إِقََامَةُ البَرَاهِينِ عَلَى
حُكْمِ مَنِ اسْتَغَاثَ بِغَيرِ اللهِ
ማስረጃዎችን ማቅረብ ስለ ከአላህ ውጭ እርዳታ የሚጠይቅ ሰው ላይ ያለው የፍርድ ጉዳይ
لِسَمَاحَةِ الشَّيْخِ العَلَّامَةِ
عَبْدِ العَزِيزِ بْنِ عَبْدِ اللهِ بْنِ بَازٍ
رَحِمَهُ اللهُ
ዝግጅት፦ የተከበሩ ሸይኽ
ዐብዱልዐዚዝ ቢን ዐብደላህ ቢን ባዝ
بِسْمِ اللهِ الرَّحمَنِ الرَّحِيمِ
ሁለተኛው መልዕክት፡
ከነቢዩ ﷺ እርዳታ የመፈለግ ብይን
ምስጋና ሁሉ ለአላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላትና ሰላምም በአላህ መልእክተኛ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው እንዲሁም የእርሳቸውን ቅን ጎዳና በተከተለም ላይ ሁሉ ይስፈን።
ከዚህ በመቀጠል፦ የኩዌት አልሙጅተመዕ ጋዜጣ በቁጥር 15፣ በቀን 19/4/1390 ዓ.ሂ. በወጣው እትሟ «የተከበረው የነብዩ መውሊድ መታሰቢያ» በሚል ርዕስ ስር ግጥሞችን አሳትማለች። እነዚህን ግጥሞች ያፀደቀችውም (አሚና) ብላ እራሷን የጠራች ሴት ናት። እነዚህ ግጥሞች ኡማውን ለማዳን፣ ድል ለማድረግና ኡማው ከወደቀበት መለያየትና ልዩነት ነፃ ለማውጣት ነብዩን ﷺ እርዳታ መለመንንና ድልን ከእርሳቸው መጠየቅን ያካተቱ ነበሩ። ከተጠቀሱትም ግጥሞች መካከል የተወሰነው ይህ ነው፦
የአላህ መልክተኛ ሆይ! ጦርነትን የሚያቀጣጥልና በነበልባሉ የሚለበለብ ዓለምን ይታደጉ...
የአላህ መልእክተኛ ሆይ፤ በጥርጣሬ ጨለማ ውስጥ መንከራተቷ የረዘመባትን ኡማ አድኗት...
የአላህ መልእክተኛ ሆይ፤ ራእይዋ በኃዘን ጥልፍልፎሽ የጠፋባትን ህዝብ ይታደጉ፤
እንዲህ እስከምትለው ድረስ
እርዳታውን አፋጥን፤ በበድር ቀን ጌታን በጠራህ ጊዜ እንዳፋጠንከው።
ውርደቱም ወደ ግሩም ድል ተለወጠ፤ ለአላህ የማታያቸው ሰራዊቶች አሉትና።
(ይህች ጸሐፊ፣ ድል በአላህ እጅ ብቻ እንጂ በነቢዩ ﷺ እጅም ሆነ በሌሎች ፍጡራን እጅ አለመሆኑን ረስታ -ወይም ሳታውቅ-፣ ድልን እንዲያፋጥኑና ኡማውን እንዲታደጉ በመጠየቅ ጥሪዋንና የእርዳታ ልመናዋን ወደ መልዕክተኛው ﷺ ታቀርባለች፤ አላህ በግልፅ ቁርአኑ ላይ እንዲህ ብሎ ሳለ:-
﴿...وَمَا النَّصْرُ إِلَّا مِنْ عِنْدِ اللَّهِ الْعَزِيزِ الْحَكِيمِ﴾
{... ድልም አሸናፊና ጥበበኛ ከሆነው ከአላህ ዘንድ ብቻ እንጂ ከሌላ ከማንም የሚገኝ አይደለም::} [አሊ-ዒምራን 126] ክብሩ የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿إِنْ يَنْصُرْكُمُ اللَّهُ فَلَا غَالِبَ لَكُمْ وَإِنْ يَخْذُلْكُمْ فَمَنْ ذَا الَّذِي يَنْصُرُكُمْ مِنْ بَعْدِهِ...﴾
{አላህ ቢረዳችሁ ለእናንተ አሸናፊ የለም:: እርሱ ካዋረዳቸሁ ደግሞ ከእርሱ ማዋረድ በኋላ የሚረዳችሁ ያ ማን ነው?} [አሊ-ዒምራን፡ 160]
ይህ ዱዓ እና እርዳታን መፈለግ ከአምልኮ አይነቶች አንዱን ከአላህ ውጪ ለሆነ አካል መስጠት ነው። ይህ ነገር እንደማይፈቀድ፣ ጥራት የተገባው አላህ ፍጡራንን የፈጠረው እርሱን እንዲያመልኩት እንደሆነ፣ እንዲሁም ይህንኑ አምልኮ እንዲያብራሩና ወደርሱም ጥሪ እንዲያደርጉ መልዕክተኞችን ልኮ መጻሕፍትን እንዳወረደ በግልፅ መረጃና በዑለማዎች ባጠቃላይ የጋራ ስምምነት ይታወቃል። ጥራት የተገባው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنْسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ56﴾
{ጂኒንና ሰዉንም ሊገዙኝ እንጂ ለሌላ አልፈጠርኳቸዉም::} [አዝ-ዛሪያት፡ 56] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِي كُلِّ أُمَّةٍ رَسُولًا أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ وَاجْتَنِبُوا الطَّاغُوتَ...﴾
{በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ አላህን ተገዙ ጣዖትንም ራቁ በማለት መልዕክተኛን በእርግጥ ልከናል...} [አን-ነሕል፡ 36] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿وَمَا أَرْسَلْنَا مِنْ قَبْلِكَ مِنْ رَسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ 25﴾
{ካንተ በፊትም እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢሆን እንጂ ከመልዕክተኛ አንድንም አላክንም።} [አል-አንቢያእ፡ 25] ክብሩ የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿الر كِتَابٌ أُحْكِمَتْ آيَاتُهُ ثُمَّ فُصِّلَتْ مِنْ لَدُنْ حَكِيمٍ خَبِيرٍ1 أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا اللَّهَ إِنَّنِي لَكُمْ مِنْهُ نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ2﴾
{አሊፍ፤ ላም፤ ራ፤ ይህ ቁርኣን አናቅጾቹ በጥንካሬ የተሰካኩ ከዚያም የተዘረዘሩ፤ ጥበበኛና ውስጠ አዋቂ ከሆነው (አምላክ) ዘንድ የተወረደ መጽሐፍ ነው::
(እንዲህ በላቸው) «አላህን እንጂ ሌላን አትገዙ:: እኔ ለእናንተ ከእርሱ ዘንድ የተላኩ አስፈራሪና አብሳሪ ነኝ።» [ሁድ: 1-2]
የላቀው አላህ በእነዚህ ግልፅ አንቀፆች ሰዎችንና ጋኔኖችን የፈጠራቸው ምንም አጋር የሌለውን እርሱን በብቸኝነት እንዲያመልኩት መሆኑን፣ መልዕክተኞቹንም የላከው በዚሁ አምልኮ እንዲያዙና ከተቃራኒው እንዲከለክሉ እንደሆነ፣ እንዲሁም ከእርሱ ውጪ ሌላ አካል እንዳይመለክ የቁርአንን አንቀፆች በማጥራት በዝርዝር እንዳብራራቸውም ግልፅ አድርጓል።
እንደሚታወቀው ዒባዳ (አምልኮ) ማለት፡- አላህን በብቸኝነት ማምለክና ያዘዘውን በመፈጸም እንዲሁም ከከለከለው በመራቅ እርሱን መታዘዝ ነው። አላህም ይህን አስመልክቶ በበርካታ የቁርኣን አንቀጾች ላይ አዟልም ገልጿልም። ከእነዚህም መካከል የሚከተለው የአላህ ንግግር ይገኝበታል፦
﴿وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ حُنَفَاءَ...﴾
{ሃይማኖትን ለአላህ ብቻ አጥሪዎችና ቀጥተኞች ሆነው አላህን ሊገዙት እንጂ ያልታዘዙ ሲሆኑ (ተለያዩ)...} [አል-በይናህ፡ 5] አሸናፊና የበላይ የሆነው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿وَقَضَى رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ...﴾
{ጌታህ እንዲህ ሲል አዘዘ:: እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፤…} [አልኢስራእ: 23] የላቀው አላህ እንዲህም ይላል፦
﴿إِنَّآ أَنزَلۡنَآ إِلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ بِٱلۡحَقِّ فَٱعۡبُدِ ٱللَّهَ مُخۡلِصٗا لَّهُ ٱلدِّينَ2 أَلَا لِلَّهِ ٱلدِّينُ ٱلۡخَالِصُۚ وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ إِنَّ ٱللَّهَ يَحۡكُمُ بَيۡنَهُمۡ فِي مَا هُمۡ فِيهِ يَخۡتَلِفُونَۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي مَنۡ هُوَ كَٰذِبٞ كَفَّارٞ3﴾
{እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት የተሞላ ሲሆን አወረድነው:: አላህንም ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠራህ ሆነህ ተገዛው::
ንቁ! ፍጹም ጥሩ የሆነው ሃይማኖት የአላህ ብቻ ነው:: እነዚያም ከእርሱ ሌላ ጣዖታትን ረዳቶች አድረገው የያዙት «ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቃርቡን እንጂ ለሌላ አንገዛቸዉም።» ይላሉ:: አላህ በዚያ እነርሱ በሚለያዩበት ነገር በመካከላቸው ይፈርዳል:: አላህም ውሸታም ከሓዲ የሆነን ሰው አያቀናም::} [አዝ-ዙመር: 2-3]
ይህንኑ መልዕክት ይዘው የመጡ አንቀፆች በርካታ ናቸው። ሁሉም የሚያመላክቱት በአምልኮ አላህን ብቻ ነጥለን መገዛታችን እና ከእርሱ ውጭ ያሉ ነቢያትንም ሆኑ ሌሎችን ማምለክን መተው ግዴታ መሆኑን ነው።
ዱዓእ ከታላላቅና ሁሉን አቃፊ ከሆኑ የአምልኮ አይነቶች መካከል አንዱ በመሆኑ ለአላህ ብቻ ጥርት ተደርጎ መፈፀሙ ግዴታ ነው። አሸናፊና የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፡-
﴿فَادْعُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ14﴾
{አላህንም ከሓዲዎች ቢጠሉም (እንኳ) ሃይማኖትን ለእርሱ አጥሪዎች ሆናችሁ ተገዙ::} [ጋፊር፡ 14] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿وَأَنَّ الْمَسَاجِدَ لِلَّهِ فَلَا تَدْعُوا مَعَ اللَّهِ أَحَدًا18﴾
{ እነሆ መስጊዶችም የአላህ ብቻ ናቸው:: በውስጣቸው ከአላህ ጋር አንድንም አትገዙ ማለትን ተወረደልኝ::} [አል_ጂን፡ 18] ይህ አላህን በዱዓእ ብቸኛ የማድረግ መመሪያ ነቢያትንም ሆነ ሌሎችን ፍጡራን ሁሉ ያጠቃልላል፤ የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿وَلَا تَدْعُ مِنْ دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَنْفَعُكَ وَلَا يَضُرُّكَ فَإِن فَعَلۡتَ فَإِنَّكَ إِذٗا مِّنَ ٱلظَّٰلِمِينَ106﴾
{«ከአላህም በቀር የማይጠቅምህንና የማይጎዳህን አትገዛ:: ይህን ብትሠራ ያን ጊዜ አንተ ከበደለኞቹ ትሆናለህ» (ተብያለሁ በላቸው)።} [ዩኑስ፡ 106] ይህም ለነቢዩ ﷺ የተላለፈ ንግግር ሲሆን፤ አላህ እርሳቸውን ከሽርክ መጠበቁ የታወቀ ነው። ከዚህ የተፈለገበት ዓላማ ግን እርሳቸውን ሳይሆን ሌሎችን ለማስጠንቀቅ ነው። የላቀው አላህ እንዲህ አለ፡
﴿وَلَا تَدۡعُ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَنفَعُكَ وَلَا يَضُرُّكَ فَإِنْ فَعَلْتَ فَإِنَّكَ إِذًا مِنَ الظَّالِمِينَ106﴾
{«ከአላህ በስተቀር የማይጠቅምህንና የማይጎህዳን አትገዛ:: ይህን ብትሠራ ያን ጊዜ አንተ ከበደለኞቹ ትሆናለህ» (ተብያለሁ በላቸው)።} [ዩኑስ፡ 106] ይህ ለነቢዩ ﷺ የቀረበ ንግግር ሲሆን፥ የተፈለገበትም ከእርሳቸው ውጭ ያሉ ሌሎችን ማስጠንቀቅ ነው፤ ምክንያቱም አላህ (ሱብሃነሁ ወተዓላ) መልዕክተኛውን ከሽርክ መጠበቁ የታወቀ ነው። ከዚያም አላህ ክልከላውንና ማስጠንቀቂያውን በማጠናከር እንዲህ አለ፦
﴿...فَإِنْ فَعَلْتَ فَإِنَّكَ إِذًا مِنَ الظَّالِمِينَ﴾
{«ይህን ብትሠራ ግን ያን ጊዜ ከበደለኞቹ ትሆናለህ»…} በደል በደፈናው ሲጠቀስ የሚፈለግበት፡ ትልቁ ሺርክ ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፡-
﴿...وَالْكَافِرُونَ هُمُ الظَّالِمُونَ﴾
{…ከሃዲዎችም በዳዮቹ እነርሱ ናቸው።} [አልበቀራህ፡ 254] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿...إِنَّ الشِّرْكَ لَظُلْمٌ عَظِيمٌ﴾
{…ማጋራት ታላቅ በደል ነውና።} [ሉቅማን: 13] የአደም ልጆች ሁሉ አለቃ የሆኑት ﷺ እርሳቸው እንኳ ከአላህ ውጭ ሌላን ቢጣሩ ከበዳዮች የሚመደቡ ከሆኑ ሌላው እንዴት ሊሆን ነው?
ከነዚህና ከሌሎችም አንቀፆች ያወቅነው ነገር ቢኖር ከአላህ ውጭ ያለን አካል — ሙታንን፣ ዛፎችን፣ ጣዖታትንና የመሳሰሉትን — መማፀን በላቀው አላህ ላይ ሽርክ (ማጋራት) እንደሆነ ነው። ይህ ድርጊት አላህ ሰዎችንና ጂኖችን የፈጠረበት፣ መልክተኞችን የላከበትና መጽሐፍትን ያወረደበት አላማ የሆነውን በአምልኮ አላህን መነጠልን (ተውሒድን) የሚፃረርና፤ ከአላህ ውጭ ላለ አካል አምልኮን ውድቅ በማድረግ ለአላህ ብቻ የምታፀድቅ የሆነችውን የ«ላ ኢላሀ ኢለላህ»ን ትርጉምም የሚጋጭ ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿ذَٰلِكَ بِأَنَّ ٱللَّهَ هُوَ ٱلۡحَقُّ وَأَنَّ مَا يَدۡعُونَ مِن دُونِهِۦ هُوَ ٱلۡبَٰطِلُ وَأَنَّ ٱللَّهَ هُوَ ٱلۡعَلِيُّ ٱلۡكَبِيرُ62﴾
{ይህ አላህ ፍፁም እውነት በመሆኑ፤ ከርሱም ሌላ የሚገዙት ነገር ፍጹም ውሸት በመሆኑና አላህም የሁሉ በላይ ታላቅ በመሆኑ ነው::} [አል'ሐጅ፡ 62]
ይህም የሃይማኖቱ መሰረት እና የሃይማኖቱም ምሰሶ ነው፤ አምልኮዎችም ትክክል የሚሆኑት ይህ መሰረት ትክክለኛ ከሆነ በኋላ ነው። የበላይ የሆነው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَلَقَدْ أُوحِيَ إِلَيْكَ وَإِلَى الَّذِينَ مِنْ قَبْلِكَ لَئِنْ أَشْرَكْتَ لَيَحْبَطَنَّ عَمَلُكَ وَلَتَكُونَنَّ مِنَ الْخَاسِرِينَ65﴾
{(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ብታጋራ ስራህ በእርግጥ ይታበሳል:: በእርግጥም ከከሓዲያን ትሆናለህ በማለት ወደ አንተና እነዚያ ካንተ በፊት ወደ ነበሩት በእርግጥ ተወርዷል::} [አዝ-ዙመር፡ 65] ጥራት የተገባውና የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿...وَلَوْ أَشْرَكُوا لَحَبِطَ عَنْهُمْ مَا كَانُوا يَعْمَلُونَ﴾
{…በአላህ ባጋሩም ኖሮ ይሰሩት የነበሩት መልካም ተግባር ሁሉ ከእነርሱ በታበሰባቸው ነበር::} [አልአንዓም፡ 88]
ቀደም ብለን ካብራራነው የእስልምና ሃይማኖትና ‹ላ ኢላሃ ኢለላህ› የምትለዋ የምስክርነት ቃል ሁለት ታላላቅ መሰረቶች እንዳላቸው እንረዳለን፦
አንደኛው፡ አላህ ብቻውን ሊመለክና በርሱ ላይ ምንም ነገር ላይጋራበት ነው። ስለዚህ ከነብያትም ሆነ ከሌሎች ሙታንን የለመነ፣ ወይም ጣዖታትን፣ ዛፎችን፣ ድንጋዮችን ወይም ሌሎች ፍጡራንን የለመነ፣ ወይም በእነርሱ እርዳታ የጠየቀ፣ ወይም በእርድና በስለት ወደ እነርሱ የተቃረበ፣ ወይም ለነርሱ የሰገደ ሰው በእርግጥ ከአላህ ውጭ ጌቶች አድርጓቸዋል ለእርሱ ባላንጣዎችም አድርጓቸዋል። የላ ኢላሃ ኢለሏህንም ትርጉም ተፃርሯል ውድቅም አድርጓል።
ሁለተኛው: ከፍ ያለው አላህን በመልዕክተኛው ﷺ ሸሪዓ እንጂ በሌላ አለማምለክ ነው። በሃይማኖት ውስጥ አላህ ያልፈቀደውን አዲስ ነገር የፈጠረ ሰው ሙሐመድ የአላህ መልዕክተኛ የመሆናቸውን የምስክርነት ቃል ፅንሰ ሃሳብ አላረጋገጠም፤ ስራውም አይጠቅመውም፤ ከእርሱም ተቀባይነት አይኖረውም። ታላቅነትና ክብር የተገባው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَقَدِمْنَا إِلَى مَا عَمِلُوا مِنْ عَمَلٍ فَجَعَلْنَاهُ هَبَاءً مَنْثُورًا23﴾
{ከስራም ወደ ሰሩት እናስባለን:: የተበተነ ትቢያም እናደርገዋለን::} [አልፉርቃን: 23] በአንቀጹ ውስጥ ስራዎች በማለት የተፈለገው በአላህ ላይ በማጋራት የሞተ ሰው ስራዎች ናቸው።
በተጨማሪም አላህ ያልፈቀዳቸው የቢድዓ ስራዎችም እዚህ ውስጥ ይካተታሉ። የቢድዓ ስራዎች ንፁህ ከሆነው የአላህ ሸሪዓ ጋር ባለመግጠማቸው በትንሳኤው ቀን የተበታተነ ትቢያ ይሆናሉ። ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
«مَنْ أَحْدَثَ فِي أَمْرِنَا هَذَا مَا لَيْسَ مِنْهُ فَهُوَ رَدٌّ».
