግበውታል።

ሙስሊም (1/539) በቁጥር (780) ዘግበውታል።

ቡኻሪ (4/126) በቁጥር (3293) ዘግበውታል።

«በሁሉም ውስጥ መልካም ነገር ቢኖርም፤ ጠንካራ ሙእሚን ከደካማው ሙእሚን አላህ ዘንድ የተሻለና ይበልጥ ተወዳጅ ነው። በሚጠቅምህ ነገር ላይ ጉጉት ይኑርህ! በአላህም ታገዝ! አትስነፍ! አንዳች ነገር ሲያገኝህም ‹እንዲህ አድርጌ በነበር እንዲህ እንዲህ ይሆን ነበር።› አትበል። ይልቁንም ‹ይህ የአላህ ውሳኔ ነው። የሻውንም ፈፀመ።› በል። (እንዲህ ቢሆን ኖሮ) ማለት የሰይጣንን ስራ ትከፍታለችና።» ሙስሊም (4/2052) በቁጥር (2664)።

ከሐሰኑል በስሪ ንግግር ተጠቅሷል። የኢብኑል ቀዪምን "ቱሕፈቱል መውዱድ" (ገፅ 20) ይመልከቱ፣ እንዲሁም በ "አልአውሰጥ" ውስጥ ለኢብኑል ሙንዚር አስጠግተውታል።

ነወዊ በ "አልአዝካር" (ገፅ 349) ላይ ብለውታል። የሰሊም አልሂላሊን "ሶሒሕ አልአዝካር ሊነወዊ" (2/713) እና የአዘጋጁን "ተማሙ አትተኽሪጅ ፊዝዚክር ወድዱዓእ ወልዒላጅ ቢርሩቃ" (1/416) ይመልከቱ።

ቡኻሪ (4/119) ከኢብን ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ በቁጥር (3371) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (10/118) በቁጥር (3616) ዘግበውታል።

«አንድም ሙስሊም ባሪያ ሞቱ ያልቀረበን በሽተኛ የጠየቀና ሰባት ጊዜ... ካለ ይፈወሳል።» ቲርሚዚ በቁጥር (2083) እንዲሁም አቡ ዳውድ በቁጥር (3106) ዘግበውታል፤ ሶሒሕ አቲርሚዚ (2/210) እና ሶሒሑል ጃሚዕ (5/180) ይመልከቱ።

ቲርሚዚ በቁጥር (969)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (1442)፣ አሕመድ በቁጥር (975) ዘግበውታል። በሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (1/244) ላይና በሶሒሕ አትቲርሚዚ (1/286) ላይ ይመልከቱ። አሕመድ ሻኪርም ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪ (7/10) በቁጥር (4435) እና ሙስሊም (4/1893) በቁጥር (2444) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (8/144) በቁጥር (4449) ዘግበውታል፣ በሐዲሱ ውስጥም ሲዋክ ተጠቅሷል።

ቲርሚዚይ በቁጥር (3430)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3794) የዘገቡት ሲሆን አልባኒይ ሶሒሕ ብለውታል። ሶሒሕ አትቲርሚዚይ (3/152) እና ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/317) ተመልከት።

አቡዳውድ (3/190) ላይ በቁጥር (3116) ዘግበውታል። እንዲሁም "ሶሒሕ አልጃሚዕ" (5/432) ይመልከቱ።

ሙስሊም (2/632) በቁጥር (918) ዘግበውታል።

ሙስሊም (2/634) በቁጥር (920) ዘግበውታል።

ሙስሊም (2/663) በቁጥር (963) ዘግበውታል።

አቡዳውድ በቁጥር (3201)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (1024)፣ ነሳኢ በቁጥር (1985)፣ ኢብኑ ማጀህ (1/480) በቁጥር (1498)፣ አሕመድ (2/368) በቁጥር (8809) የዘገቡት ሲሆን በ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/251) ላይ ይመልከቱ።

ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (1499) ዘግበውታል፣ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/251) ይመልከቱ፤ እንዲሁም አቡዳውድ በ(3/211) በቁጥር (3202) ላይ ዘግበውታል።

ሐኪም ዘግበው ሶሒሕ ያሉት ሲሆን ዘሀቢም (1/359) ተስማምተውበታል። የአልባኒን "አሕካሙል ጀናኢዝ" (ገፅ 125) ላይ ይመልከቱ።