"በዚህ ሃይማኖታችን ውስጥ ከእርሱ ያልሆነን አዲስ ነገር ያመጣ ይዞት የመጣው አዲስ መጤ ነገር ውድቅ ነው።" ሶሒሕ በመሆኑ ላይ ተስማምተውበታል።
ነገሩን ስናጠቃልልም: ይህች ጸሐፊ የይድረሱልኝ ጥሪዋንና ዱዓዋን ለረሱል ﷺ እንዳቀረበች፤ ከእነዚህ ነገሮች መካከል አንዳቸውም ከእርሱ ውጭ ከማንም እጅ የማይገኝ ከሆነው፣ ድል ሰጪ ከሆነው፣ ጉዳትና ጥቅም በእጁ ከሆነው የዓለማት ጌታ ጀርባዋን መስጠቷ ነው።
ይህ ታላቅና ከባድ በደል መሆኑ ምንም ጥርጥር የለውም። ከፍ ያለው አላህ እርሱን እንዲለምኑት አዟል፤ የሚለምኑትንም እንደሚቀበላቸው ቃል ገብቷል። ከዚህ የሚኮሩትንም ጀሀነም እንደሚያስገባቸው በዛቻ አስጠንቅቋል፤ ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ብሏል፡
﴿وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ 60﴾
{ጌታችሁም አለ: «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና። እነዚያ እኔን ከመገዛት የሚኮሩት ተዋራጆች ሆነው ገሀነም በእርግጥ ይገባሉ።»} (ጋፊር፡60) ማለትም፡ የተዋረዱና የተናቁ ሆነው ጀሃነም ይገባሉ። ይህች የተከበረች አንቀፅ ዱዓእ አምልኮ መሆኑንና ከእርሱ የሚኮራ ሰው መዳረሻው ጀሀነም መሆኑን ታስረዳለች። አላህን ከመለመን የተኩራራ ሰው ፍፃሜው ይህ ከሆነ፤ አላህ ጥራት የተገባው ቅርብ፣ የሁሉም ነገር ባለቤትና በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ሆኖ ሳለ ከእርሱ ፊቱን አዙሮ ሌላን የለመነ ሰው ሁኔታው እንዴት ሊሆን ነው? ጥራት የተገባው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ فَلْيَسْتَجِيبُوا لِي وَلْيُؤْمِنُوا بِي لَعَلَّهُمْ يَرْشُدُونَ 186﴾
{ባሮቼም ስለ እኔ በጠየቁህ ጊዜ እኔ ቅርብ ነኝ:: የለማኝን ጸሎትም በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ:: ስለዚህ ለእኔ ይታዘዙ፤ በእኔም ይመኑ፤ እነሱ ሊመሩ ይከጀላልና። (በላቸው።)} (አል'በቀራህ፡186) ረሱል ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም በሶሒሕ ሐዲሣቸው ዱዓእ አምልኮ እንደሆነ ተናግረዋል። እንዲሁም ለአጎታቸው ልጅ ለዐብደላህ ኢብኑ ዐባስ ረዲየላሁ ዐንሁማ እንዲህ ብለዋል፡-
«احْفَظِ اللهَ يَحْفَظْكَ، احْفَظِ اللهَ تَجِدْهُ تُجَاهَكَ، إِذَا سَأَلْتَ فَاسْأَلِ اللهَ، وَإِذَا اسْتَعْنَتَ فَاسْتَعِنْ بِاللهِ».
"የአላህን ትእዛዝና ክልከላ ጠብቅ አላህ ይጠብቅሃል። የአላህን ትእዛዝና ክልከላ ጠብቅ ከፊትህ ታገኘዋለህ። ማንኛውንም ነገር ስትለምን ከአላህ ዘንድ ለምን፤ እርዳታ ከፈለግክም በአላህ ታገዝ።" ቲርሚዚይና ሌሎችም ዘግበውታል።
ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፡
«مَنْ مَاتَ وَهُوَ يَدْعُو لِلَّهِ نِدًّا؛ دَخَلَ النَّارَ».
«ከአላህ ውጭ ሌላን እየተጣራ የሞተ ሰው እሳት ገባ።» ቡኻሪ ዘግበውታል። በሶሒሕ ቡኻሪና ሙስሊም እንደተዘገበው ነብዩ ﷺ ‹እጅግ ትልቁ ወንጀል ምንድነው?› ተብለው ተጠይቀው እንዲህ አሉ፦
«أَنْ تَجْعَلَ لِلَّهِ نِدًّا وَهُوَ خَلَقَكَ».
«አላህ ፈጥሮህ ሳለ፤ ለአላህ ቢጤ ማድረግህ ነው፡፡» "ኒድ" ማለት አቻና አምሳያ ማለት ነው። ስለዚህም ነብይንም፣ ወልይንም፣ መልአክንም፣ ጂንንም፣ ጣዖትንም ሆነ ወይም ከዚህ ውጭ ያለን ሌላ ፍጡር ከአላህ ውጭ የተጣራ፣ የድረሱልኝ ጥሪ ያቀረበ፣ ስለት የተሳለለት፣ እርድ ያረደለት ወይም ከነዚህ ውጭ የሆነ ማንኛውንም የአምልኮ አይነት ለእርሱ የፈፀመ ማንም ቢሆን በእርግጥም ይህንን አካል (ለአላህ) ኒድ አድርጎ ይዞታል።
እዚህ ላይ አንድ ሰው እንዲህ የሚል ጥያቄ ሊያነሳ ይችላል፦ በህይወት ያለንና በቦታው ላይ የሚገኝን ሰው ሊያሳካልን የሚችለውን ነገር መጠየቅና አቅሙ የሚፈቅድለትን ህዋሳዊ (ተጨባጭ) ጉዳይ እንዲያግዘን በእርሱ መታገዝስ ብይኑ ምንድን ነው? መልሱም፦ ይህ ከሽርክ የሚመደብ አይደለም፤ ይልቁንም በሙስሊሞች መካከል የተፈቀዱ እና የተለመዱ ከሆኑ ጉዳዮች መካከል ነው። አላህ ስለ ሙሳ ሲተርክ እንዲህ ብሏል፦
﴿...فَاسْتَغَاثَهُ الَّذِي مِنْ شِيعَتِهِ عَلَى الَّذِي مِنْ عَدُوِّهِ...﴾
{…ያም ከወገኑ የሆነው ሰው በዚያ ከጠላት በሆነው ሰው ላይ እርዳታን ጠየቀው…} [አል-ቀሶስ፡ 15] በተመሳሳይ በሌላ አንቀፅ አላህ ስለ ሙሳ ሲተርክ እንዲህ ብሏል፦
﴿فَخَرَجَ مِنْهَا خَائِفًا يَتَرَقَّبُ...﴾
{የፈራና የሚጠባበቅ ሆኖም ከእርሷ ወጣ...} [አል-ቀሶስ፡ 21] አንድ ሰው እንደ ጦርነትና መሰል ሰዎችን የሚያጋጥሟቸው አደጋዎች ሲከሰቱበት እርስ በርስ ስለሚፈላለጉ ከጓዶቹ እርዳታን መማፀኑ እንደተጨማሪ ምሳሌ ይጠቀሳል።
አላህም ነቢዩን ﷺ ለማንም ሰው ጥቅምና ጉዳት ማምጣት እንደማይችሉ ለኡመታቸው እንዲነግሩ አዟል። አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿قُلْ إِنَّمَا أَدْعُو رَبِّي وَلَا أُشْرِكُ بِهِ أَحَدًا21 قُلْ إِنِّي لَا أَمْلِكُ لَكُمْ ضَرًّا وَلَا رَشَدًا22﴾
{«እኔ የማመልከው ጌታየን ብቻ ነው:: በእርሱም አንድንም አላጋራም» በል።
«እኔ ለእናንተ ጉዳትንም ሆነ ማቅናትን አልችልም» በላቸው።} [አል-ጂን: 20-21] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿قُلْ لَا أَمْلِكُ لِنَفْسِي نَفْعًا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ وَلَوْ كُنْتُ أَعْلَمُ الْغَيْبَ لَاسْتَكْثَرْتُ مِنَ الْخَيْرِ وَمَا مَسَّنِيَ السُّوءُ إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ لِقَوْمٍ يُؤْمِنُونَ188﴾
{«አላህ የሻዉን በስተቀር ለራሴ ጥቅምንም ሆነ ጉዳት ማምጣት አልችልም:: የሩቅን ሚስጥር የማውቅ በነበርኩ ኖሮ ከመልካም ነገር ሁሉ ባበዛሁና ክፉም ነገር ባልነካኝ ነበር:: እኔም ለሚያምኑ ህዝቦች ሁሉ አስፈራሪና አብሳሪ እንጂ ሌላ አይደለሁም።» በላቸው::} [አል'አዕራፍ: 188]
ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው ቁርአናዊ ማስረጃዎች በርካታ ናቸው።
እንደሚታወቀው ነቢዩ ﷺ ከጌታቸው በቀር አይማፀኑም ነበር። ከእርሳቸው እንደተረጋገጠውም በበድር ቀን አላህን እርዳታ ጠይቀው ነበር፣ በጠላታቸው ላይ ድልን እንዲያጎናፅፋቸው ይማፀኑት ነበር። አስ-ሲዲቁል አክበር አቡበክር (አላህ መልካም ሥራውን ይውደድለትና) «የአላህ መልእክተኛ ሆይ ይበቃዎታል፤ አላህ የገባልህን ቃል ፈጻሚ ነው» እስከሚላቸውም ድረስ «ጌታዬ ሆይ! የገባህልኝን ቃል ሙላልኝ» እያሉ አጥብቀው ይለምኑ ነበር። የላቀው አላህም በዚያን ጊዜ እንዲህ ሲል ንግግሩን አወረደ፦
﴿إِذۡ تَسۡتَغِيثُونَ رَبَّكُمۡ فَٱسۡتَجَابَ لَكُمۡ أَنِّي مُمِدُّكُم بِأَلۡفٖ مِّنَ ٱلۡمَلَٰٓئِكَةِ مُرۡدِفِينَ9﴾
{ከጌታችሁ እርዳታን በፈለጋችሁ ጊዜ «እኔ በሺህ መላዕክት ተከታታዮች ሲሆኑ እረዳችኋለሁ።» ሲል ለእናንተ የተቀበላችሁን አስታውሱ።} [አል-አንፋል: 9] ጥራት የተገባው ጌታ በእነዚህ አንቀጾች ሙስሊሞች እርዳታን መፈለጋቸውን አስታውሷቸዋል፡፡ ለእነርሱም እንደተቀበላቸውና ድልን ለማበሰርና እርጋታን ለመስጠትም በመላእክት እንደረዳቸው አሳውቋል፡፡ ድሉ ከመላእክት ሳይሆን ከእርሱ ዘንድ ብቻ መሆኑንም አብራርቷል፡፡ ከፍ ያለው ጌታም እንዲህ አለ፡-
﴿وَمَا النَّصْرُ إِلَّا مِنْ عِنْدِ اللَّهِ...﴾
{ድልም ከአላህ ዘንድ ብቻ ነው...} [አሊ-ዒምራን፡ 126] የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَلَقَدْ نَصَرَكُمُ اللَّهُ بِبَدْرٍ وَأَنْتُمْ أَذِلَّةٌ فَاتَّقُوا اللَّهَ لَعَلَّكُمْ تَشْكُرُونَ123﴾
{በበድርም እናንተ ጥቂቶች ሆናችሁ ሳለ አላህ በእርግጥ ረዳችሁ:: አላህን ታመሰግኑ ዘንድ ፍሩት::} [አሊ-ዒምራን፡ 123] ከፍ ያለው አላህ በበድር ቀን ረዳታቸው እርሱ መሆኑን በዚህች አንቀጽ አብራርቷል፡፡ በዚህም የሰጣቸው የጦር መሣሪያና ኃይል፣ እንዲሁም በመላእክት ያገዛቸውም እገዛ፣ ይህ ሁሉ ለድል፣ ለብስራትና ለልብ እርካታ ሰበቦች ብቻ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ድል ማድረግን የሚሰጡት ግን እነዚህ ሰበቦች አይደሉም፤ ይልቁንም ድል አድራጊነት ከአላህ ዘንድ ብቻ ነው፡፡ ይህቺ ፀሐፊ ወይም መሰሎቿ፣ የሁሉም ነገር ባለቤትና በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ከሆነው ከዓለማቱ ጌታ ፊታቸውን አዙረው፣ እንዴት ደፍረው ነው የእርዳታ ጥሪያቸውንና የድል ልመናቸውን ወደ ነቢዩ (ሶለሏሁ ዐለይሂ ወሰለም) የሚያቀርቡት?
ይህ ምንም ጥርጥር የሌለው እጅግ አስፀያፊ መሃይምነት ነው፤ ይልቁንም ከባባድ ከሆኑ የሽርክ አይነቶች ነው። በመሆኑም ጸሐፊዋ ወደ አላህ (ሱብሃነሁ) ተጸጽታ በንጹህ ተውበት መመለስ ይኖርባታል። ንጹህ ተውበት የሚባለው ደግሞ በርካታ ጉዳዮችን ያካተተ ሲሆን እነሱም፥ የመጀመሪያው: በፈጸመችው ነገር መጸጸት ነው። ሁለተኛው፡ ከተፈፀመው ወንጀል መላቀቅ ነው። ሶስተኛው: አላህን በማላቅ፣ ለእርሱም ጥርት በማድረግ፣ ትዕዛዙንም በመፈጸምና ከከለከለው ነገር በመጠንቀቅ ወደ ወንጀሉ ላለመመለስ መወሰን ነው፤ እውነተኛ ተውበት (ንስሀ) የሚባለው ይህ ነው። አራተኛው ደግሞ ወንጀሉ ከፍጡራን ሐቅ ጋር የተያያዘ ከሆነ ሐቁን ለባለቤቱ መመለስ ወይም ይቅርታውን መጠየቅ ነው።
አላህ ባሮቹን ተውበት እንዲያደርጉ አዟቸዋል፤ እንደሚቀበላቸውም ቃል ገብቶላቸዋል፤ የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿...وَتُوبُوا إِلَى اللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ الْمُؤْمِنُونَ لَعَلَّكُمْ تُفْلِحُونَ﴾
{ምዕመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ በመመለስ ተጸጸቱ::} (አን-ኑር 31) ክርስትያኖችንም አስመልክቶ እንዲህ ብሏል፦
﴿أَفَلَا يَتُوبُونَ إِلَى اللَّهِ وَيَسْتَغْفِرُونَهُ وَاللَّهُ غَفُورٌ رَحِيمٌ74﴾
{ወደ አላህ አይመለሱምና ምህረትን አይለምኑትምን? አላህም መሀሪና አዛኝ ነው::} [አል-ማኢዳህ: 74] ጥራት ይገባውና እንዲህም ብሏል፡
﴿وَالَّذِينَ لَا يَدْعُونَ مَعَ اللَّهِ إِلَهًا آخَرَ وَلَا يَقْتُلُونَ النَّفْسَ الَّتِي حَرَّمَ اللَّهُ إِلَّا بِالْحَقِّ وَلَا يَزْنُونَ وَمَنْ يَفْعَلْ ذَلِكَ يَلْقَ أَثَامًا68 يُضَاعَفْ لَهُ الْعَذَابُ يَوْمَ الْقِيَامَةِ وَيَخْلُدْ فِيهِ مُهَانًا69 إِلَّا مَنْ تَابَ وَآمَنَ وَعَمِلَ عَمَلًا صَالِحًا فَأُولَئِكَ يُبَدِّلُ اللَّهُ سَيِّئَاتِهِمْ حَسَنَاتٍ وَكَانَ اللَّهُ غَفُورًا رَحِيمًا70﴾
{ እነዚያም ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማይገዙት፤ ያችንም አላህ እርም ያደርጋትን ነፍስ ያለ ህግ የማይገድሉ እና የማያመነዝሩት ናቸው:: ይህንንም የሚፈጽም ሰው ቅጣትን ያገኛል::
በትንሳኤ ቀን ቅጣቱ ይደራረብበታል:: በእርሱም ውስጥ የተዋረደ ሆኖ ዘላለሙን ይኖራል::
ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ስራ የሰራ ሰው ብቻ ሲቀር እነዚያም አላህ መጥፎ ስራዎቻቸውን በመልካም ስራዎች ይለውጣል:: አላህም እጅግ መሓሪና አዛኝ ነው::} [አል-ፉርቃን፡ 68-70] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿وَهُوَ الَّذِي يَقْبَلُ التَّوْبَةَ عَنْ عِبَادِهِ وَيَعْفُو عَنِ السَّيِّئَاتِ وَيَعْلَمُ مَا تَفْعَلُونَ25﴾
{እርሱም ያ ከባሮቹ ንስሓን የሚቀበል፣ ከኃጢአቶችም ይቅር የሚል የምትሰሩትንም ሁሉ የሚያውቅ ነው።} [አሽ-ሹራ: 25]
የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ማለታቸውም በሶሒሕ ሐዲሥ ተዘግቧል፡-
«الإِسْلَامُ يَهْدِمُ مَا كَانَ قَبْلَهُ، وَالتَّوْبَةُ تَجُبُّ مَا كَانَ قَبْلَهَا».