(ሰዒድ ቢን አል-ሙሰየብ እንዲህ አሉ፡- ከአቡ ሁረይራ ረዲየላሁ ዐንሁ ኋላ ፈፅሞ ኃጢአት ሰርቶ በማያውቅ ህፃን ላይ ሰገድኩ፤ እንዲህ ሲሉም ሰማኋቸው..) ሐዲሱን እስከመጨረሻው። ማሊክ በሙወጦእ (1/288)፣ ኢብኑ አቢ ሸይባ በሙሶነፍ (3/217) እና በይሀቂ (4/9) የዘገቡት ሲሆን፤ ሹዐይብ አል-አርናዑጥ ለበገዊ ‹ሸርሁስ-ሱና› (5/357) ባደረጉት ተሕቂቅ የሐዲሱን ኢስናድ ሶሂህ ብለውታል።

የኢብኑ ቁዳማን አል‐ሙግኒ (3/416) እና የሸይኽ ዐብዱልዐዚዝ ብን ዐብዱላህ ብን ባዝን (ረሒመሁላህ) "አሳሳቢ ትምህርቶች ለብዙሀኑ ህዝብ" (ገፅ 15) ይመልከቱ።

ሐሰን በህፃኑ ላይ ፋቲሓን ይቀራና እንዲህ ይል ነበር... ሐዲሡ (እስከ መጨረሻው)። አል-በገዊ በሸርሁስ-ሱንና (5/357) እና ዐብዱረዛቅ በቁጥር (6588) ዘግበውታል፤ ቡኻሪም በኪታቡል ጀናኢዝ (65) «በጀናዛ ላይ ፋቲሓን መቅራት» በሚለው ምዕራፍ (2/113) ከሐዲሥ ቁጥር (1335) በፊት ሙዐለቅ አድርገው አስፍረውታል።

ቡኻሪ (2/80) በቁጥር (1284) ፣ ሙስሊም (2/636) በቁጥር (923) ዘግበውታል።

የነወዊ "አልአዝካር" (ገፅ 126)።

" አቡዳውድ (3/314) በቁጥር (3215) በሶሒሕ ሰነድ፣ አሕመድ በቁጥር (5234) እና በቁጥር (4812) «ቢስሚላህ፣ ወዐላ ሚለቲ ረሱሊላህ» በሚለው ቃል የዘገቡት ሲሆን ሰነዱም ሶሒሕ ነው።"

ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ሟችን ከቀበሩ በኋላ እርሱ ዘንድ ቆመው እንዲህ ይሉ ነበር፦ «ለወንድማችሁ ምህረትን ጠይቁለት! እርሱ አሁን ይጠየቃልና ፅናትን ለምኑለት።» አቡ ዳውድ (3/315) በቁጥር (3223) እና አል-ሓኪም ዘግበውት ሶሒሕ ብለውታል፣ አዝ-ዘሀቢም (1/370) ተስማምተውበታል።

ሙስሊም (2/671) በቁጥር (975)፣ እና ኢብኑ ማጀህ (1/494) ቃላቱ የሳቸው ሲሆን በቁጥር (1547) ከቡረይዳህ ረዲየላሁ ዐንሁ ዘግበውታል። በቅንፎች መካከል ያለው ደግሞ ሙስሊም ዘንድ ከዓኢሻ ረዲየላሁ ዐንሃ (2/671) በቁጥር (975) ተዘግቧል።

አቡ ዳውድ በ(4/326) በቁጥር (5099) ላይ ኢብኑ ማጀህም በ(2/1228) በቁጥር (3727) ላይ ዘግበውታል። "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/305) ይመልከቱ።

ሙስሊም (2/666) በቁጥር (899)፣ ቡኻሪይ (4/76) በቁጥር (3206) እና (4829) ዘግበውታል፤ ቃሉ የሙስሊም ዘገባ ላይ ያለው ነው።

ዐብደላህ ቢን አዝ'ዙበይር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- ነጎድጓድ በሰሙ ጊዜ ንግግርን ያቋርጡና እንዲህ ይሉ ነበር፦ ... ሐዲሱ አልሙወጦእ (2/992) ላይ የተዘገበ ሲሆን አልባኒም በ "ሶሒሕ አልከሊም አጥጦይብ" (157) ላይ "ሶሒሕ አልኢስናድ መውቁፍ" ብለውታል።

አቡዳውድ (1/303) በቁጥር (1171) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በሶሒሕ አቡዳውድ (1/216) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪ (1/224) በቁጥር (1014) እና ሙስሊም (2/613) በቁጥር (897) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (1/305) በቁጥር (1178) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በሶሒሕ አቡዳውድ (1/218) ላይ ሐሰን ብለውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (2/518) በቁጥር (1032) ዘግበውታል።

ቡኻሪ (1/205) በቁጥር (846) ፣ ሙስሊም (1/83) በቁጥር (71) ዘግበውታል።

ቡኻሪ (1/224) በቁጥር (933) እና ሙስሊም (2/614) በቁጥር (897) ዘግበውታል።

ቲርሚዚ (5/504) በቁጥር (3451)፣ ዳሪሚ በዚሁ ቃሉ (1/336) ላይ ዘግበውታል። "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/157) ይመልከቱ።

አቡ ዳውድ (2/306) በቁጥር (2359) ላይ እና ሌሎችም ዘግበውታል። "ሶሒሑል ጃሚዕ" (4/209) ይመልከቱ።

ኢብኑ ማጀህ (1/557) በቁጥር (1753) ከዐብዱላህ ኢብኑ ዐምር (ረዲየላሁ ዐንሁማ) ዱዓ የዘገቡት ሲሆን ሓፊዝ በ "ተኽሪጁል አዝካር" ላይ ሐሰን ብለውታል። ይመልከቱ፦ ሸርሑል አዝካር (4/342)።

አቡ ዳውድ በ(3/347) በቁጥር (3767) ላይ ቲርሚዚይም በ(4/288) በቁጥር (1858) ላይ ዘግበውታል። ሶሒሕ ቲርሚዚይ (2/167) ይመልከቱ።

ቲርሚዚይ (5/506) በቁጥር (3455) ዘግበውታል፣ ሶሒሕ አትቲርሚዚ (3/158) ላይ ይመልከቱ።

ከነሳኢ በስተቀር የሱነን አዘጋጆች የዘገቡት ሲሆን እነሱም፦ አቡ ዳውድ በቁጥር (4025)፣ ቲርሚዚይም በቁጥር (3458)፣ ኢብኑ ማጀህም በቁጥር (3285) ናቸው። "ሶሒሕ ቲርሚዚ" (3/159) ይመልከቱ።

ቡኻሪ (6/214) በቁጥር (5458) እና ቲርሚዚ በቃሉ (5/507) በቁጥር (3456) ዘግበውታል።

ሙስሊም (3/1615) በቁጥር (2042) ዘግበውታል።

ሙስሊም (3/1626) በቁጥር (2055) ዘግበውታል።

ሱነን አቡዳውድ (3/367) በቁጥር 3856፣ ኢብኑ ማጀህ (1/556) በቁጥር 1747፣ ነሳኢ በ "ዐመሉል የውሚ ወልለይላ" ውስጥ በቁጥር 296-298 የዘገቡት ሲሆን፣ ነቢዩ ﷺ ከአንድ ቤተሰብ ዘንድ ባፈጠሩ ጊዜ ይህንን እንደሚሉ ተገልጿል። አልባኒም በ "ሶሒሕ አቡዳውድ" (2/730) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ሙስሊም (2/1054) በቁጥር (1150) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (4/103) በቁጥር (1894) እና ሙስሊም (2/806) በቁጥር (1151) ዘግበውታል።

ሙስሊም (2/1000) በቁጥር (1373) ዘግበውታል።

ቡኻሪ (7/125) በቁጥር (5870) ዘግበውታል።

ቲርሚዚ (5/82) በቁጥር (2741)፣ አሕመድ (4/400) በቁጥር (19586) እና አቡዳውድ (4/308) በቁጥር (5040) ዘግበውታል፤ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (2/354) ይመልከቱ።

ከነሳኢ ውጭ አስሓቡስ-ሱነን ዘግበውታል፡ አቡ ዳውድ በቁጥር (2130)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (1091)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (1905)፣ እንዲሁም ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር (259) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (1/316) ይመልከቱ።