«ኢስላም ከእርሱ በፊት የነበረውን (ወንጀል) ያስምራል፤ ንስሐም ከእርሷ በፊት የነበረውን ወንጀል ታስሰርዛለች።»
የሽርክ አደገኝነት ታላቅ በመሆኑ፣ ከወንጀሎችም ሁሉ የከፋ በመሆኑ፣ ከዚህች ፀሐፊ የወጣው ጽሑፍ ሰዎችን እንዳይሸውድ በመስጋት፣ እንዲሁም ለአላህና ለባሮቹ መቆርቆር እና ታማኝ መሆን ግዴታ በመሆኑ፤ ይህችን አጠር ያለች መልዕክት አዘጋጅቻለሁ። ታላቅና የላቀ የሆነውን አላህ በእርሷ ተጠቃሚ እንዲያደርገን፤ የእኛንም ሆነ የመላው ሙስሊሞችን ጉዳይ እንዲያበጅልን፤ ሁላችንንም በዲን ላይ ግንዛቤንና በርሱም ላይ ፅናትን እንዲለግሰን፤ እኛንም ሆነ ሙስሊሞችን ከነፍሶቻችን ክፋትና ከመጥፎ ስራዎቻችን እንዲታደገን እማፀነዋለሁ። እነሆ እርሱ ለዚህ ተማፅኖ የተገባ እውን ሊያደርገው ቻይም ነውና።
የአላህ ሰላት፣ ሰላምና በረከት ባሪያውና መልዕክተኛው በሆኑት በነብያችን ሙሐመድ እንዲሁም በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ይስፈን።
***
بِسْمِ اللهِ الرَّحمَنِ الرَّحِيمِ
ሦስተኛው መልዕክት:
ጂኒዎችና ሰይጣናትን እርዳታን መለመንና ለእነርሱ ስለት መግባት ያለው ብይን:-
ከዐብዱልዐዚዝ ቢን ዐብደላህ ቢን ባዝ ይህንን መልዕክት ለሚያይ ሙስሊም ባጠቃላይ የተላለፈ መልዕክት: አላህ እኔንም እነርሱንም ሃይማኖቱን አጥብቀን ለመያዝና በርሱ ላይ ለመጽናት ይግጠመን! አሚን።
አስሰላሙ ዐለይኩም ወረሕመቱሏሂ ወበረካቱህ
ከዚህ በመቀጠል፥ አንድ ወንድም አንዳንድ መሃይማን ስለሚፈፅሙት ድርጊት ጠየቀኝ፤ ይኸውም ከአላህ (ሱብሓነሁ) ውጪ ያለን አካል መለመን፣ በአሳሳቢ ጉዳዮች ላይ ከእርሱ እርዳታ መፈለግ፤ ለምሳሌ ጂንን መለመን፣ ከእነርሱ እርዳታን መፈለግ፣ ለእነርሱ ስለት መግባትና ለእነርሱ እርድ ማቅረብ ያሉትን በተመለከተ ነው። ከዚህ ጋርም ተያይዞ የአንዳንዶች እንዲህ የሚል ንግግር ይጠቀሳል፦ «ያ ሰብዓህ (ማለትም ሰባቱ የጂን መሪዎች ሆይ!) ውሰዱት፤ አጥንቱን ስበሩት፤ ደሙን ጠጡ፤ አካሉን አበላሹት፤ እናንተ ሰባቶች ሆይ! እንዲህ እንዲህ አድርጉት።» ወይም አንዳንዶች፡ «የቀትር ጅኖች ሆይ፣ የአስር ጅኖች ሆይ ውሰዱት» የሚለው ንግግር፤ ይህም በአንዳንድ ደቡባዊ አካባቢዎች በብዛት ይገኛል። ነብያትን፣ ደጋጎችንና ሌሎች ሙታንን መለመን፣ እንዲሁም መላኢካዎችን መለመንና ከነርሱ እርዳታ መፈለግም እዚህ ርዕስ ውስጥ ከሚካተቱት መካከል ነው፦ ይህ ሁሉና መሰሎቹ ወደ እስልምና የሚጠጉ ብዙ ሰዎች ባለማወቅና ቀዳሚዎቻቸውን በመከተል የሚፈፅሙት ነው። ምናልባትም አንዳንዶቻቸው በዚህ ጉዳይ ላይ በማቅለል እንዲህ ሲሉ ይሞግታሉ፡- «ይህ በምላስ ላይ እንዲሁ የሚባል ነገር እንጂ የምንፈልገውም ሆነ የምናምንበት አይደለም።»
እነዚህን ስራዎች በመስራት የሚታወቁ ሰዎችን ስለማግባት፣ እርዳቸውን ስለመብላት፣ በነርሱ ጀናዛ ላይ ስለመስገድና ከኋላቸው ተከትሎ ስለመስገድ ስላለው ኢስላማዊ ፍርድ፤ እንዲሁም ከታካሚው ሰውነት ጋር የተነካካን ነገር እንደ ጥምጣም፣ ሱሪ፣ ሻሽ እና መሰል ነገሮችን ብቻ በማየት የበሽታውን አይነትና መንስኤውን እናውቃለን ብለው በሚሞግቱ አጭበርባሪዎችና ሟርተኞች ስለማመንም ጨምሮ ጠይቆኛል።
መልሱም፦ ምስጋና ሁሉ ለብቸኛው አላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላትና ሰላም ከእሳቸው በኋላ ነብይ በሌለ በሆኑት ነብይ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸውም እንዲሁም እስከ ዕለተ ፍርድ ድረስ የእነርሱን ቅን ጎዳና በተከተሉትም ላይ ሁሉ ይስፈን።
ከዚህ በመቀጠል፦ ጥራት የተገባውና ከፍ ያለው አላህ ሰውንና ጋኔኖችን የፈጠረው ከእርሱ ውጪ ያለን ነገር ሁሉ ትተው እርሱን በብቸኝነት እንዲያመልኩት፤ እንዲሁም ዱዓእን፣ እርዳታ መፈለግን፣ እርድን፣ ስለትንና ሌሎች የአምልኮ ዓይነቶችን በሙሉ ለእርሱ ብቻ እንዲያደርጉ ነው። መልዕክተኞችንም የላከውና ያዘዛቸውም ለዚሁ ነው። ታላቁ የሆነውን የተከበረውን ቁርአን ጨምሮ መለኮታዊ መጽሐፍትን ያወረደው ይህንኑ ጉዳይ እንዲያብራሩና ወደርሱም ጥሪ እንዲያደርጉ፣ ሰዎችንም በአላህ ከማጋራትና ከእርሱ ሌላ ያለን አካል ከማምለክ እንዲያስጠነቅቁ ነው። ይህ የመሠረቶች ሁሉ መሠረት እንዲሁም የሃይማኖትና እምነት መሠረት ነው። ይህም የምስክር ቃል የሆነችው የ “ላ ኢላሃ ኢለሏህ” ፅንሰ ሃሳብ ሲሆን “ከአላህ በስተቀር በእውነት አምልኮ የሚገባው ሌላ አምላክ የለም” የሚለው ማረጋገጫም ነው። ላኢላሃ ኢለሏህ ከአላህ ውጭ ላለ ነገር ተመላኪነትንና አምልኮን ውድቅ ታደርጋለች፤ ይህንኑ አምልኮ ከእርሱ ውጭ ካሉ ፍጥረታት ሁሉ በመነጠል ለአላህ ብቻ መሆኑን ታጸድቃለች። በዚህ ዙሪያ ከቁርአንና ከመልዕክተኛው ﷺ ሱና የተገኙ ማስረጃዎች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ከእነዚህም መካከል ልዕልናው የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنْسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ56﴾
{ጂኒንና ሰዉንም ሊገዙኝ እንጂ ለሌላ አልፈጠርኳቸዉም::} [አዝ-ዛሪያት፡ 56] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿وَقَضَى رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ...﴾
{ጌታህም እንዲህ ሲል አዘዘ:: እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ።} [አልኢስራእ፡23] አላህ እንዲህም ብሏል:
﴿وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ حُنَفَاءَ...﴾
{ሃይማኖትን ለአላህ ብቻ አጥሪዎችና ቀጥተኞች ሆነው አላህን ሊገዙት እንጂ ያልታዘዙ ሲሆኑ (ተለያዩ)} [አል-በይናህ፡ 5] አላህ እንዲህም ብሏል:
﴿وَقَالَ رَبُّكُمُ ادْعُونِي أَسْتَجِبْ لَكُمْ إِنَّ الَّذِينَ يَسْتَكْبِرُونَ عَنْ عِبَادَتِي سَيَدْخُلُونَ جَهَنَّمَ دَاخِرِينَ60﴾
{ጌታችሁም አለ: «ለምኑኝ እቀበላችኋለሁና። እነዚያ እኔን ከመገዛት የሚኮሩት ተዋራጆች ሆነው ገሀነም በእርግጥ ይገባሉ።»} [ጋፊር፡ 60] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿وَإِذَا سَأَلَكَ عِبَادِي عَنِّي فَإِنِّي قَرِيبٌ أُجِيبُ دَعْوَةَ الدَّاعِ إِذَا دَعَانِ...﴾
{ባሮቼም ስለ እኔ በጠየቁህ ጊዜ (እንዲህ በላቸው) እኔ ቅርብ ነኝ:: የለማኝን ጸሎትም በለመነኝ ጊዜ እቀበለዋለሁ...} [አልበቀራህ: 186]
ጥራት የተገባው አምላክ ሰውንና ጋኔንን የፈጠራቸው እርሱን እንዲያመልኩት መሆኑን፣ እንዲሁም በተብራራው ቁርኣኑና በመልዕክተኛውም ﷺ አንደበት አማካኝነት ከጌታቸው በስተቀር ሌላን እንዳያመልኩ በባሮቹ ላይ የደነገገ መሆኑን በእነዚህ አንቀጾች አብራርቷል።
የላቀውና ከፍ ያለው አላህ ዱዓእ ታላቅ አምልኮ መሆኑንና ከእርሱ የኮራ ሰው እሳት እንደሚገባ አብራርቷል። ባርያዎቹንም እርሱን ብቻ እንዲለምኑት አዟል፤ እርሱም ቅርብ መሆኑንና ልመናቸውንም እንደሚቀበል አሳውቋል። በመሆኑም በሁሉም ባርያዎች ላይ ጌታቸውን ብቻ በዱዓእ የመለመን ግዴታ አለባቸው፤ ምክንያቱም (ዱዓእ) ከተፈጠሩበትና ከታዘዙበት የአምልኮ አይነት ነውና። የላቀውና ከፍ ያለው አላህም እንዲህ ብሏል፦
﴿قُلْ إِنَّ صَلَاتِي وَنُسُكِي وَمَحْيَايَ وَمَمَاتِي لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ162 لَا شَرِيكَ لَهُ وَبِذَلِكَ أُمِرْتُ وَأَنَا أَوَّلُ الْمُسْلِمِينَ163﴾
{ «ስግደቴ፤ መገዛቴም፣ ሕይወቴም፤ ሞቴም ለዓለማት ጌታ ለሆነው ለአላህ ብቻ ነው።
ለእርሱ (ለአላህ) አጋር የለዉም:: በዚህም (አላህን ከተጋሪ በማጥራት) ታዘዝኩ:: እኔም የሙስሊሞች መጀመሪያ ነኝ።» በል።} [ሱረቱል አንዓም: 162 - 163]
አላህም ለነቢዩ ﷺ ሶላታቸው፣ እርዳቸው፣ ህይወታቸውና ሞታቸውም ተጋሪ ለሌለው የዓለማት ጌታ ለአላህ ብቻ እንደሆነ ለሰዎች እንዲነግሩ አዟቸዋል። በዚህ መሰረት ከአላህ ውጭ ላለ አካል እርድን የሰዋ ልክ ከአላህ ውጭ ላለ አካል ሶላት እንደሰገደው ሁሉ በአላህ ላይ በእርግጥም አጋርቷል። ምክንያቱም የላቀው አላህ ሶላትንና እርድን አጣምሮ ነው የገለፃቸውና፤ ሁለቱም ተጋሪ ለሌለው ለአላህ ብቻ መሆናቸውንም ገልጿል። ለጋኔኖች፣ ለመላእክቶች፣ ለሙታኖች እና ለመሳሰሉት ከአላህ ውጭ ላሉ አካላት ወደነሱ ለመቃረብ በማሰብ እርድ የፈፀመ ሰው ከአላህ ውጭ ላለ አካል ከሰገደ ሰው ጋር ተመሳሳይ ነው። ሶሒሕ በሆነ ሐዲሥም ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«لَعَنَ اللهُ مَنْ ذَبَحَ لِغَيْرِ اللهِ».
«ከአላህ ውጭ ላለ አካል እርድን መስዋእት ያደረገ አላህ ረግሞታል።» ኢማሙ አሕመድም ሐሰን በሆነ ሰነድ ከጧሪቅ ኢብኑ ሺሀብ (ረዲየላሁ ዐንሁ) በዘገቡት ሐዲሥ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡-
«مرَّ رَجُلَانِ عَلَى قَومٍ لَهُم صَنَمٌ لَا يَجُوزُهُ أَحَدٌ حَتَّى يُقرِّبَ لَهُ شَيئًا، فَقَالُوا لِأَحَدِهِمَا: قَرِّبْ. قَالَ: لَيسَ عِندِي شَيءٌ أَقَرِّبُهُ، قَالُوا: قَرِّبْ وَلَوْ ذَبَابًا، فَقَرَّبَ ذُبَابًا، فَخَلُّوا سَبِيلَهُ، فَدَخَلَ النَّارَ، وَقَالُوا لِلآخَرِ: قَرِّبْ. قَالَ: مَا كُنْتُ لِأُقَرِّبَ لِأَحَدٍ شَيْئًا دُونَ اللهِ جَلَّ جَلَالُهُ، فَضَرَبُوا عُنُقَه، فَدَخَلَ الجَنَّةَ».