አቡ ዳውድ (2/248) በቁጥር (2160)፣ ኢብኑ ማጀህ (1/617) በቁጥር (1918) ዘግበውታል። "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/324) ይመልከቱ።

ቡኻሪይ (6/141) በቁጥር (141) እና ሙስሊም (2/1028) በቁጥር (1434) ዘግበውታል።

ቡኻሪ (7/99) በቁጥር (3282)፣ ሙስሊም (4/2015) በቁጥር (2610) ዘግበውታል።

ቲርሚዚይ (5/494)ና (5/493) ላይ በቁጥር (3432) ዘግበውታል። ሶሒሕ አትቲርሚዚ (3/153) ላይ ይመልከቱ።

ቲርሚዚ በቁጥር (3434)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3814) ዘግበውታል፤ ሶሒሕ አትቲርሚዚ (3/153) እና ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/321) ላይ ይመልከቱ፤ ቃሉም የቲርሚዚ ነው።

አስሓቡስ-ሱነን፡ አቡዳውድ በቁጥር (4858)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (3433)፣ ነሳኢ በቁጥር (1344) የዘገቡት ሲሆን፤ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/153) ይመልከቱ። ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንዲህ ማለታቸው ተረጋግጧል፡- «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ማናቸውንም መቀመጫ አልተቀመጡም፣ ቁርኣንንም አላነበቡም፣ ሶላትንም አልሰገዱም በነዚህ ቃላቶች የደመደሙት ቢሆን እንጂ…» ሐዲሱን። ነሳኢ 'ዐመሉል የውሚ ወልለይላ' በሚለው ኪታባቸው ውስጥ በቁጥር (308)፣ አሕመድ (6/77) በቁጥር (24486) የዘገቡት ሲሆን፣ ዶክተር ፋሩቅ ሐማዳ ለነሳኢ 'ዐመሉል የውሚ ወልለይላ' ባደረጉት ተሕቂቅ 273 ገፅ ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

አሕመድ (5/82) በቁጥር (20778)፣ ነሳኢይ በ‹ዐመል አል-የውም ወል-ለይላ› (ገጽ 218) በቁጥር (421)፣ በዶክተር ፋሩቅ ሐማዳ ተሕቂቅ።

ቲርሚዚይ በቁጥር (2035) ዘግበውታል፤ "ሶሒሑል ጃሚዕ" (6244) እና "ሶሒሑ ቲርሚዚይ" (2/200) ይመልከቱ።

እዚህ መጽሐፍ ውስጥ ሐዲሥ ቁጥር (55) እና ሐዲሥ (56) (ገጽ 41) ተመልከት።

ሙስሊም (1/555) በቁጥር (809) ዘግበውታል። በሌላ ዘገባ ደግሞ፡- ከከህፍ መጨረሻ (1/556) በቁጥር (809) ዘግበውታል።

አቡ ዳውድ (4/333) በቁጥር (5125) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በ "ሶሒሕ ሱነን አቢ ዳውድ" (3/965) ውስጥ ሐሰን ብለውታል።

ቡኻሪይ ከፈትሕ ጋር (4/288) በቁጥር (2049) ዘግበውታል።

" ነሳኢ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ (ገፅ 300)፣ ኢብኑ ማጀህ (2/809) በቁጥር (2424) ዘግበውታል። ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ (2/55) ይመልከቱ።"

አሕመድ (4/403) ላይ በቁጥር (19606)፣ ቡኻሪይ በ "አደቡል ሙፍረድ" በቁጥር (716) ዘግበውታል። "ሶሒሕ አልጃሚዕ" (3/233) እና የአልባኒን "ሶሒሕ ተርጚብ ወትተርሂብ" (1/19) ይመልከቱ።

ኢብኑ ሱኒይ (ገጽ 138) በቁጥር (278) ዘግበውታል፣ ይመልከቱ፦ አል-ዋቢል አስ-ሰዪብ የኢብኑል ቀዪም (ገጽ 304)፣ የበሺር ሙሐመድ ዑዩን ተሕቂቅ።