«ሁለት ሰዎች ጣኦት አምላኪያን በሆኑ ህዝቦች በኩል አለፉ፤ ለዚያ ጣኦት አንዳች ነገር ሳያቀርብለት ማንም ሰው አያልፍም ነበር። ለአንደኛቸውም፦ ‹አቅርብ› አሉት። እርሱም፦ ‹የማቀርበው ምንም ነገር የለኝም› አለ። እነርሱም፦ ‹ዝንብ እንኳ ቢሆን አቅርብ› አሉት። ዝንብም አቀረበ። መንገዱንም ለቀቁለት፤ እሳትም ገባ። ሌላኛውንም፦ ‹አቅርብ› አሉት። እርሱም፦ ‹ክብሩ ከፍ ካለው አላህ ውጪ ለማንም አንዳችንም ነገር የማቀርብ አይደለሁም› አለ። አንገቱንም ቀሉት፤ ጀነትም ገባ።»
ወደ ጣኦትና መሰል ነገሮች ዝንብን ወይም መሰል ነገር ቁርባን ያቀረበ ሰው ሙሽሪክ (አጋሪ) ከሆነና የእሳት ቅጣት የሚገባው ከሆነ ጂኖችን፣ መላእክቶችንና ወሊዮችን የሚለምን፣ እነርሱ ከጭንቅ እንዲገላግሉት የሚፈልግ፣ ለእነርሱ ስለት የሚሳል፣ በእርድም ወደነርሱ የሚቃረብ ሰው እንዴት ሊታይ ነው? ይህንንም የገንዘቡን መጥጠበቅ፣ የህመምተኛውን መዳን፣ ወይም የእንሰሳዎቹንና የዘሩን ሰላም በመከጀል፣ አልያም የጂኖችን ክፋት በመፍራትና ይህን በመሰለ ምክንያት የሚፈፅምስ ምን ይሆን ቅጣቱ? ይህንንና መሰል ድርጊቶችን የፈፀመ ሰው፤ ያ ዝንብን ለጣኦት መቃረቢያ አድርጎ ካቀረበው ሰውዬ ይልቅ ሙሽሪክ (አጋሪ) ለመሆንና የእሳት ተገቢ ለመሆን ይበልጥ የተገባ እንደሆነ ምንም ጥርጥር የለውም።
በዚህ ዙሪያ ከመጡ ማስረጃዎች መካከል የሚከተለው የአላህ ንግግር ይገኝበታል፦
﴿إِنَّآ أَنزَلۡنَآ إِلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ بِٱلۡحَقِّ فَٱعۡبُدِ ٱللَّهَ مُخۡلِصٗا لَّهُ ٱلدِّينَ2 أَلَا لِلَّهِ ٱلدِّينُ ٱلۡخَالِصُۚ وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ إِنَّ ٱللَّهَ يَحۡكُمُ بَيۡنَهُمۡ فِي مَا هُمۡ فِيهِ يَخۡتَلِفُونَۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي مَنۡ هُوَ كَٰذِبٞ كَفَّارٞ3﴾
{ እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት የተሞላ ሲሆን አወረድነው:: አላህንም ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠራህ ሆነህ ተገዛው::
ንቁ! ፍጹም ጥሩ የሆነው ሃይማኖት የአላህ ብቻ ነው:: እነዚያ ከእርሱ ሌላ ጣዖታትን ረዳቶች አድረገው የያዙት «ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቃርቡን እንጂ ለሌላ አንገዛቸዉም።» ይላሉ:: አላህ በዚያ እነርሱ በሚለያዩበት ነገር በመካከላቸው ይፈርዳል:: አላህም ውሸታም ከሓዲ የሆነን ሰው አያቀናም::} [አዝ'ዙመር፡ 2-3] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿وَيَعْبُدُونَ مِنْ دُونِ اللَّهِ مَا لَا يَضُرُّهُمْ وَلَا يَنْفَعُهُمْ وَيَقُولُونَ هَؤُلَاءِ شُفَعَاؤُنَا عِنْدَ اللَّهِ قُلْ أَتُنَبِّئُونَ اللَّهَ بِمَا لَا يَعْلَمُ فِي السَّمَاوَاتِ وَلَا فِي الْأَرْضِ سُبْحَانَهُ وَتَعَالَى عَمَّا يُشْرِكُونَ18﴾
{ከአላህም ሌላ የማይጎዳቸውንና የማይጠቅማቸውን ይገዛሉ:: «እነዚህ አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው።» ይላሉ። «አላህን በሰማያትና በምድር ውስጥ የማያውቀው ነገር ኖሮ እናንተ ትነግሩታላችሁን?» በላቸው:: አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፤ ላቀም::} [ዩኑስ፡ 18]
ጥራት የተገባው አላህ በእነዚህ ሁለት አንቀጾች አጋርያን ከአላህ ውጪ ከፍጡራን መካከል ወዳጆች መያዛቸውን ገልጿል። እነዚያ ወዳጆች ወደ አላህ እንደሚያቃርቧቸውና ከእርሱ ዘንድ እንደሚያማልዷቸው በመሞገት በፍርሃት፣ በተስፋ፣በእርድ፣ በስለት፣ በዱዓና በመሳሰሉት የአምልኮ መገለጫዎች ከአላህ ጋር በማጋራት ያመልኳቸዋል። ከዚያም ጥራት የተገባው አላህ ውሸታምነታቸውን አጋለጠ፤ የሙግታቸውንም ከንቱነት ግልጽ አደረገ። ውሸታሞች፣ ከሓዲዎችና አጋርያን በማለትም ሰየማቸው። ከሽርካቸውም ራሱን አጠራ። አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿...سُبْحَانَهُ وَتَعَالَى عَمَّا يُشْرِكُونَ﴾
{…አላህ ከማይገባው ሁሉ ጠራ ከሚያጋሩትም ሁሉ ላቀ::} [አን-ነሕል: 1] በዚህም አንድ ሰው አላህ ዘንድ እንዲያማልደው ወይም እንዲያቃርበው በመፈለግ አልያም የታመመ እንዲድንለት፣ ንብረቱ እንዲጠበቅለት፣ በሩቅ ያለ ሰው ሰላም እንዲሆንለት እና ይህን መሰል ነገሮች በመከጀል መልአክን፣ ነቢይን፣ ጋኔንን፣ ዛፍን ወይም ድንጋይን ከአላህ ጋር በማጋራት የሚማፀን ከርሱም እርዳታን የሚጠይቅ፣ በስለትና በእርድም ወደርሱ የሚቃረብ ከሆነ አላህ እንዲህ ሲል የተናገረው በሆነው ከባዱ ሽርክ ውስጥና አደገኛ መከራ ውስጥ ወድቋል፦
﴿إِنَّ اللَّهَ لَا يَغْفِرُ أَنْ يُشْرَكَ بِهِ وَيَغْفِرُ مَا دُونَ ذَلِكَ لِمَنْ يَشَاءُ وَمَنْ يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدِ افْتَرَى إِثْمًا عَظِيمًا48﴾
{አላህ በእርሱ ማጋራትን ፈጽሞ አይምርም:: ከዚህ ውጪ ያለውንም ኃጢአት ለሚሻው ሰው ይምራል:: በአላህ የሚያጋራ ሰው ታላቅን ኃጢአት በእርግጥ ቀጠፈ::} [አን-ኒሳእ፡ 48] ጥራት ይገባውና እንዲህም ብሏል፡
﴿...إِنَّهُ مَنْ يُشْرِكْ بِاللَّهِ فَقَدْ حَرَّمَ اللَّهُ عَلَيْهِ الْجَنَّةَ وَمَأْوَاهُ النَّارُ وَمَا لِلظَّالِمِينَ مِنْ أَنْصَارٍ﴾
{እነሆ በአላህ የሚያጋራ ሰው አላህ በእርሱ ላይ ገነትን በእርግጥ እርም አደረገ:: መኖሪያዉም እሳት ናት:: ለበዳዩችም ምንም ረዳቶች የሏቸዉም::} [አልማኢዳህ: 72]
የትንሳኤ ቀን ምልጃ ለተውሒድና ኢኽላስ ባለቤቶች እንጂ ለሽርክ ባለቤቶች አትሆንም። ነቢዩ ﷺ "የአላህ መልእክተኛ ሆይ! በርሶ ምልጃ ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛው ማን ነው?" ተብለው ሲጠየቁ:
«مَنْ قَالَ: لَا إِلَهَ إِلَّا اللهُ خَالِصًا مِنْ قَلْبِهِ».
«ከልቡ ጥርት አድርጎ 'ላኢላሃ ኢለሏህ' ያለ ሰው ነው» በማለት መልሰዋል። ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል:
«لِكُلِّ نَبِيٍّ دَعْوَةٌ مُسْتَجَابَةٌ، فَتَعَجَّلَ كُلُّ نَبِيٍ دَعْوَتَهُ، وَإِنِّي اخْتَـبَأْتُ دَعْوَتِي شَفَاعَةً لِأُمَّتِي يَومَ القِيَامَةِ، فَهِيَ نَائِلَةٌ إِنْ شَاءَ اللهِ مَن مَاتَ مِنْ أُمَّتِي لَا يُشْرِكُ بِاللهِ شَيْئًا».
"እያንዳንዱ ነቢይ ተቀባይነት ያለው አንዲት ልመና አለችው። እያንዳንዱ ነቢይም በልመናው ተቻኩሏል። እኔ ግን ልመናዬን ለህዝቦቼ የትንሳኤ ቀን ምልጃ ትሆን ዘንድ ሸሽጌዋለሁ። እርሷም አላህ ከፈቀደ ከህዝቦቼ መካከል በአላህ ላይ ምንም ነገር ሳያጋራ ለሞተ ሰው ትደርሰዋለች።"
የቀድሞዎቹ ሙሽሪኮች አላህ ጌታቸው፣ ፈጣሪያቸውና ሲሳያቸውን የሚሰጣቸው መሆኑን ያምኑ ነበር። ይልቁንም በነቢያት፣ በወሊዮች፣ በመላእክት፣ በዛፎች፣ በድንጋዮችና በመሰል ነገሮች ላይ ተጣብቀው የቀሩት አላህ ዘንድ የነርሱን ምልጃና ወደርሱ ያቃርቡናል ብለው ይከጅሉ ስለነበር ነው፤ ይህም ከዚህ ቀደም ብሎ በአንቀጾቹ ላይ ተገልጿል። አላህ በዚህ ሰበብ ምህረት አላደረገላቸውም። ይልቁንም አላህ በታላቅ ምጽሐፉ አውግዟቸዋል፤ ካፊሮችና ሙሽሪኮችም ሲል ሰይሟቸዋል። እነዚህ አማልክት ያማልዱናል፤ ወደ አላህም ያቃርቡናል የሚለውን ሙግታቸውንም ውሸትነቱን አጋልጦባቸዋል። የአላህ መልዕክተኛም ﷺ ይህን ሰበባቸውን አልተቀበላቸውም። ይልቁንም ረሱል ﷺ በዚህ ሽርክ ምክንያት አምልኳቸውን ለአላህ ብቻ ጥርት እስኪያደርጉ ድረስ ተፋልመዋቸዋል። ይህም የጥራት ባለቤት የሆነውን ጌታ ቃል ለመተግበር ነው፦
﴿وَقَاتِلُوهُمْ حَتَّى لَا تَكُونَ فِتْنَةٌ وَيَكُونَ الدِّينُ لِلَّهِ...﴾
{ፈተና (ሁከት) እስከማይኖርና ሃይማኖት ለአላህ ብቻ እስከሚሆን ድረስ ተጋደሏቸው...} [አል-በቀራህ: 193] የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«أُمِرْتُ أَنْ أُقَاتِلَ النَّاسَ حَتَّى يَشْهَدُوا أَنْ لَا إِلهَ إِلَّا اللهُ وَأَنَّ مُحَمَّدًا رَسُولُ اللهِ، وَيُقِيمُوا الصَّلَاةَ، وَيُؤتُوا الزَّكَاةَ، فَإِذَا فَعَلُوا ذَلِكَ عَصَمُوا مِنِّي دِمَاءَهُم وَأَمْوَالَهُمْ إِلَّا بِحَقِّ الإِسْلَامِ، وَحِسَابُهُم عَلَى اللهِ».
"ከአላህ በቀር በእውነት የሚመለክ የለም ሙሐመድም የአላህ መልክተኛ ናቸው ብለው እስኪመሰክሩ፣ ሶላትን ቀጥ አድርገው እስኪሰግዱና ዘካን እስኪሰጡ ድረስ ሰዎችን እንድጋደል ታዝዣለሁ። ይህንን ከፈፀሙ በኢስላም ሐቅ ካልሆነ በቀር ደማቸውና ገንዘባቸውን ከኔ ጠብቀዋል። ሒሳባቸውም አላህ ዘንድ ነው።" የሐዲሡ ፍሬ ሃሳብም፦
«حَتَّى يَشْهَدُوا أَن لَا إِلهَ إِلَّا اللهُ».
«ከአላህ በስተቀር በሐቅ የሚመለክ አምላክ እንደሌለ እስከሚመሰክሩ ድረስ» ማለትም: ከአላህ ውጪ ያሉትን በሙሉ ትተው አላህን በአምልኮ እስኪነጥሉት ድረስ ማለት ነው።
ሙሽሪኮችም ጂንን ይፈሩና በነሱም ይጠበቁ ነበር፤ ይህንንም በተመለከተ የላቀው አሏህ እንዲህ የሚለው ቃሉን አወረደ፡
﴿وَأَنَّهُ كَانَ رِجَالٌ مِنَ الْإِنْسِ يَعُوذُونَ بِرِجَالٍ مِنَ الْجِنِّ فَزَادُوهُمْ رَهَقًا6﴾
{እነሆም ከሰዎች የሆኑ ወንዶች በጋኔን ወንዶች ይጠበቁ ነበር። ኩራትንም (ጥመትን) ጨመሯቸው።} [አል-ጂን: 6] የተፍሲር ሊቃውንቶች ስለዚህች የተከበረች አንቀጽ እንዲህ ብለዋል፦
﴿...فَزَادُوهُمْ رَهَقًا﴾
{…ኩራትንም (ጥመትን) ጨመሯቸው።} ማለትም፡ ፍራቻንና ድንጋጤን፤ ምክንያቱም ጂኖች ሰዎች በነርሱ ሲጠበቁ ባዩ ጊዜ በራሳቸው ስለሚፎክሩና ስለሚኮሩ እነርሱን ማምለክንና ወደነርሱ መጠጋትን እንዲያበዙ ማስፈራራትንና ማስደንገጥን ይጨምሩባቸዋል።
አላህም ሙስሊሞችን ከዚህ ሺርክ ፋንታ ጥራት በተገባው አላህና ፍፁም በሆኑ ቃላቶቹ እንዲጠበቁ አድርጓል፤ በዚህም ላይ እንዲህ ሲል ቃሉን አወረደ፦
﴿وَإِمَّا يَنْزَغَنَّكَ مِنَ الشَّيْطَانِ نَزْغٌ فَاسْتَعِذْ بِاللَّهِ إِنَّهُ سَمِيعٌ عَلِيمٌ200﴾
{የሰይጣን ጉትጎታ ቢያጋጥምህ በአላህ ብቻ ተጠበቅ:: አላህ ሁሉን ሰሚና ሁሉንም አዋቂ ነው::} [አል-አዕራፍ፡ 200] ልቅናው ከፍ ያለው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿قُلْ أَعُوذُ بِرَبِّ الْفَلَقِ1﴾
{በል፡ -በተፈልቃቂው ጎህ (በአል-ፈለቅ) ጌታ እጠበቃለሁ፤} ነቢዩ ﷺ እንዲህ ማለታቸውም በሶሒሕ ሐዲሥ ተዘግቧል፦
«مَنْ نَزَلَ مَنْزِلًا فَقَالَ: (أَعُوذُ بِكَلِمَاتِ اللهِ التَّامَّاتِ مِنْ شَرِّ مَا خَلَقَ)؛ لَم يَضُرَّهُ شَيءٌ حَتَّى يَرْتَحِلَ مِنْ مَنْزِلِهِ ذَلِكَ».
"በአንድ ስፍራ ላይ አርፎ ከዚያም ‹አዑዙ ቢከሊማቲላሂ አትታማቲ ሚን ሸሪ ማ ኸለቀ (ምሉዕ በሆኑ የአላህ ቃላት ከፈጠራቸው ጎጂ ነገሮች እጠበቃለሁ)› ያለ ሰው ከዛ ስፍራ እስኪንቀሳቀስ ድረስ አንዳችም አይጎዳውም።"
ከዚህ ቀደም ከተጠቀሱት የቁርኣን አንቀፆችና ሐዲሦች መዳንን የሚፈልግ፣ ሃይማኖቱን ለመጠበቅ የሚጓጓና ከትንሹም ይሁን ከትልቁ ሺርክ በሰላም መውጣትን የሚሻ ሰው በሙታን፣ በመላእክቶች፣ በጂኖችና በሌሎችም ፍጡራን ላይ ልብን ማንጠልጠል፣ እነርሱንም መማፀን፣ በእነርሱም መጠበቅ እና የመሳሰሉት ነገሮች ሁሉ የጃሂሊያ ዘመን የሆኑ ሙሽሪኮች ስራና እንዲሁም በአላህ ላይ ከሚፈፀም የሽርክ አይነት ሁሉ እጅግ አስቀያሚው መሆኑን ይገነዘባል። በመሆኑም ይህን ድርጊት መተው፣ ከእርሱም መጠንቀቅ፣ ሌሎችም እንዲተዉት መመካከርና በፈፃሚዎቹም ላይ ማውገዝ ግዴታ ነው።
በነዚህ የሽርክ ስራዎች የሚታወቅ ሰው ከዚያ ስራው ወደ አላህ በግልፅ ተውበት አድርጎ ዱዓውንና አምልኮውን ለአላህ ብቻ እስካላደረገ ድረስ ከእርሱ ጋር ጋብቻ መፈፀም፣ ያረደውን መብላት፣ በጀናዛው ላይ ሶላት መስገድም ሆነ ከኋላው ሆኖ መስገድ አይፈቀድም። ዱዓ ራሱ አምልኮ ነው፤ እንደውም የአምልኮ አስኳል (አንኳር) ነው። ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል:
«الدُّعَاءُ هُوَ العِبَادَةُ».
"ዱዓእ እርሱ አምልኮ ነው።" በሌላ ዘገባ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፡
«الدُّعَاءُ مُخُّ العِبَادَةِ».
"ዱዓእ የአምልኮ አስኳል (ቁንጮው) ነው።" ሙሽሪኮችን ማግባትን በተመለከተም የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿وَلَا تَنْكِحُوا الْمُشْرِكَاتِ حَتَّى يُؤْمِنَّ وَلَأَمَةٌ مُؤْمِنَةٌ خَيْرٌ مِنْ مُشْرِكَةٍ وَلَوْ أَعْجَبَتْكُمْ وَلَا تُنْكِحُوا الْمُشْرِكِينَ حَتَّى يُؤْمِنُوا وَلَعَبْدٌ مُؤْمِنٌ خَيْرٌ مِنْ مُشْرِكٍ وَلَوْ أَعْجَبَكُمْ أُولَئِكَ يَدْعُونَ إِلَى النَّارِ وَاللَّهُ يَدْعُو إِلَى الْجَنَّةِ وَالْمَغْفِرَةِ بِإِذْنِهِ وَيُبَيِّنُ آيَاتِهِ لِلنَّاسِ لَعَلَّهُمْ يَتَذَكَّرُونَ221﴾
{በአላህ አጋሪ የሆኑ ሴቶችን እስከሚያምኑ ድረስ አታግቧቸው:: አጋሪይቱ ነፃ ሴት ምንም ብትስባችሁ እንኳ ያመነችው ባሪያ ሴት በእርግጥ ለእናንተ በላጭ ናት:: ለአጋሪዎቹ እስከሚያምኑ ድረስ አትዳሩላቸው:: አጋሪ ወንድ ምንም ቢስባችሁ አማኝ ባሪያዎች ለእናንተ በላጭ ናቸው:: እነዚያ አጋሪዎች ወደ እሳት ይጣራሉ:: አላህም በፈቃዱ ወደ ገነትና ወደ ምህረት ይጠራል:: ህግጋቱንም ለሰዎች ሊገሰጹ ይከጀላልና ይገልጻል፡፡} [አልበቀራህ: 221] እናም ጥራት የተገባው አላህ ሙስሊሞች ጣዖታትን፣ ጂንኖችን፣ መላእክትንና ሌሎችንም ከሚገዙ አጋሪ ሴቶች ጋር አምልኮን ለአላህ ብቻ በማጥራት፣ መልእክተኛውንም ﷺ ባመጡት ነገር በማመንና መንገዳቸውንም በመከተል እስከሚያምኑ ድረስ እንዳይጋቡ ከልክሏል፡፡ ሙስሊም ሴቶችንም ለአጋሪዎች አምልኮን ለአላህ ብቻ በማጥራት፣ መልእክተኛውንም ﷺ በማመንና እርሳቸውንም በመከተል እስከሚያምኑ ድረስ ከመዳር ከልክሏል፡፡
ነፃዋ አጋሪ ሴት ለተመለከታት የምትማርክና ስትናገር የሰማትን የምታስደንቅ ብትሆን እንኳ አማኝ የሆነችው ባሪያ የተሻለች መሆኗን፤ እንዲሁም ነፃው አጋሪ ወንድ ሰሚውንና ተመልካቹን በውበቱ፣ በንግግር ጥበቡ፣ በጀግንነቱና በመሳሰሉት ቢማርክም እንኳን አማኝ የሆነው ባሪያ የተሻለ መሆኑን አሳወቀ። ከዚያም የዚህን ብልጫ ምክንያት እንዲህ በማለት አብራርቷል፦
﴿...أُولَئِكَ يَدْعُونَ إِلَى النَّارِ...﴾
{…እነዚያ አጋሪዎች ወደ እሳት ይጠራሉ…} [አል-በቀራህ፡ 221] አላህ በዚህ አንቀፅ ወደ እሳት ይጠራሉ ማለት የፈለገው አጋሪ ወንዶችንና አጋሪ ሴቶችን ነው፤ እነርሱ በንግግራቸው፣ በሥራቸው፣ በአኗኗራቸውና በባህሪያቸው ወደ እሳት ከሚጠሩት ናቸው። አማኝ ወንዶችና አማኝ ሴቶች ግን በባህሪያቸው፣ በሥራቸውና በአኗኗራቸው ወደ ጀነት ከሚጠሩት ናቸው። ታዲያ እነዚህና እነዚያ እንዴት ይስተካከላሉ?