አሕመድ በ(2/220) በቁጥር (7045)፣ ኢብኑ አስ-ሱኒ በቁጥር (292) የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በ"ሲልሲለቱል አሓዲሲስ-ሶሒሓ" (3/54) በቁጥር (1065) ላይ ሶሒሕ ብለውታል። "አልፈእል" (በጎ ምኞት) ግን ነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ያስደስታቸው ነበር፤ ስለዚህም ከአንድ ሰው መልካም ቃልን ሰምተው ስላስደሰታቸው እንዲህ አሉ፦ «"ፈእል"ህን ከአፍህ ወስደናል።» አቡዳውድ በቁጥር (3719)፣ አሕመድ በቁጥር (9040) የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በ"ሲልሲለቱል አሓዲሲስ-ሶሒሓ" (2/363) ላይ ሶሒሕ ብለውታል። ይህም አቡሸይኽ ዘንድ በ"አኽላቁን-ነቢይ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና)" ገፅ 270 ላይ ይገኛል።

አቡዳውድ (3/34) በቁጥር (2602)፣ ቲርሚዚ (5/501) በቁጥር (3446) የዘገቡት ሲሆን፤ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/156)፣ ሱረቱ አዝዙኽሩፍ [13- 14] ይመልከቱ።

ሙስሊም (2/978) በቁጥር (1342) ዘግበውታል።

ሐኪም ዘግበውት ሶሒሕ ሲሉት ዘሀቢም ተስማምተውበታል (2/100)። ኢብኑሱኒም በቁጥር (524) ዘግበውታል። ሐፊዝ በ "ተኽሪጅ አልአዝካር" 5/154 ላይ ሐሰን ብለውታል። ዐላማህ ኢብኑ ባዝ ረሒመሁላህ እንዲህ ብለዋል፦ "ነሳኢ በሐሰን ሰነድ ዘግበውታል።" ተመልከት፦ ቱሕፈቱል አኽያር (ገጽ 37)።

ቲርሚዚ በቁጥር 3428፣ ኢብኑ ማጀህ 5/291 በቁጥር 3860፣ ሐኪም 1/538 ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" 2/21 እና በ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" 3/152 ላይ ሐሰን ብለውታል።

አቡዳውድ (4/296) በቁጥር (4982) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በሶሒሕ አቡዳውድ (3/941) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

አሕመድ (2/403) በቁጥር (9230) እና ኢብኑ ማጀህ (2/943) በቁጥር (2825) ዘግበውታል፤ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (2/133) ይመልከቱ።

አሕመድ (2/7) በቁጥር (4524)፣ እንዲሁም ቲርሚዚይ (5/499) በቁጥር (3443) ዘግበውታል፤ አልባኒይም በሶሒሕ ሱነን አትቲርሚዚይ (3/419) ሶሒሕ ብለውታል።

ቲርሚዚይ በቁጥር (3444)፣ እንዲሁም ሶሒሕ አትቲርሚዚ (3/155) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/135) በቁጥር (2993) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2086) በቁጥር (2718) ዘግበውታል። የ«ሰመዐ ሳሚዑን» ትርጉም፡- አላህ ተዓላ በዋለልን ጸጋዎችና በመልካም ስጦታው ላይ ለአላህ ያቀረብነውን ምስጋና መስካሪ መሰከረ ማለት ነው። እንዲሁም የ«ሰመዐ ሳሚዑን» ትርጉም፡- ይህን ንግግሬን የሰማ ሰው ለሌላው አደረሰ፣ በሰሐር ጊዜ ዚክርና ዱዓእ ማድረግን ለማስታወስ ሲልም መሰሉን ተናገረ ማለት ነው። ሸርሕ አን-ነወዊ ዐላ ሰሒሕ ሙስሊም (17/39)።

ሙስሊም (4/2080) በቁጥር (2709) ዘግበውታል።

ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከዘመቻ ወይም ከሐጅ በሚመለሱ ወቅት ይሉት ነበር፣ ቡኻሪ (7/163) በቁጥር (1797) እና ሙስሊም (2/980) በቁጥር (1344) ዘግበውታል።

ኢብኑ ሱኒ "ዐመሉል የውሚ ወልለይለህ" በሚለው መፅሀፋቸው ውስጥ በቁጥር (377)፣ እንዲሁም ሓኪም (1/499) የዘገቡትና ሶሒሕ ያሉት ሲሆን አልባኒም በሶሒሑል ጃሚዕ (4/201) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ሙስሊም (1/288) በቁጥር (384) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (2/218) በቁጥር (2044)፣ አሕመድ (2/367) በቁጥር (8804) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በሶሒሕ አቡዳውድ (2/383) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ቲርሚዚ በ(5/551) በቁጥር (3546) እና ሌሎችም ዘግበውታል፣ ይመልከቱ፦ "ሶሒሕ አልጃሚዕ" (3/25) እና "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/177)።

ነሳኢ (3/43) በቁጥር (1282)፣ ሐኪም በ (2/421) የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በ "ሶሒሕ ነሳኢ" (1/274) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

አቡዳውድ በቁጥር (2041) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በሶሒሕ አቡዳውድ (1/383) ላይ ሐሰን ብለውታል።

ሙስሊም (1/74) በቁጥር (54)፤ አሕመድም በቁጥር (1430) ዘግበውታል፤ ይህ የቃላት አወቃቀርም የዚሁ ዘገባ ነው፤ የሙስሊም ቃል ደግሞ፦ «لَا تَدْخُلُونَ...» የሚል ነው።

ቡኻሪይ ከአልፈትህ ጋር (1/82) በቁጥር (28)፣ ከዐማር (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና - መውቁፍና ሙዐለቅ ሆኖ የተዘገበ ነው።

ቡኻሪ ከአልፈትህ ጋር (1/55) በቁጥር (12) እና ሙስሊም (1/65) በቁጥር (39) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/42) በቁጥር (6258)፣ ሙስሊም (4/1705) በቁጥር (2163) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/350) በቁጥር (3303) እና ሙስሊም (4/2092) በቁጥር (2729) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (4/327) በቁጥር (5105)፣ አሕመድ (3/306) በቁጥር (14283) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በሶሒሕ አቡዳውድ (3/961) ላይ ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/171) በቁጥር (6361) እና ሙስሊም (4/2007) በቁጥር (396) ዘግበውታል፤ ቃሉም፡- «ለእርሱ ማጥሪያ እና እዝነት አድርግለት» ይላል።

ሙስሊም (4/2296) በቁጥር (3000) ዘግበውታል።

ቡኻሪይ በአደቡል ሙፍረድ በቁጥር (761) የዘገቡት ሲሆን፣ አልባኒይ በሶሒሕ አደቡል ሙፍረድ በቁጥር (585) ኢስናዱን ሶሒሕ ብለውታል። በማዕዘን ቅንፍ ውስጥ ያለው ደግሞ አል-በይሀቂ በ “ሹዓብ አል-ኢማን” (4/228) በሌላ መንገድ ያመጡት ጭማሪ ነው።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (3/408) በቁጥር (1549) እና ሙስሊም (2/841) በቁጥር (1184) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከአልፈትህ ጋር (3/476) በቁጥር (1613) ዘግበውታል፤ በነገሩ የተፈለገው፡ አልሚሕጀን ነው። ቡኻሪ ከአልፈትህ ጋር (3/472)ን ይመልከቱ።

አቡዳውድ (2/179) በቁጥር (1894) ፣ አሕመድ (3/411) በቁጥር (15398) ፣ በገዊ በ "ሸርሑስ ሱነህ" (7/128) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በሶሒሕ አቡዳውድ (1/354) ላይ ሐሰን ብለውታል። ሱረቱል በቀራህ።

ሙስሊም (2/888) በቁጥር (1218) ሱረቱል በቀራህ፡ ቁጥር 158.

ቲርሚዚ በቁጥር (3585) የዘገቡት ሲሆን አልባኒም በ "ሶሒሕ አት-ቲርሚዚ" (3/184) ላይና "ሲልሲለቱል አሐዲሢ-ስሶሒሐ" (4/6) ላይ ሐሰን ብለውታል።

ሙስሊም (2/891) በቁጥር (1218) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (3/583) በቁጥር (1751)፣ ቃሉንም እዚያው ይመልከቱ። እንዲሁም ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (3/583)፣ (3/584) እና (3/581) በቁጥር (1753)፣ ሙስሊምም እንዲሁ በቁጥር (1218) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከአልፈትህ ጋር (210/1)፣ (390) እና (414) በቁጥር (115)፣ (3599) እና (6218)፤ ሙስሊም (1857/4) በቁጥር (1674) ዘግበውታል።