በአጋሪዎች ጀናዛ ላይ ሶላት መስገድን በተመለከተ: የላቀው አላህ ስለ መናፍቃን እንዲህ ብሏል፦
﴿وَلَا تُصَلِّ عَلَى أَحَدٍ مِنْهُمْ مَاتَ أَبَدًا وَلَا تَقُمْ عَلَى قَبْرِهِ إِنَّهُمْ كَفَرُوا بِاللَّهِ وَرَسُولِهِ وَمَاتُوا وَهُمْ فَاسِقُونَ84﴾
{ከእነርሱ መካከል በሞተ በአንዱም ሰው ላይ ቢሆን ፈጽሞ አትስገድ:: በመቃብሩም ላይ አትቁም:: እነርሱ በአላህና በመልዕክተኛው ክደዋልና:: እነርሱም አመጸኞች ሆነው ሞተዋልና::} [አት-ተውባህ፡ 84] ከፍ ያለውና የላቀው አላህ በዚህች በተከበረች አንቀፅ መናፍቅና ከሃዲ በአላህና በመልዕክተኛው በመካዳቸው ምክንያት እንደማይሰገድባቸው ግልፅ አድርጓል። እንደዚሁም ከኋላቸው አይሰገድም፤ ለሙስሊሞችም ኢማሞች አይደረጉም። ይህም በመካዳቸው፣ ታማኝ ባለመሆናቸው፣ በእነርሱና በሙስሊሞች መካከል ባለው ታላቅ ጠላትነት፣ እንዲሁም የሰላትና የአምልኮ ሰዎች ባለመሆናቸው ነው። ምክንያቱም ክህደትና ከሽርክ ጋር ምንም ስራ አይቀርም። አላህን ከዚህ ነገር ደህንነትን እንዲለግሰን እንለምነዋለን። የአጋሪዎችን እርድ መብላትን በተመለከተም ክብሩ የላቀው አላህ የበክትና የአጋሪዎች እርድ ሐራም መሆኑን ሲያብራራ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَلَا تَأْكُلُوا مِمَّا لَمْ يُذْكَرِ اسْمُ اللَّهِ عَلَيْهِ وَإِنَّهُ لَفِسْقٌ وَإِنَّ الشَّيَاطِينَ لَيُوحُونَ إِلَى أَوْلِيَائِهِمْ لِيُجَادِلُوكُمْ وَإِنْ أَطَعْتُمُوهُمْ إِنَّكُمْ لَمُشْرِكُونَ121﴾
{በእርሱ ላይ የአላህ ስም ያልተጠራበትን ነገር አትብሉ:: እርሱም በእርግጥ አመጽ ነው:: ሰይጣናትም ወደ ወዳጆቻቸው በክትን በመብላት ይከራከሯችሁ ዘንድ ያሾከሹካሉ:: ብትታዘዟቸው በእርግጥ አጋሪዎች ናችሁ::} [አል‐አንዓም: 121] ልቅናው የላቀው አላህ ሙስሊሞችን የበከተ ስጋ እና የአጋሪን እርድ ከመብላት ከልክሏል፤ የዚህም ምክንያት አጋሪው የረከሰ ስለሆነ ነው። እርዱም የአላህን ስም ቢያወሳበት እንኳ እንደ በክት ይቆጠራል። ከርሱ የሚወጣው (ቢስሚላህ) ምንም ተጽእኖ የሌለው ከንቱ ነው፤ ምክንያቱም ሲያርዱ ቢስሚላህ ማለት አምልኮ ነው፤ አጋሪው ወደ አላህ ተውበት እስካላደረገ ድረስ አምልኮን ያበላሻል ውድቅም ያደርገዋል። አላህ የመጽሐፍ ሰዎችን ምግብ (ያረዱትን) እንዲህ በሚለው ቃሉ የፈቀደው:
﴿...وَطَعَامُ الَّذِينَ أُوتُوا الْكِتَابَ حِلٌّ لَكُمْ وَطَعَامُكُمْ حِلٌّ لَهُمْ...﴾
{...የእነዚያ መጽሐፍን የተሰጡ ሰዎች ምግብም (እርድ) ለእናንተ የተፈቀደ ነው:: ምግባችሁም ለእነርሱ የተፈቀደ ነው...} [አል‐ማኢዳህ: 5] ምክንያቱም ራሳቸውን ወደ መለኮታዊ ኃይማኖት ስለሚያስጠጉ እና በዚህ ጉዳይ ላይ ውሸታሞች ቢሆኑ እንኳ የሙሳና የዒሳ ተከታዮች ነን ብለው ስለሚሞግቱ ነው። አላህ ሙሐመድን ﷺ ለሰው ልጆች ሁሉ በመላክ ኃይማኖታቸውን ሽሮታል፤ ውድቅም አድርጎታል። ነገር ግን አላህ የመጽሐፉን ሰዎች ምግብና ሴቶቻቸውን ለእኛ ፍቁድ አድርጓል፤ ይህም የመፈቀዱ ምክንያት ታላቅ ጥበብና የተጠበቁ ምስጢሮች አሉት። በርግጥም የዕውቀት ባለቤቶች ጥበቡን አብራርተውታል። ይህ ግን ነብያትን፣ ወሊዮችንና የመሳሰሉትን ሙታንንና ጣዖታትን የሚያመልኩ አጋሪዎችን አይመለከትም። ምክንያቱም ኃይማኖታቸው መሰረትም ሆነ ምንም ዓይነት ማምታቻ የሌለው ነው፤ ይልቁንም ከመሰረቱ ውድቅ ነው። ስለሆነም የእነሱ እርድ በክት ነው፤ መብላቱም አይፈቀድም።
አንድ ሰው ለሚያናግረው ሰው፡- ‹ጂኒ አግኝቶሃል›፣ ‹ጂኒ ይዞሃል›፣ ‹ሸይጧን ዞሮብሃል› እና የመሳሰሉትን መናገር በተመለከተ ይህ ከስድብና ዘለፋ የሚመደብ ነው። ይህም ልክ እንደሌሎች የስድብና የዘለፋ አይነቶች ሁሉ በሙስሊሞች መካከል አይፈቀድም። ይህ ግን ከሽርክ የሚመደብ አይደለም፤ ተናጋሪው ጂኖች ያለ አላህ ፈቃድና ውሳኔ በሰዎች ላይ ተጽእኖ እንደሚያሳድሩ እምነት ካለው ግን ሺርክ ይሆናል። ጅኖችም ሆኑ ሌሎች ፍጡራን ያለ አላህ ፈቃድ ተፅእኖ ያሳድራሉ የሚል እምነት የያዘ ሰው በዚህ እምነቱ ከሀዲ ነው፤ ምክንያቱም ጥራት የተገባው አላህ የሁሉም ነገር ገዥ፣ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ፣ የሚጠቅመውም የሚጎዳውም እርሱ ብቻ ነውና። ያለ አላህ ፈቃድ፣ መሻትና ውሳኔ የሚሆን አንዳችም ነገር የለም። ግርማው ከፍ ያለው አላህ ነቢዩን ﷺ ይህን ታላቅ መሠረት ለሰዎች እንዲነግሩ ሲያዝ እንዲህ ብሏል፦
﴿قُلْ لَا أَمْلِكُ لِنَفْسِي نَفْعًا وَلَا ضَرًّا إِلَّا مَا شَاءَ اللَّهُ وَلَوْ كُنْتُ أَعْلَمُ الْغَيْبَ لَاسْتَكْثَرْتُ مِنَ الْخَيْرِ وَمَا مَسَّنِيَ السُّوءُ إِنْ أَنَا إِلَّا نَذِيرٌ وَبَشِيرٌ لِقَوْمٍ يُؤْمِنُونَ188﴾
{«አላህ የሻዉን በስተቀር ለራሴ ጥቅምንም ሆነ ጉዳት ማምጣት አልችልም:: የሩቅን ሚስጥር የማውቅ በነበርኩ ኖሮ ከመልካም ነገር ሁሉ ባበዛሁና ክፉም ነገር ባልነካኝ ነበር:: እኔም ለሚያምኑ ህዝቦች ሁሉ አስፈራሪና አብሳሪ እንጂ ሌላ አይደለሁም።» በላቸው::} [አል-አዕራፍ፡ 188] የፍጡራን አይነታና ከሁሉም በላጭ የሆኑት ነቢይ ﷺ አላህ ከሻላቸው በቀር ለራሳቸው ጥቅም ማምጣትም ሆነ ጉዳት መከላከል የማይችሉ ከሆኑ ታዲያ ከእርሳቸው ውጭ ያሉ ሌሎች ፍጡራንስ እንዴት ሊሆኑ ይችላሉ?! በዚህ ዙሪያ የተወሱ የቁርኣን አንቀጾች እጅግ በርካታ ናቸው።
የሩቅ ምስጢራትን እናውቃለን ብለው የሚሞግቱ ሟርተኞችን፣ አጭበርባሪዎችን፣ ኮከብ ቆጣሪዎችንና መሰሎቻቸውን መጠየቅ የማይፈቀድ የተወገዘ ድርጊት ነው። የሚሉትን አምኖ መቀበል ደግሞ ይበልጥ የከፋና የተወገዘ ነው። ይልቁንም ከክህደት ዘርፎች መካከል አንዱ ነው፤ ነብዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«مَنْ أَتَى عَرَّافًا فَسَأَلَهُ عَنْ شَيءٍ؛ لَمْ تُقْبَلْ لَهُ صَلَاةٌ أَرْبَعِينَ يَومًا».
"ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ስለ አንዳች ነገር የጠየቀ የአርባ ቀናት ሶላቱ ተቀባይነት የለውም።" ሙስሊም በሶሒሓቸው ዘግበውታል። ሙስሊም በሶሒሕ መጽሐፋቸው ላይ ከሙዓዊያህ ቢን አል'ሐከም አስ'ሱለሚይ ረዲየሏሁ ዓንሁ እንዳስተላለፉት፦
«أَنَّ النَّبيَّ ﷺ نَهَى عَنْ إِتْيَانِ الكُهَّانِ وَسُؤَالِهِم».
"ነቢዩ ﷺ ወደ ጠንቋዮች ከመሄድና እነርሱንም ከመጠየቅ ከልክለዋል።"
በሱነኖች ውስጥ ነቢዩ ﷺ እንዲህ ማለታቸው ተዘግቧል፦
«مَنْ أَتَى كَاهِنًا، فَصَدَّقَهُ بِمَا يَقُولُ؛ فَقَدْ كَفَرَ بِمَا أُنْزِلَ عَلَى مُحَمَّدٍ ﷺ».
"ጠንቋይ ዘንድ ሄዶ ጠንቋዩ የተናገረውን ያመነ ሰው ሙሐመድ ﷺ ላይ በወረደው ክዷል።" ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው ሐዲሦች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። በመሆኑም የሙስሊሞች ግዴታ በህክምናም ይሁን በሌላ ስም ስለ ሩቅ ምስጢራት በማውራትና ሙስሊሞችን በማወዛገብ ላይ የተሰማሩ ጠንቋዮችን፣ ሟርተኞችንና ሌሎች አጭበርባሪዎችን ከመጠየቅ መጠንቀቅ ነው። ይህም ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው ነቢዩ ﷺ ከዚህ ነገር በመከልከላቸውና በማስጠንቀቃቸው ነው። እዚህ ውስጥ ከሚካተቱ ነገሮች መካከል: አንዳንድ ሰዎች በሕክምና ስም የሩቅ ምስጢራዊ ጉዳዮችን እንደሚያውቁ መሞገታቸው ነው፤ የታመመውን ሰው ጥምጣም ወይም የታመመችዋን ሴት ሻሽ እና መሰል ነገሮችን በማሽተት “ይህ ህመምተኛ ወይም ይህች ህመምተኛ እንዲህ እንዲህ አድርጓል፤ እንዲህ እንዲህ ሰርቷል” በማለት በህመምተኛው ጥምጣም እና በመሰል ነገሮች ውስጥ ምንም አይነት ማመላከቻ የሌለውን የሩቅ ምስጢራዊ ጉዳዮችን ይናገራሉ። የዚህም አላማ ተራውን ህዝብ ማወናበድ ብቻ ነው፤ ይህም ሰዎች፡- “እርሱ ህክምናን፣ የህመም አይነቶችንና ምክንያቶቻቸውን ጠንቅቆ የሚያውቅ ነው” እንዲሉ ነው። ምናልባትም አንዳንድ መድኃኒቶችን ይሰጣቸውና በአላህ ፈቃድ ከፈውሱ ጋር ሊገጣጠም ይችላል፤ በመሆኑም ሰዎች ፈውሱ የተገኘው በእርሱ መድኃኒት ሰበብ እንደሆነ ያስባሉ። አንዳንዴም ህመሙ ሀኪም ነኝ ባዩን በሚያገለግሉ አንዳንድ ጂኒዎችና ሰይጣናት ሰበብ ሊከሰት ይችላል። እነርሱም ስለሚያውቋቸው አንዳንድ የሩቅ ሚስጥራት ይነግሩትና በዚህ ላይ ይተማመናል። ጂኒዎችንና ሰይጣናትንም ለእነርሱ በሚስማማቸው የአምልኮ አይነት ያስደስታቸዋል። በዚህም ምክንያት ከህመምተኛው ላይ ይነሳሉ፤ ተጣብቀውበት የነበረውንም ጥቃት ይተዉለታል። ይህም ስለ ጂኒዎችና ሰይጣናት እንዲሁም ይህን ስልት ስለሚጠቀሙ ሰዎች ያጤነ ሰው የሚያውቀው ነገር ነው።
በሙስሊሞችም ላይ ያለባቸው ግዴታ ከዚህ ነገር መጠንቀቅ፣ ሙስሊሞች እንዲተዉት መተዋወስ፣ በሁሉም ጉዳዮች ላይ ጥራት በተገባው አላህ ላይ መደገፍና በእርሱ ላይ መመካት ነው። ሸሪዓዊ በሆኑ ሩቃዎችና በተፈቀዱ መድኃኒቶች መጠቀም እንዲሁም በሽተኛውን በቤተ-ሙከራ በመመርመር በሽታውን በማረጋገጥ በሚያክሙ ሐኪሞች ዘንድ መታከም ችግር የለውም። ከነቢዩም ﷺ በትክክል እንደተዘገበው እንዲህ ብለዋል፦
«مَا أَنْزَلَ اللهُ دَاءً إِلَّا أَنْزَلَ لَهُ شِفَاءً، عَلِمَهُ مَنْ علِمه، وَجَهِلَهُ مَنْ جَهِلَهُ».
"አላህ ምንም አይነት በሽታን አላወረደም ለርሱ ፈውሱንም ያወረደ ቢሆን እንጂ፤ የሚያውቅ ያውቀዋል ያላወቀ አያውቀውም።" ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፡
«لِكُلِّ دَاءٍ دَوَاءٌ، فإِذَا أُصِيبَ دَوَاءٌ الدَّاءَ بََرَأَ بِإِذْنِ اللهِ».
«ለእያንዳንዱ በሽታ መድኃኒት አለው፤ መድኃኒቱ በሽታውን ካገኘው በአላህ ፈቃድ ይድናል።» ነቢዩ ﷺ እንዲህም ብለዋል፡
«عِبَادَ اللهِ، تَدَاوَوا وَلَا تَدَاوَوا بِحَرَامٍ».
"የአላህ ባሪያዎች ሆይ፤ ተካከሙ በሓራም ነገር ግን አትተካከሙ።" ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው ሐዲሦች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው።
ልቅናው የላቀ የሆነው አላህ የሙስሊሞችን ሁሉ ሁኔታ እንዲያስተካክልልን፣ ልባቸውንም ሆነ አካላቸውን ከክፉ ነገር ሁሉ እንዲፈውስ፣ በቅን መንገድ ላይ እንዲሰበስባቸው፣ እኛንም ሆነ እነርሱንም ከአጥማሚ ፈተናዎችና ለሰይጣንና ለወዳጆቹ ከመታዘዝ እንዲጠብቀን እንለምነዋለን። እርሱ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነውና። ብልሃትም ሆነ ኃይል በታላቁና ልቅናው ከፍ ባለዉ በአላህ ቢሆን እንጂ የለም።
የአላህ ሰላት፣ ሰላምና በረከት በባሪያውና በመልዕክተኛው በነቢያችን ሙሐመድ እንዲሁም በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸው ላይ ይስፈን።
***
بِسْمِ اللهِ الرَّحمَنِ الرَّحِيمِ
አራተኛው መልዕክት፡
በቢድዓዊና ሽርካዊ አውራዶች አላህን መገዛት ያለው ብይን:
ከዐብዱልዐዚዝ ቢን ዐብደላህ ቢን ባዝ ለተከበረው ወንድም (.........) አላህ ለመልካም ነገር ሁሉ ይግጠመው፤ አሚን።
የአላህ ሰላም፣ እዝነትና በረከት በናንተ ላይ ይሁን።
ከዚህ በመቀጠል፦ አላህ በቀናው ጎዳና ይምራዎትና በሀገራችሁ ላይ አላህ ምንም ማስረጃ ያላወረደባቸውን አውራዶች አጥብቀው የያዙ ሰዎች መኖራቸውን፣ ከእነዚህም ውስጥ የቢድዓም የሽርክም ስራዎች እንደሚገኙበት፣ እንዲሁም ይህንን ተግባር የምእመናን መሪ ወደ ሆኑት ዐሊይ ኢብን አቢ ጧሊብ (አላህ ስራቸውን ይውደድላቸውና) እና ወደ ሌሎችም እንደሚያስጠጉ የሚገልጸው ክቡር ደብዳቤዎ ደርሶኛል። እነዚህንም አውራዶች በዚክር መድረኮች ወይም ከመግሪብ ሶላት በኋላ በመስጂዶች ውስጥ ወደ አላህ የሚያቃርብ ነው ብለው እየሞገቱ ይላሉ፤ ለምሳሌም እንደ «ቢሐቂላህ፣ ሪጃለላህ፣ አዒኑና ቢዐውኒላህ፣ ወኩኑ ዐውነና ቢላህ» ማለታቸው። እንዲህም ይላሉ፡ «እናንተ አቅጧቦችም፣ ጌቶችም፣ በኛም ውስጥ ያላችሁ የእርዳታ ባለቤቶችም ሆይ! (ጥሪያችንን) ተቀበሉን፤ አላህ ዘንድም አማልዱን፡፡ ይህ ባሪያችሁ በደጃፋችሁ ቆሟል፤ በበራችሁም ላይ ተወስኗል፡፡ ከጉድለቱም የተነሳ ፈሪ ነው፡፡ የአላህ መልክተኛ ሆይ! ድረስልን፡፡ ከእናንተ ሌላ የምሄድበት የለኝም፡፡ ፍላጎትም የሚገኘው ከእናንተ ዘንድ ነው፡፡ እናንተም የአላህ ቅርብ ሰዎች ናችሁ፡፡ የሰማዕታት አለቃ በኾነው በሐምዛ እንዲሁም ከእናንተ ውስጥ ለኛ ረዳት በኾኑት እንማጸናችኋለን፡፡ የአላህ መልክተኛ ሆይ! ድረስልን፡፡» እንዲህም ይላሉ: «አላህ ሆይ! የሃይልህ ምስጢሮች መገለጥና ለእዝነታዊ ብርሃኖችህ መፍለቅ ሰበብ ላደረከው፤ ለአምላካዊ ስፍራህ ምትክና ለዛታዊ ምስጢሮችህ ምትክ በሆነውም ላይ ሶላትህን አውርድ።»
ቢድዓና ሽርክ ምን እንደሆኑ እንዲሁም ይህን ዱዓ በሚያደርግ ኢማም ኋላ የሚሰገድ ሶላት ይፈቀድ እንደሆነ እንዲብራራላችሁ የነበራችሁ ፍላጎት ከጥያቄያችሁ አውድ ይታወቅ ነበር?
መልሱም፦ ምስጋና ሁሉ ለብቸኛው አላህ የተገባ ነው። የአላህ ሰላትና ሰላም ከእሳቸው በኋላ ነብይ የሌለ በሆኑት ነብይ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸውም እንዲሁም እስከ ዕለተ ፍርድ ድረስ በእርሳቸው መመሪያ በተመሩትም ላይ ሁሉ ይስፈን።
በመቀጠል:- አላህ መልካሙን ይግጠምህና - አላህ ፍጡራንን የፈጠረውና መልክተኞችንም (ዐለይሂሙ ሰላቱ ወሰላም) የላከው ምንም ተጋሪ ሳይኖረው እርሱ በብቸኝነት እንዲመለክ እንደሆነ እወቅ! ከፍ ያለው አላህም እንዲህ ብሏል፦
﴿وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنْسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ56﴾
{ጂኒንን እና ሰዉን ሊገዙኝ እንጂ ለሌላ አልፈጠርኳቸዉም::} [አዝ-ዛሪያት፡ 56]
አምልኮ ማለት -ከዚህ በፊት እንደተብራራው- አላህና መልክተኛው ያዘዙትን በመፈጸምና የከለከሉትን በመተው፣ በአላህና በመልክተኛው በማመን፣ ሥራን ለአላህ ብቻ ጥርት በማድረግ፣ ለአላህም ከፍ ያለ ውዴታን እንዲሁም ከርሱ ውጭ ለማንም ሳይሆን ለእርሱ ብቻ ሙሉ መተናነስን በመላበስ ጥራት የተገባውን አላህንና መልክተኛውን ሙሐመድ (ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) መታዘዝ ነው፤ የበላይ የሆነው አላህ እንዲህ ብሏል፡-
﴿وَقَضَى رَبُّكَ أَلَّا تَعْبُدُوا إِلَّا إِيَّاهُ...﴾
{ጌታህም እንዲህ ሲል አዘዘ:: እርሱን እንጂ ሌላን አትገዙ፤} [አል-ኢስራእ፡ 23] ማለትም፦ እርሱ በብቸኝነት እንዲመለክ አዘዘ፤ አደራም አለ ማለት ነው። ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿الْحَمْدُ لِلَّهِ رَبِّ الْعَالَمِينَ2 الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ3 مَالِكِ يَوْمِ الدِّينِ4 إِيَّاكَ نَعْبُدُ وَإِيَّاكَ نَسْتَعِينُ5﴾
{{ምስጋና ሁሉ የዓለማት ጌታ ለሆነው ለአሏህ የተገባ ነው።
እጅግ በጣም ሩህሩህ በጣም አዛኝ ለሆነው፤
የፍርዱ ቀን ባለቤት ለሆነው (ለአላህ ብቻ የተገባ ነው)::
አንተን ብቻ እንግገዛለን:: አንተንም ብቻ እርዳታን እንለምናለን (በሉ)።} [አል-ፋቲሓ፡ 2-5] በመሆኑም ከፍ ያለው አላህ በነዚህ አንቀፆች በብቸኝነት ሊመለክና እርዳታ ሊጠየቅበት የሚገባው እርሱ ብቻ መሆኑን ግልፅ አድርጓል። ልቅናው ከፍ ያለው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿إِنَّآ أَنزَلۡنَآ إِلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ بِٱلۡحَقِّ فَٱعۡبُدِ ٱللَّهَ مُخۡلِصٗا لَّهُ ٱلدِّينَ2 أَلَا لِلَّهِ ٱلدِّينُ ٱلۡخَالِصُۚ...﴾
{ እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት የተሞላ ሲሆን አወረድነው:: አላህንም ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠራህ ሆነህ ተገዛው::
አስተውሉ ፍጹም ጥሩ የሆነው ሃይማኖት ለአላህ ብቻ ነው::…} [አዝ-ዙመር፡ 2-3] ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿فَادْعُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ وَلَوْ كَرِهَ الْكَافِرُونَ14﴾
{አላህንም ከሓዲያን ቢጠሉም እንኳ ሃይማኖትን ለእርሱ አጥሪዎች ሆናችሁ ተገዙት}:: [ጋፊር፡ 14] ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿وَأَنَّ الْمَسَاجِدَ لِلَّهِ فَلَا تَدْعُوا مَعَ اللَّهِ أَحَدًا18﴾
{እነሆ መስጊዶችም የአላህ ብቻ ናቸው:: እናም በውስጣቸው ከአላህ ጋር አንድንም አትገዙ ማለትም ተወረደልኝ::} [አል_ጂን፡ 18] በዚህ መልኩ የመጡ ቁርአናዊ ማስረጃዎች በርካታ ሲሆኑ ሁሉም የሚያመለክቱት አላህን በአምልኮ መነጠል ግዴታ መሆኑን ነው።
የዱዓእ አይነቶች ባጠቃላይ አምልኮ እንደሆኑ የታወቀ ነው። በመሆኑም በእነዚህ የተከበሩ አንቀፆችና ተመሳሳይ ሃሳብ ይዘው የመጡትን ማስረጃዎች መሰረት በማድረግ ዱዓእ ማድረግ፣ እገዛን መሻትና የድረሱልኝ ጥሪ ማቅረብ ከአላህ በቀር ከማንም መጠየቅ አይፈቀድም። ይህ ግን ህያውና በቅርብ የሚገኝ ፍጡር ሊፈፅማቸው የሚችላቸው የተለመዱና ተጨባጭ የሆኑ ጉዳዮችን አያካትትም፤ ምክንያቱም እነኚህ ከአምልኮ አይመደቡምና። ይልቁንም አንድ ሰው አቅሙ በሚፈቅድላቸው የተለመዱ ጉዳዮች ላይ ህያው ከሆነና ማድረግ ከሚችል ሌላ ሰው እርዳታን መከጀሉ በግልፅ መረጃና በዑለማዎች ስምምነት የተፈቀደ ነው። ለምሳሌ ልጁ፣ አገልጋዩ ወይም ውሻው እና የመሳሰሉት የሚያደርሱበትን ጉዳት ለመከላከል ባለቤቱን እርዳታ ቢጠይቅ ወይም የድረስልኝ ጥሪ ቢጣራ ችግር የለውም። ለምሳሌ አንድ ሰው ህያው በሆነ በአካል ቀርቦ በሚገኝና አቅም ባለው ወይም ደግሞ ሩቅ በሆነ ሰው እንደ መጻጻፍና በመሳሰሉት ተጨባጭ መንገዶች አማካኝነት ቤቱን በመገንባት፣ መኪናውን በማሰራት ወይም ይህን በመሰሉ ጉዳዮች ላይ መታገዙ ይፈቀዳል። ከዚህም ውስጥ አንድ ሰው በጂሀድና በጦርነት እንዲሁም በመሳሰሉት አጋጣሚዎች ከባልደረቦቹ እገዛን መሻቱ ይገኝበታል። ከዚሁ ጋር በተያያዘም ከፍ ያለው አላህ በነብዩሏህ ሙሳ ዓለይሂ ሰላም ታሪክ ላይ እንዲህ ብሏል፦
﴿...فَاسْتَغَاثَهُ الَّذِي مِنْ شِيعَتِهِ عَلَى الَّذِي مِنْ عَدُوِّهِ...﴾
{ያም ከወገኑ የሆነው ሰው በዚያ ከጠላት በሆነው ሰው ላይ እርዳታን ጠየቀው።} [አልቀሶስ፡ 15]
በሙታን፣ በጂኖች፣ በመልአኮች፣ በዛፎችና በድንጋዮች እርዳታን መፈለግ ከትልቁ ሽርክ ነው። ይህም የቀድሞዎቹ ሙሽሪኮች እንደ አል-ዑዛና አል-ላት ከመሳሰሉ አማልክቶቻቸው ጋር ይፈፅሙት ከነበረው ተግባር ጋር ተመሳሳይ ነው። በተመሳሳይ መልኩ ወሊይነት አላቸው ተብለው ከሚታመኑ ህያዋን ህሙማንን መፈወስ፣ ልቦችን መምራት፣ ጀነት ማስገባት፣ ከእሳት ማዳን እና በመሳሰሉት አላህ እንጂ ሌላ አካል ሊፈፅመው በማይችለው ጉዳይ ላይ እርዳታን መፈለግና መከጀልም ከዚሁ የሚመደብ ነው።
ከላይ የተጠቀሱት አንቀፆችና ይህንኑ ትርጉም ይዘው የመጡ ሌሎች አንቀፆችም ሆኑ ሐዲሶች ሁሉ የሚያመለክቱት በሁሉም ጉዳዮች ላይ ልብን ወደ አላህ ማዞርና አምልኮንም ለእርሱ ብቻ ጥርት አድርጎ መፈፀም ግዴታ መሆኑን ነው፤ ምክንያቱም ቀደም ብሎ በተጠቀሱ አንቀጾች ላይ እንደሰፈረው የአላህ ባሮች የተፈጠሩት ለዚህ ነው፤ የታዘዙትም በዚሁ ነው። ጥራት የተገባው ጌታችንም እንዲህ ብሏል፡-
﴿وَاعْبُدُوا اللَّهَ وَلَا تُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا...﴾
{አላህን ተገዙ:: በእርሱ ምንንም አታጋሩ።…} [አን-ኒሳእ: 36] የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿وَمَا أُمِرُوا إِلَّا لِيَعْبُدُوا اللَّهَ مُخْلِصِينَ لَهُ الدِّينَ...﴾
{ሃይማኖትን ለአላህ ብቻ አጥሪዎችና ቀጥተኞች ሆነው አላህን ሊገዙት እንጂ ያልታዘዙ ሲሆኑ (ተለያዩ)} [አል-በይናህ፡ 5] ነቢዩም ﷺ በሙዓዝ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ሓዲሥ እንዲህ ብለዋል፦
«حَقُّ اللهِ عَلَى العِبَادِ أَنْ يَعْبُدُوهُ وَلَا يُشْرِكُوا بِهِ شَيْئًا».
"አላህ በባሮቹ ላይ ያለው መብት በእርሱ ምንንም ሳያጋሩ በብቸኝነት ሊያመልኩት ነው።" ሶሒሕ በመሆኑ ላይ ተስማምተውበታል። ነቢዩም ﷺ ከኢብኑ መስዑድ -ረዲየሏሁ ዐንሁ- በተላለፈ ሐዲስ እንዲህ ብለዋል፦
«مَنْ مَاتَ وَهُوَ يَدْعُو لِلَّهِ نِدًّا؛ دَخَلَ النَّارَ».
«ከአላህ ውጭ ሌላን ሲማፀን የሞተ ሰው እሳት ገባ።» ቡኻሪ ዘግበውታል። በሶሒሕ ቡኻሪና ሙስሊም ከኢብኑ ዐባስ - አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - በተላለፈ ሓዲሥ ነብዩ ﷺ ሙዓዝን ወደ የመን በላኩት ጊዜ እንዲህ ብለውታል፦
«إِنَّكَ تَأْتِي قَومًا أَهْلَ كِتَابٍ، فَلْيَكُنْ أَوَّلَ مَا تَدْعُوهُم إِلَيهِ شَهَادَةِ أَنْ لَا إِلهَ إِلَّا اللهُ».
"አንተ የምትሄድባቸው ሰዎች ከመጽሐፉ ባለቤት የሆኑ ህዝቦች ናቸው፤ በመሆኑም የመጀመሪያው ጥሪህ ወደ "ላ ኢላሃ ኢለሏህ" ምስክርነት ይሁን።" በሌላ ዘገባ:
«اُدْعُهُمْ إِلَى شَهَادَةِ أَنْ لَا إِلهَ إِلَّا اللهُ وَأَنِّي رَسُولُ اللهِ».
«ከአላህ በስተቀር በእውነት የሚመለክ አምላክ እንደሌለና እኔም የአላህ መልዕክተኛ መሆኔን እንዲመሰክሩ ጥራቸው»። በቡኻሪ ዘገባ:
«فَلْيَكُنْ أَوَّلَ مَا تَدْعُوهُم إِلَى أَنْ يُوَحِّدُوا اللهَ».
«በቅድሚያ ልትጠሯቸው የሚገባው አላህን በአምልኮ ወደ መነጠል ይሁን!» በሶሒሕ ሙስሊምም ከጧሪቅ ቢን አሽየም አልአሽጀዒይ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፦
«مَنْ قَالَ: لَا إِلهَ إِلَّا اللهُ، وَكَفَرَ بِمَا يُعْبَدُ مِن دُونِ اللهِ؛ حَرُمَ مَالُهُ وَدَمُهُ، وَحِسَابُهُ عَلَى اللهِ جَلَّ جَلَالُهُ».