ቡኻሪ ከ "አልፈትሕ" ጋር (8/441) በቁጥር (4741) እና (3062)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (2180)፣ ነሳኢ በ "አልኩብራ" ውስጥ በቁጥር (11185) የዘገቡት ሲሆን፤ ይመልከቱ፦ "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (2/103) እና (2/235)፣ እንዲሁም "ሙስነድ አሕመድ" (5/218) በቁጥር (21900)።

ከነሳኢ በስተቀር የሱነን አዘጋጆች የሆኑት አቡዳውድ በቁጥር (2774)፣ ቲርሚዚ በቁጥር (1578)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (1394) የዘገቡት ሲሆን፤ በ "ሶሒሕ ኢብኑ ማጀህ" (1/233) እና በ "ኢርዋኡል ገሊል" (2/226) ላይ ይመልከቱ።

ሙስሊም (4/1728) በቁጥር (2202) ዘግበውታል።

ሙስነድ አሕመድ (4/447) በቁጥር (15700)፣ ኢብኑ ማጀህ በቁጥር (3508)፣ ማሊክ (3/118-119) ላይ የዘገቡት ሲሆን አልባኒ በ "ሶሒሕ አልጃሚዕ" (1/212) ላይ ሶሒሕ ብለውታል። እንዲሁም የአርናኡጥን የ "ዛዱል መዓድ" ተሕቂቅ (4/170) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (6/381) በቁጥር (3346) እና ሙስሊም (4/2208) በቁጥር (2880) ዘግበውታል።

ሙስሊም (3/1557) በቁጥር (1967) እና በይሀቂ (9/287) ዘግበውታል። በቅንፍ ውስጥ ያሉት የበይሀቂ (9/287) እና የሌሎችም ነው፤ የመጨረሻዋን ዓረፍተ ነገር ከሙስሊም ዘገባ በመልእክቱ ነው ያሰፈርኳት።

አሕመድ (3/419) ላይ በቁጥር (15461) በሶሒሕ ሰነድ፣ ኢብኑስ-ሱኒይም በቁጥር (637) ዘግበውታል፤ አልአርናኡጥም በ"ጦሐዊያህ" ተኽሪጅ (ገፅ 133) ላይ ሰነዱን ሶሒሕ ብለውታል። "መጅመዑዝ-ዘዋኢድ" (10/127) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከአልፈትህ ጋር (11/101) በቁጥር (6307) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2076) በቁጥር (2702) ዘግበውታል።

አቡዳውድ (2/85) በቁጥር (1517)፣ ቲርሚዚ (5/569) በቁጥር (3577) እና ሐኪም የዘገቡት ሲሆን ሐኪም ሶሒሕ ብለውት ዘሀቢም (1/511) ተስማምተውበታል። አልባኒም ሶሒሕ ብለውታል። "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/182) እና "ጃሚዑል ኡሱል ሊአሓዲሲር ረሱል ﷺ" (4/389-390) በአርናኡጥ ተሕቂቅ ይመልከቱ።

ቲርሚዚ በቁጥር (3579) ፣ ነሳኢ (1/279) በቁጥር (572) ፣ ሐኪም (1/309) ላይ የዘገቡት ሲሆን "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/183) እና አርነኡጥ "ጃሚዑሉ ኡሱልን" በከለሱበት ስራቸው (4/144) ላይ ይመልከቱ።

ሙስሊም (1/350) በቁጥር (482) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2075) ላይ በቁጥር (2702) ዘግበውታል። ኢብኑል አሢር እንዲህ አሉ: "«ለዩጋኑ ዐላ ቀልቢ» 'በልቤ ላይ ይሸፈንበታል' ማለትም ይሸፈናል፤ ይጋረዳል ማለት ነው። የተፈለገበትም ትርጉም መዘናጋት ነው። ምክንያቱም ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ምንጊዜም አላህን አብዝቶ በማውሳት (በዚክር)፣ ወደ እርሱ በመቃረብ እና አላህን ዘወትር በመከታተል ላይ ነበሩ። በአንዳንድ ጊዜያት ከነዚህ ነገሮች ላይ ጥቂት እንኳ ቢዘናጉ ወይም ቢረሱ፤ በነፍሳቸው ላይ እንደ ወንጀል ይቆጥሩትና ወዲያውኑ የአላህን ምህረት ወደ መጠየቅ ይፈጥኑ ነበር።" "ጃሚዑል ኡሱል" (4/386) ይመልከቱ።