«ላኢላሃ ኢለሏህ ብሎ ከአላህ ውጪ በሚመለኩ ነገሮች የካደ ሰው፤ ገንዘቡም ደሙም እርም ይሆናል። ሂሳቡ ያለው አላህ ላይ ነው።» ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው ሐዲሦች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው።
ይህ ተውሒድ የእስልምና ሃይማኖት መሰረትና አስኳል፣ የነገሩ ሁሉ ቁንጮና ከግዴታዎችም ሁሉ ታላቁ ነው። ሰውንና ጋኔንን የመፍጠሩም ሆነ መልዕክተኞችን ሁሉ (በእነርሱ ላይ የአላህ ሰላም ይሁን) የመላኩ ጥበብም ይኸው ነው። ለዚህም ማስረጃ የሚሆኑ አንቀፆች ከዚህ በፊት አልፈዋል። ከእነዚህም መካከል የላቀው ጌታችን እንዲህ ብሏል፦
﴿وَمَا خَلَقْتُ الْجِنَّ وَالْإِنْسَ إِلَّا لِيَعْبُدُونِ56﴾
{ጂኒንና ሰዉን ሊገዙኝ እንጂ ለሌላ አልፈጠርኳቸዉም::} [አዝ-ዛሪያት፡ 56] ለዚህም ሌላኛው ማስረጃው ተከታዩ ክብሩ የላቀው የአላህ ንግግር ነው፦
﴿وَلَقَدْ بَعَثْنَا فِي كُلِّ أُمَّةٍ رَسُولًا أَنِ اعْبُدُوا اللَّهَ وَاجْتَنِبُوا الطَّاغُوتَ...﴾
{በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ አላህን ተገዙ ጣዖትን ራቁ በማለት የሚያስተምር መልዕክተኛን ልከናል...} [አን-ነሕል፡ 36] ጥራት የተገባውና የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَمَا أَرْسَلْنَا مِنْ قَبْلِكَ مِنْ رَسُولٍ إِلَّا نُوحِي إِلَيْهِ أَنَّهُ لَا إِلَهَ إِلَّا أَنَا فَاعْبُدُونِ25﴾
{ካንተ በፊትም እነሆ ከእኔ ሌላ አምላክ የለምና ተገዙኝ በማለት ወደ እርሱ የምናወርድለት ቢሆን እንጂ ከመልዕክተኛ አንድንም አላክንም::} [አል-አንቢያእ፡ 25] ታላቅና የላቀው አላህም ኑሕ፣ ሁድ፣ ሷሊህና ሹዐይብ (የአሏህ ሶለዋትና ሰላም በእነርሱ ላይ ይስፈንና) ለህዝቦቻቸው እንዲህ ማለታቸውን ነግሮናል፦
﴿...اعْبُدُوا اللَّهَ مَا لَكُمْ مِنْ إِلَهٍ غَيْرُهُ...﴾
{አላህን ብቻ ተገዙ:: ከእርሱ ሌላ ምንም አምላክ የላችሁም::…} [አልአዕራፍ 59] ይህች ከዚህ በፊት የነበሩት ሁለት አንቀፆች እንዳመለከቱት የሁሉም መልክተኞች ጥሪ ናት። የመልክተኞቹ ጠላቶችም እንኳ መልክተኞቹ አላህን በአምልኮ እንዲነጥሉና ከእርሱ ሌላ የሚመለኩ አማልክትን እንዲተዉ እንዳዘዟቸው አምነዋል። ልክ ክብሩ የላቀው አላህ በዓድ ህዝቦች ታሪክ ውስጥ እንደገለጸው፤ እነርሱም ለሁድ - የአላህ ሰላም በእርሳቸው ላይ ይሁንና - እንዲህ ብለውታል፦
﴿...أَجِئْتَنَا لِنَعْبُدَ اللَّهَ وَحْدَهُ وَنَذَرَ مَا كَانَ يَعْبُدُ آبَاؤُنَا...﴾
{አላህን አንድ አድርገን ብቻውን እንድንገዛውና አባቶቻችን ይገዟቸው የነበሩትን አማልክት እንድንተው መጣህብን?...} [አል-አዕራፍ፡ 70] ነብያችን ሙሐመድ ﷺ ቁረይሾችን አላህን በብቸኝነት ወደ ማምለክና ከእርሱ ሌላ የሚያመልኳቸውን መላእክትን፣ ወሊዮችን፣ ጣዖታትን፣ ዛፎችንና ሌሎችንም ነገሮች ወደ መተው በጠሯቸው ጊዜ ስለነርሱ መልስ አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿أَجَعَلَ الْالِهَةَ إِلَهًا وَاحِدًا إِنَّ هَذَا لَشَيْءٌ عُجَابٌ5﴾
{«አማልዕክቶችን አንድ አምላክ አደረጋቸውን? ይህ አስደናቂ ነገር ነው።»} [ሷድ፡ 5] ጥራት ይገባውና የላቀው አላህ ስለ መካ አጋርያን እንዲህ ብሏል፦
﴿إِنَّهُمْ كَانُوا إِذَا قِيلَ لَهُمْ لَا إِلَهَ إِلَّا اللَّهُ يَسْتَكْبِرُونَ35 وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ36﴾
{ እነርሱ «ከአላህ ሌላ እውነተኛ አምላክ የለም» በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ።
«እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን እንዴ?» ይሉ ነበር።} [አስ-ሷፋት፡ 35-36] ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው የቁርኣን አንቀጾች በርካታ ናቸው።
አላህ እኔንም አንተንም በዲኑ ላይ ጥልቅ ግንዛቤንና የዓለማቱን ጌታ እውነት በተመለከተም አስተዋይነትን ይግጠመንና በጠቀስናቸው አንቀፆችና ሐዲሦች መሰረት በጥያቄህ ላይ ያብራራሃቸው እነዚህ ዱዓዎችና የእርዳታ ፍለጋ አይነቶች ሁሉም ከትልቁ ሺርክ አይነቶች የሚመደቡ መሆናቸው ግልጽ ይሆንልሃል። ምክንያቱም ከአላህ ውጭ ላለ አካል የሚደረግ አምልኮና ከእርሱ ውጭ ማንም ሊያደርጋቸው የማይችላቸውን ነገሮች ከሙታንና ሩቅ ካሉ አካላት መጠየቅ ናቸውና። ይህ ደግሞ ከቀድሞዎቹ ሰዎች ሺርክ የከፋ ነው። ምክንያቱም የቀድሞዎቹ ሰዎች የሚያጋሩት በድሎት ጊዜ ብቻ ነው። በችግር ጊዜ ግን አምልኮን ለአላህ ጥርት ያደርጋሉ። ምክንያቱም ከችግር ሊያላቅቃቸው የሚችለው እርሱ ብቻ መሆኑን ያውቃሉና። አላህም ግልፅ በሆነው መጽሐፉ ላይ ስለነዚያ አጋሪዎች እንዲህ ብሏል፦
﴿فَإِذَا رَكِبُواْ فِي ٱلۡفُلۡكِ دَعَوُاْ ٱللَّهَ مُخۡلِصِينَ لَهُ ٱلدِّينَ فَلَمَّا نَجَّىٰهُمۡ إِلَى ٱلۡبَرِّ إِذَا هُمۡ يُشۡرِكُونَ65﴾
{በመርከቦች ውስጥ በተሳፈሩ ጊዜም አላህን መገዛትን ለእርሱ ብቻ ያጠሩ ሆነው ይጠሩታል:: ወደ የብስ በማውጣት ባዳናቸው ጊዜ ግን ወዲያውኑ እነርሱ ጣዖትን ያጋራሉ::} [አል'ዓንከቡት፡ 65] ጥራት ይገባውና የላቀው አላህ በሌላ አንቀጽ ሲያናግራቸው እንዲህ ብሏል፦
﴿وَإِذَا مَسَّكُمُ ٱلضُّرُّ فِي ٱلۡبَحۡرِ ضَلَّ مَن تَدۡعُونَ إِلَّآ إِيَّاهُۖ فَلَمَّا نَجَّىٰكُمۡ إِلَى ٱلۡبَرِّ أَعۡرَضۡتُمۡۚ وَكَانَ ٱلۡإِنسَٰنُ كَفُورًا67﴾
{በባህሩ ውስጥ ጉዳት በደረሰባችሁ ጊዜ የምትጠሯቸው አማልክት ሁሉ ይጠፉባችሁና እርሱ አላህ ብቻ ይቀራል። ወደ የብስም በማድረስ ባዳናችሁ ጊዜ እምነትን ትተዋላችሁ:: ሰውም በጣም ከሓዲ ነው::} [አል-ኢስራእ: 67]
ከእነዚህ በዘመናችን ካሉ አጋሪዎች አንዱ እንዲህ ቢል፡- «እኛ እነዚያ በራሳቸው እንደሚጠቅሙ፣ በሽተኞቻችንንም በራሳቸው እንደሚፈውሱ፣ ወይም በራሳቸው እንደሚጠቅሙን ወይም በራሳቸው እንደሚጎዱን አናስብም፡፡ ይልቁንስ የምንፈልገው በዚህ ጉዳይ ላይ ወደ አላህ የሚያቃርቡበትን ምልጃቸውን ነው፡፡»
መልሱም፦ ይህ የቀድሞዎቹ ከሃዲያን አላማና ፍላጎት ነበር። ፍላጎታቸው አማልክቶቻቸው ይፈጥራሉ ወይም ሲሳይ ይሰጣሉ፣ አልያም በራሳቸው ጥቅም ማምጣትም ይሁን ጉዳትን ማስወገድ ይችላሉ የሚል አልነበረም። ይህን አላህ በቁርኣን ውስጥ ስለነርሱ የጠቀሰው ነገር ውድቅ ያደርገዋል። ይልቁንም እነርሱ የፈለጉት የእነዚያን አማልክት ምልጃና ክብር እንዲሁም ወደ አላህ ያቃርቡናል የሚለውን ነበር። ጥራት የተገባው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَيَعۡبُدُونَ مِن دُونِ ٱللَّهِ مَا لَا يَضُرُّهُمۡ وَلَا يَنفَعُهُمۡ وَيَقُولُونَ هَٰٓؤُلَآءِ شُفَعَٰٓؤُنَا عِندَ ٱللَّهِ...﴾
{አጋሪዎች ከአላህ ሌላ የማይጎዳቸውንና የማይጠቅማቸውን ይገዛሉ:: «እነዚህ አላህ ዘንድ አማላጆቻችን ናቸው።…» [ዩኑስ፡ 18] አላህም እንዲህ በማለት መለሰላቸው፦
﴿...قُلۡ أَتُنَبِّـُٔونَ ٱللَّهَ بِمَا لَا يَعۡلَمُ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَلَا فِي ٱلۡأَرۡضِۚ سُبۡحَٰنَهُۥ وَتَعَٰلَىٰ عَمَّا يُشۡرِكُونَ﴾
{…«አላህ በሰማያትና በምድር ውስጥ የማያውቀው ነገር ኖሮ እናንተ ትነግሩታላችሁን?» በላቸው:: አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ፤ ላቀም::} [ዩኑስ፡ 18] ከእንከን የጠራው ጌታችን በሰማያትም ሆነ በምድር አጋሪዎቹ በሚፈልጉት መልኩ እርሱ ዘንድ አማላጅ እንደሌለ ግልጽ አድርጓል፡፡ አላህ መኖሩን የማያውቀው ነገር ህልውና የለውም፤ ምክንያቱም ከርሱ ምንም ነገር አይሰወርምና፡፡ የላቀው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿تَنزِيلُ ٱلۡكِتَٰبِ مِنَ ٱللَّهِ ٱلۡعَزِيزِ ٱلۡحَكِيمِ 1 إِنَّآ أَنزَلۡنَآ إِلَيۡكَ ٱلۡكِتَٰبَ بِٱلۡحَقِّ فَٱعۡبُدِ ٱللَّهَ مُخۡلِصٗا لَّهُ ٱلدِّينَ2 أَلَا لِلَّهِ ٱلدِّينُ ٱلۡخَالِصُۚ وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ إِنَّ ٱللَّهَ يَحۡكُمُ بَيۡنَهُمۡ فِي مَا هُمۡ فِيهِ يَخۡتَلِفُونَۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي مَنۡ هُوَ كَٰذِبٞ كَفَّارٞ3﴾
{ የመጽሐፉ መወረድ አሸናፊና ጥበበኛ ከሆነው ከአላህ ነው::
እኛ ወደ አንተ መጽሐፉን በእውነት የተሞላ ሲሆን አወረድነው:: አላህንም ሃይማኖትን ለእርሱ ብቻ ያጠራህ ሆነህ ተገዛው::
ንቁ! ፍጹም ጥሩ የሆነው ሃይማኖት ለአላህ ብቻ ነው:: እነዚያ ከእርሱ ሌላ ጣዖታትን ረዳቶች አድረገው የያዙት «ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቃርቡን በማሰብ እንጂ ለሌላ አንገዛቸዉም።» ይላሉ:: አላህ በዚያ እነርሱ በሚለያዩበት ነገር በመካከላቸው ይፈርዳል:: አላህም ውሸታም ከሓዲ የሆነን ሰው አያቀናም::} [አዝ-ዙመር: 1-3]
እዚህ አንቀጽ ላይ ሃይማኖት በማለት የተፈለገው አምልኮ ነው። ይህም -ከዚህ ቀደም እንደተገለጸው- አላህንና መልዕክተኛውን ﷺ መታዘዝ ነው። በውስጡም የሚከተሉት ይካተታሉ፦ ዱዓእ፣ እገዛን መጠየቅ፣ ፍራቻ፣ ተስፋ ማድረግ፣ እርድ፣ ስለት፣ ሶላት፣ ፆምና ሌሎችም አላህና መልዕክተኛው ያዘዙባቸው ነገሮች ሁሉ ይካተቱበታል። ጥራት የተገባው ጌታችንም አምልኮ ለእርሱ ብቻ እንደሆነና ባሮቹም ለታላቁ ጌታ በኢኽላስ ሊፈጽሙት ግዴታ መሆኑን አብራርቷል። ምክንያቱም አላህ ለነቢዩ ﷺ አምልኮን በኢኽላስ እንዲፈጽሙ ማዘዙ ለኡመታቸውም ሁሉ የተሰጠ ትዕዛዝ ነውና።
ከዚያም የላቀው አላህ ስለ ከሓዲዎች እንዲህ በማለት ገለፀ፦
﴿...وَٱلَّذِينَ ٱتَّخَذُواْ مِن دُونِهِۦٓ أَوۡلِيَآءَ مَا نَعۡبُدُهُمۡ إِلَّا لِيُقَرِّبُونَآ إِلَى ٱللَّهِ زُلۡفَىٰٓ...﴾
{እነዚያ ከእርሱ ሌላ ጣዖታትን ረዳቶች አድረገው የያዙት ሁሉ «ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቃርቡን በማሰብ እንጂ ለሌላ አንገዛቸዉም።»ይላሉ።} [አዝ-ዙመር: 3] ጥራት የተገባው አላህ እንዲህ ሲል መለሰላቸው፦
﴿...إِنَّ ٱللَّهَ يَحۡكُمُ بَيۡنَهُمۡ فِي مَا هُمۡ فِيهِ يَخۡتَلِفُونَۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي مَنۡ هُوَ كَٰذِبٞ كَفَّارٞ﴾
{አላህ በዚያ እነርሱ በሚለያዩበት ነገር በመካከላቸው ይፈርዳል:: አላህም ውሸታም ከሓዲ የሆነን ሰው አያቀናም::} [አዝ'ዙመር፡ 3] ጥራት የተገባው አላህ በዚህች በተከበረች አንቀፅ ከሃዲዎች ከእርሱ ሌላ ያሉ ወሊዮችን ወደ አላህ ማቃረብን እንዲያቀርቧቸው እንጅ ለሌላ እንዳልተገዟቸው ተናግሯል። ይህም የጥንቶቹም የዘመኑም ከሃዲዎች ዓላማ ነው። አላህም ይህንን በሚከተለው ቃሉ ውድቅ አድርጎታል፦
﴿...إِنَّ ٱللَّهَ يَحۡكُمُ بَيۡنَهُمۡ فِي مَا هُمۡ فِيهِ يَخۡتَلِفُونَۗ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي مَنۡ هُوَ كَٰذِبٞ كَفَّارٞ﴾
{…አላህ በዚያ እነርሱ በሚለያዩበት ነገር በመካከላቸው ይፈርዳል:: አላህም ውሸታም ከሓዲ የሆነን ሰው አያቀናም::} [አዝ-ዙመር: 3] አማልክቶቻቸው ወደ አላህ መቃረብን ያቃርቧቸዋል የሚለው ሙግታቸው ውሸት መሆኑንና ለእነርሱ ያዋሉት አምልኮም ክህደት መሆኑን አላህ ግልፅ አድርጓል። በዚህም አነስተኛ ማስተዋል ያለው ማንኛውም ሰው የቀድሞዎቹ ከሓዲዎች ክህደት ነቢያትን፣ ወሊዮችን፣ ዛፎችን፣ ድንጋዮችን እና ሌሎች ፍጡራንን በእነርሱና በአላህ መካከል አማላጅ አድርገው በመያዛቸው የመጣ መሆኑን ይገነዘባል። ልክ ሚኒስትሮች በነገሥታት ዘንድ እንደሚያማልዱት ሁሉ እነርሱም አማላጆቻቸው ያለ እርሱ ፈቃድና ውዴታ ጉዳዮቻቸውን እንደሚፈጽሙላቸው በማመን ከጉድለት ሁሉ የጠራውንና ግርማው የላቀውን አላህ ከነገሥታትና ከመሪዎች ጋር አመሳሰሉት። እንዲህም አሉ፦ ‹‹አንድ ሰው ንጉሥ ወይም አንድ መሪ ዘንድ ጉዳይ ሲኖረው በቅርብ ሰዎቹና በአማካሪዎቹ አማላጅ እንደሚያስይዝ ሁሉ እኛም እንደዚሁ ነብያቱንና ወልዮቹን በማምለክ ወደ አላህ እንቃረባለን።›› ይህ እጅግ በጣም ከንቱ ሙግት ነው፤ ምክንያቱም አላህ አምሳያ የለውም፣ ከፍጡራኑም ጋር አይነፃፀርም፣ በእርሱ ዘንድም እርሱ ለማማለድ ካልፈቀደለት በቀር ማንም አያማልድም፤ ፈቃዱንም የሚሰጠው ለተውሒድ ሰዎች እንጂ ለሌላ አይደለም፤ እርሱም በሁሉም ነገር ላይ ቻይ ነው፤ ሁሉንም ነገርም አዋቂ ነው፤ እርሱም ከአዛኞች ሁሉ ይበልጥ አዛኝ ነው፤ ማንንም አይፈራም፤ አይሰጋምም፤ ምክንያቱም አላህ ከባሮቹ ሁሉ የበላይ የሆነ ኃያል ነውና፤ በእነርሱም ላይ እንደሻው የሚወስን ነው። ንጉሶችና መሪዎች ግን በተቃራኒ በሁሉም ነገር ላይ ቻይ አይደሉም። ስለዚህም ሊያቅታቸው በሚችሉ ጉዳዮች ላይ ከሚንስትሮቻቸው፣ ከአማካሪዎቻቸውና ከወታደሮቻቸው የሚያግዟቸው ያስፈልጓቸዋል። እንዲሁም ፍላጎቱን የማያውቁለትን ሰው ጉዳይ የሚያደርስላቸው ያስፈልጋቸዋል፤ ስለሆነም ከሚኒስትሮቻቸውና ከአማካሪዎቻቸው እዝነት የሚከቱባቸውና ውዴታቸውን የሚጠይቁላቸው ያስፈልጓቸዋል። የላቀውና ከፍ ያለው ጌታ አላህ ግን ከፍጡራኑ ሁሉ የተብቃቃ ነው፤ እርሱም ለነርሱ ከእናቶቻቸው የበለጠ አዛኝ፣ ፍትሐዊ ፈራጅ፣ ነገራትን በጥበቡ፣ በዕውቀቱና በችሎታው መሠረት በየስፍራቸው የሚያስቀምጥ ነው። ከፍጡራኑ ጋር በምንም መልኩ ሊነፃፀር ፈፅሞ አይገባውም። ለዚህም አጋርያን አላህ ፈጣሪ፣ ሲሳይ ሰጪና አስተናባሪ፣ የተቸገረን ሰው ጥሪ የሚቀበል፣ መከራንም የሚያነሳ፣ ህያው የሚያደርግና የሚገድል መሆኑንና ከዚህ ውጭ ያሉትን ሌሎች የእርሱን ድርጊቶች ጭምር እንደሚያምኑ ጥራት የተገባው አላህ በመጽሐፉ ውስጥ ግልጽ አድርጓል። በእርግጥም በሙሽሪኮችና በመልእክተኞች መካከል የነበረው ሙግት አምልኮን ለአላህ በብቸኝነት በማጥራት ዙሪያ ነበር። ክብሩ የላቀው እንዲህ ብሏል፦