ቡኻሪ (7/168) በቁጥር (6405) እና ሙስሊም (4/2071) በቁጥር (2691) ዘግበውታል። እንዲሁም ከዚህ መጽሐፍ (ገጽ 65) ላይ «ጠዋትና ማታ መቶ ጊዜ ያላት ሰው ትሩፋት» የሚለውን ይመልከቱ።

ቡኻሪ (7/67) በቁጥር (6404)፣ ሙስሊም በዚሁ ቃል (4/2071) በቁጥር (2693) ዘግበውታል። በቀን መቶ ጊዜ ያለ ሰው ትሩፋትን ይመልከቱ፦ ከዚሁ መጽሐፍ ዱዓ ቁጥር (93) (ገጽ 66)።

ቡኻሪ (7/168) በቁጥር (6404) እና ሙስሊም (4/2072) በቁጥር (2694) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2072) በቁጥር (2695) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/2073) በቁጥር (2698) ዘግበውታል።

ቲርሚዚ በ(5/511) በቁጥር (3464)፣ ሐኪም በ(1/501) ሲዘግቡት ሶሒሕም ብለውታል። ዘሀቢም ተስማምተውበታል። "ሶሒሑል ጃሚዕ" (5/531) እና "ሶሒሕ አትቲርሚዚ" (3/160) ይመልከቱ።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (11/213) በቁጥር (4206) እና ሙስሊም (4/ 2076) በቁጥር (2704) ዘግበውታል።

ሙስሊም (3/1685) በቁጥር (2137) ዘግበውታል።

ሙስሊም (4/ 2072) በቁጥር (2696) የዘገቡት ሲሆን አቡ ዳውድም (1/ 220) በቁጥር (832) ላይ እንዲህ የሚል ጭማሪ አክለዋል (ገጠሬው ዞሮ የሄደ ጊዜ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) "በርግጥም እጁን በኸይር ሞላ።" አሉ)።

ሙስሊም (4/ 2073) በቁጥር (3697) የዘገቡት ሲሆን በሌላ ዘገባቸውም (እነዚህ ቃላቶች ላንተ ዱንያህንም አኺራህንም ይሰበስቡልሀል።) የሚል ጭማሪ አለው።

ቲርሚዚ 5/462 ላይ በቁጥር 3383፣ ኢብኑ ማጀህ 2/1249 ላይ በቁጥር 3800፣ ሐኪም በ1/503 ዘግበው ሶሒሕ ሲሉት ዘሀቢም ተስማምተውበታል። በ "ሶሒሕ አልጃሚዕ" 1/362 ይመልከቱ።

አሕመድ በአሕመድ ሻኪር አደራደር በቁጥር (513) ዘግበውታል። መጅመዑዝ ዘዋኢድ (1/297) ይመልከቱ። ኢብኑ ሐጀር "ቡሉገል መራም" በሚለው ኪታባቸው ውስጥ ከአቡ ሰዒድ ዘገባ ወደ ነሳኢ [በ "አልኩብራ" ውስጥ] በቁጥር (10617) ያስጠጉት ሲሆን፤ ኢብኑ ሒባን በቁጥር (840) እና ሐኪም (1/541) ላይ ሶሒሕ ብለውታል ብለዋል።

አቡዳውድ በራሱ ቃል (2/81) በቁጥር (1502)፤ ቲርሚዚይ (5/521) በቁጥር (3486) ዘግበውታል፤ "ሶሒሑል ጃሚዕ" (4/271) በቁጥር (4865) ይመልከቱ፤ አልባኒይም በ "ሶሒሕ ሱነን አቡዳውድ" (1/411) ሶሒሕ ብለውታል።

ቡኻሪ ከፈትሕ ጋር (10/ 88) በቁጥር (5623) እና ሙስሊም (3/ 1595) በቁጥር (2012) ዘግበውታል።

ከላይ የተጠቀሰው ዋቢ መጽሐፍ ለአላህ ምስጋና ይድረሰውና ውስጡ የሚገኙ ሐዲሦችን በሰፊው ምንጫቸውን ከመዘርዘር ጋር በአራት ቅፅ ታትሟል። ሒስኑል ሙስሊም በመጀመሪያውና ሁለተኛው ቅፅ ይገኛል።