﴿وَلَئِن سَأَلۡتَهُم مَّنۡ خَلَقَهُمۡ لَيَقُولُنَّ ٱللَّهُ...﴾
{ማን እንደ ፈጠራቸው ብትጠይቃቸው በእርግጥ አላህ ነው ይላሉ...} [አዝ-ዙኽሩፍ፡ 87] ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿قُلۡ مَن يَرۡزُقُكُم مِّنَ ٱلسَّمَآءِ وَٱلۡأَرۡضِ أَمَّن يَمۡلِكُ ٱلسَّمۡعَ وَٱلۡأَبۡصَٰرَ وَمَن يُخۡرِجُ ٱلۡحَيَّ مِنَ ٱلۡمَيِّتِ وَيُخۡرِجُ ٱلۡمَيِّتَ مِنَ ٱلۡحَيِّ وَمَن يُدَبِّرُ ٱلۡأَمۡرَۚ فَسَيَقُولُونَ ٱللَّهُۚ فَقُلۡ أَفَلَا تَتَّقُونَ31﴾
{«ከሰማይና ከምድር ሲሳይን የሚሰጣችሁ ማን ነው? መስሚያዎችንና ማያዎችንስ የፈጠረላችሁ ማን ነው? ከሙትም ህያውን የሚያወጣ፤ ከህያዉም ሙትን የሚያወጣስ ማን ነው? ነገሩን ሁሉ የሚያስተናብርስ ማን ነው?» በላቸው:: «በእርግጥ አላህ ነው።» ይሉሃል:: «ታዲያ ለምን ታጋራላችሁ? ታዲያ አትፈሩትምን?» በላቸው።} [ዩኑስ፡ 31] በዚህ ዙሪያ የመጡ ቁርአናዊ ማስረጃዎች በርካታ ናቸው።
ቀደም ብሎ እንደተገለፀው በመልዕክተኞችና በሕዝቦቻቸው መካከል የነበረው ሙግት ዋናው ነጥብ አላህን በብቸኝነት ማምለክ እንደሆነ የሚያመላክቱ አንቀፆች ተጠቅሰዋል። ጥራት የተገባው አምላክ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَلَقَدۡ بَعَثۡنَا فِي كُلِّ أُمَّةٖ رَّسُولًا أَنِ ٱعۡبُدُواْ ٱللَّهَ وَٱجۡتَنِبُواْ ٱلطَّٰغُوتَ...﴾
{በየሕዝቡም ሁሉ ውስጥ «አላህን ተገዙ ጣዖትንም ራቁ» በማለት መልዕክተኛን በእርግጥ ልከናል...} [አን-ነሕል፡ 36] ተመሳሳይ መልዕክት ያላቸው የቁርአን አንቀፆች በርካታ ናቸው: ከጉድለት የጠራው አላህ በታላቁ መጽሐፍ ውስጥ በበርካታ ቦታዎች የምልጃን ጉዳይ አብራርቷል። ከፍ ያለው አላህ እንዲህም ብሏል፦
﴿...مَن ذَا ٱلَّذِي يَشۡفَعُ عِندَهُۥٓ إِلَّا بِإِذۡنِهِ...﴾
{…ያ እርሱ ዘንድ በፍቃዱ ቢሆን እንጂ የሚያማልድ ማን ነው?…} [አል-በቀራህ፡ 255] የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَكَم مِّن مَّلَكٖ فِي ٱلسَّمَٰوَٰتِ لَا تُغۡنِي شَفَٰعَتُهُمۡ شَيۡـًٔا إِلَّا مِنۢ بَعۡدِ أَن يَأۡذَنَ ٱللَّهُ لِمَن يَشَآءُ وَيَرۡضَىٰٓ26﴾
{በሰማያት ውስጥ ካሉ መላዕክት ብዙዎች አላህ እንዲያማልዱ ለሚሻውና ለሚወደው ሰው ያማልዱ ዘንድ ከፈቀደላቸው በኋላ እንጂ ምልጃቸው የማይፈይድ አያሌዎች ናቸው::} [አን-ነጅም፡ 26]
መላእክትንም ሲገልጽ እንዲህ ብሏል፡
﴿...وَلَا يَشۡفَعُونَ إِلَّا لِمَنِ ٱرۡتَضَىٰ وَهُم مِّنۡ خَشۡيَتِهِۦ مُشۡفِقُونَ﴾
{…ለወደደውም እንጂ ለሌላው አያማልዱም:: እነርሱም እርሱን ከመፍራታቸው የተነሳ ተጨናቂዎች ናቸው::} [አል'አንቢያእ፡ 28]
ክብሩ የላቀው አላህ ባሪያዎቹ ክህደትን ሲፈፅሙ እንደማይወድ፤ ይልቁንም የሚወድላቸው ምስጋናን እንደሆነ አሳውቋል። ምስጋና ማለት ደግሞ እርሱን መነጠልና ትእዛዙን መፈፀም ነው። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿إِن تَكۡفُرُواْ فَإِنَّ ٱللَّهَ غَنِيٌّ عَنكُمۡۖ وَلَا يَرۡضَىٰ لِعِبَادِهِ ٱلۡكُفۡرَۖ وَإِن تَشۡكُرُواْ يَرۡضَهُ لَكُمۡ...﴾
{ብትክዱ አላህ ከናንተ የተብቃቃ ነው:: ለባሪያዎቹም ክህደትን አይወድም፤ ብታመሰግኑም እርሱን ይወድላችኋል...} [አዝ-ዙመር: 7]
ቡኻሪ በሰሒሓቸው እንደዘገቡት አቡ ሁረይራ አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንዲህ ብለዋል፦ «የአላህ መልእክተኛ ሆይ! በርሶ ምልጃ ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ እድለኛው ማን ነው?»
«مَنْ قَالَ: لَا إِلهَ إِلَّا اللهُ خَالِصًا مِنْ قَلْبِهِ».
እርሳቸውም እንዲህ በማለት መለሱ: "ከልቡ አጥርቶ 'ላኢላሃ ኢለሏህ' ያለ ሰው ነው።" ወይም እንዲህ ብለዋል፡
«مِنْ نَفْسِهِ».
«ከነፍሱ አጥርቶ»።
በሶሒሕ ዘገባ አነስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንዳስተላለፉት: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
«لِكُلِّ نَبِيٍّ دَعْوَةٌ مُسْتَجَابَةٌ، فَتَعَجَّلَ كُلُّ نَبِيٍّ دَعْوَتَهُ، وَإِنِّي اخْتَبَأْتُ دَعْوَتِي شَفَاعَةً لِأُمَّتِي يَوْمَ الْقِيَامَةِ، فَهِيَ نَائِلَةٌ إِنْ شَاءَ اللَّهُ مَنْ مَاتَ مِنْ أُمَّتِي لَا يُشْرِكُ بِاللَّهِ شَيْئًا».
"ለእያንዳንዱ ነቢይ ተቀባይነት ያላት ልመና አለው። እያንዳንዱ ነቢይም በልመናው ተቻኩሏል። እኔ ግን ልመናዬን ለህዝቦቼ የትንሳኤ ቀን ምልጃ ትሆን ዘንድ ሸሽጌያታለሁ። እርሷም አላህ ከፈቀደ ከህዝቦቼ በአላህ ላይ አንዳችንም ነገር ሳያጋራ የሞተን ሰው ታገኛለች።" ተመሳሳይ ሃሳብ ያላቸው ሐዲሦች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው።
የጠቀስናቸው አንቀፆችና ሐዲሶች ባጠቃላይ የሚያመላክቱት አምልኮ የአላህ ብቻ ሐቅ መሆኑን፣ ከርሷም አንዳችንም ነገር ለነቢያትም ሆነ ለሌሎች ከአላህ ውጪ መስጠት እንደማይፈቀድ፣ እንዲሁም ምልጃ የዚያ ክብሩ ከፍ ያለው የአላህ ብቻ መሆኑን ነው። ክብሩ የጠራው (ጌታ) እንዲህ ብሏል፦
﴿قُل لِّلَّهِ ٱلشَّفَٰعَةُ جَمِيعٗا...﴾
{«ምልጃ ሁሉም የአላህ ብቻ ነው...»} [አዝ-ዙመር፡ 44] አላህ ለአማላጁ ከፈቀደለትና የሚማለደውንም ሰው ከወደደው በኋላ ካልሆነ በቀር አንድም ሰው ምልጃ አይገባውም። ቀደም ብሎ እንደተጠቀሰው አላህ ከተውሒድ በቀር አይወድም። በዚህም መሰረት፦ ሙሽሪኮች ከምልጃ ምንም ድርሻ የላቸውም። ይህንንም አላህ በላቀው ቃሉ እንዲህ በማለት አብራርቷል፦
﴿فَمَا تَنفَعُهُمۡ شَفَٰعَةُ ٱلشَّٰفِعِينَ 48﴾
{የአማላጆችም (ሁሉ) ምልጃ አትጠቅማቸዉም።} [አል-ሙደሢር፡ 48] ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿...مَا لِلظَّٰلِمِينَ مِنۡ حَمِيمٖ وَلَا شَفِيعٖ يُطَاعُ﴾
{…ለበዳዮች ምንም ወዳጅና ተሰሚ አማላጅ የላቸዉም::} [ጋፊር: 18]
በደል ተብሎ በጥቅሉ ሲጠቀስ በአላህ ማጋራት መሆኑ የሚታወቅ ነው፤ የላቀው አላህም እንዲህ ብሏል፦
﴿...وَٱلۡكَٰفِرُونَ هُمُ ٱلظَّٰلِمُونَ﴾
{…ከሓዲዎችም በዳዮች እነርሱ ናቸው::} [አል-በቀራህ: 254] ጥራት የተገባው አላህ እንዲህም ብሏል፡
﴿...إِنَّ ٱلشِّرۡكَ لَظُلۡمٌ عَظِيمٞ﴾
{…ማጋራት ታላቅ በደል ነውና።} [ሉቅማን: 13]
በጥያቄው ላይ የጠቀስከውን በተመለከተ፤ አንዳንድ ሱፊያዎች በመስጂዶችና በሌሎችም ቦታዎች ከሚሉት ንግግር ውስጥ፦ «አላህ ሆይ! የኃያልነትህ ምስጢሮች እንዲሰነጠቁና የእዝነታዊ ብርሃኖችህ እንዲፈልቁ ሰበብ ባደረከው፣ የመለኮታዊ ስፍራህ ተወካይና የዛታዊ ምስጢሮችህ ምትክ በሆነው ላይ ሶላት አውርድ፤ … ወዘተ።»
መልሱ፡ ይህ ንግግርና መሰሎቹ ከአቅም በላይ እና ወሰን ባለፈ መልኩ ራስን መጫን ውስጥ የሚመደብ ነው፤ ነቢያችን ሙሐመድም ﷺ ሙስሊም በሶሒሐቸው ከዐብደላህ ኢብኑ መስዑድ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- በዘገቡት ሐዲሥ ከዚህ ነገር አስጠንቅቀዋል። የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡
«هَلَكَ المُتَنَطِّعُونَ» قَالَهَا ثَلَاثًا.
{ወሰን አላፊዎች ጠፉ!' ሶስት ጊዜ ደጋገሟት።}
አልኢማም አል-ኸጧቢይ አላህ ይዘንላቸውና እንዲህ ብለዋል፡ አል‐ሙተነጢዕ፡ በአንድ ነገር ውስጥ በጥልቀት የሚገባ፣ እርሱን ለመመራመር ከአቅሙ በላይ የሚጣጣር፤ በማይመለከታቸውና አዕምሮአቸው በማይደርስበት ጉዳይ ውስጥ ሰምጠው በሚገቡት የአህሉል ከላም ሰዎች መንገድ የሚጓዝ ነው።
አቡ አስ-ሰዓዳት ኢብኑል-አሢር እንዲህ ብለዋል፦ እነርሱ በንግግራቸው ከመጠን በላይ የሚጨነቁና ወሰን የሚያልፉ፤ በጉሮሯቸው መጨረሻ የሚናገሩ ናቸው። ቃሉ የተወሰደው ‹አን-ነጥዕ› ከሚለው ሲሆን እርሱም የአፍ የላይኛው ዋሻ ነው። ከዚያም በንግግርም ሆነ በተግባር ወሰን ለሚያልፉ ሁሉ መጠቀሚያ ሆነ።
እነዚህ ሁለት የቋንቋ ሊቃውንት በጠቀሱት መሰረት ለአንተም ሆነ አነስተኛ ግንዛቤ ላለው ማንኛውም አካል ግልፅ እንደሚሆነው፤ በነቢያችንና በአይነታችን በአላህ መልእክተኛ ﷺ ላይ የሚደረገው ይህ የሶላትና ሰላም አፈፃፀም ከተከለከለው ራስን ከማስጨ ከአጉል ጥልቀት ውስጥ ይመደባል። በዚህ ዙሪያ ለሙስሊሙ የተደነገገው፤ በአላህ መልዕክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ላይ ሶላትና ሰላም በሚያወርድበት አፈጻጸም ላይ ከሳቸው የተረጋገጠውን መጠበቁ ነው፤ ይህም ከሌላው ነገር ሁሉ ያብቃቃል።
ከነዚህም መካከል ቡኻሪና ሙስሊም በሰሒሓቸው ከከዕብ ቢን ዑጅራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንደዘገቡት ሶሓቦች (ረዲየሏሁ ዐንሁም) እንዲህ ብለዋል፦ «የአላህ መልዕክተኛ ሆይ! አላህ በርሶ ላይ ሶላት እንድናወርድ አዞናል፤ በርሶ ላይ ሶላት የምናወርደውስ እንዴት ነው?» እርሳቸውም እንዲህ አሉ፦
«قُولُوا: اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى إِبرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ كَمَا بَارَكْتَ عَلَى إِبرَاهِيمَ وَعَلَى آلِ إِبرَاهِيمَ إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».
«በሉ፦ አላህ ሆይ! በኢብራሂምና በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ሰላት እንዳወረድክ ሁሉ በሙሐመድና በሙሐመድ ቤተሰቦች ላይም ሰላት አውርድ፡፡ አንተ ምስጉንና የላቅክ ነህና፡፡ አላህ ሆይ! በኢብራሂምና በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ እንደባረክክ ሁሉ በሙሐመድና በሙሐመድ ቤተሰቦች ላይም ባርክ፡፡ አንተ ምስጉንና የላቅክ ነህና፡፡»
በሶሒሕ ቡኻሪና ሙስሊም ከአቡ ሑመይድ አስ-ሳዒዲይ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውው - እንደተዘገበው፤ (ሶሐቦች) እንዲህ አሉ፦ «የአላህ መልክተኛ ሆይ! በርሶ ላይ ሶላት የምናወርደው እንዴት ነው?» እርሳቸውም እንዲህ አሉ፦
«قُولُوا: اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى أَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبرَاهِيمَ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى أَزْوَاجِهِ وَذُرِّيَّتِهِ كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبرَاهِيمَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ».
በሉ፡ “«አልላሁመ ሰሊ ዐላ ሙሐመድ ወዐላ አዝዋጂሂ ወዙርሪያቲሂ ከማ ሰለይተ ዐላ ኣሊ ኢብራሂም፣ ወባሪክ ዐላ ሙሐመድ ወዐላ አዝዋጂሂ ወዙርሪያቲሂ ከማ ባረክተ ዐላ ኣሊ ኢብራሂም፣ ኢንነከ ሐሚዱን መጂድ።»” (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ውዳሴህን እንዳወረድክ ሁሉ በሙሐመድ፣ በሚስቶቻቸውና በዝርዮቻቸው ላይም ውዳሴህን አውርድ፤ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ በረከትህን እንዳሰፈንክ ሁሉ በሙሐመድ፣ በሚስቶቻቸውና በዝርዮቻቸው ላይም በረከትህን አውርድ። አንተ ምስጉንና የላቅክ ነህና።) ማለት ነው።
በሶሒሕ ሙስሊም ከአቢ መስዑድ አል-አንሷሪ ረዲየሏሁ ዐንሁ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድለላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ፡ በሺር ኢብኑ ሰዕድ «የአላህ መልክተኛ ሆይ! አላህ በርሶ ላይ ሶላት እንድናወርድ አዞናል። በርሶ ላይ ሶላት የምናወርደውስ እንዴት ነው?» አላቸው። እርሳቸውም ዝም አሉና ከዚያም እንዲህ አሉ፡
«قُولُوا: اللَّهُمَّ صَلِّ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ؛ كَمَا صَلَّيْتَ عَلَى آلِ إِبرَاهِيمَ، وَبَارِكْ عَلَى مُحَمَّدٍ وَعَلَى آلِ مُحَمَّدٍ؛ كَمَا بَارَكْتَ عَلَى آلِ إِبرَاهِيمَ فِي العَالَمِينَ، إِنَّكَ حَمِيدٌ مَجِيدٌ، وَالسَّلَامُ كَمَا عَلِمتُم».
«በሉ፡ “አልላሁመ ሰሊ ዐላ ሙሐመድ ወዐላ ኣሊ ሙሐመድ፤ ከማ ሰለይተ ዐላ ኣሊ ኢብራሂም፣ ወባሪክ ዐላ ሙሐመድ ወዐላ ኣሊ ሙሐመድ፤ ከማ ባረክተ ዐላ ኣሊ ኢብራሂም ፊል ዓለሚን፣ ኢንነከ ሐሚዱን መጂድ።” (ትርጉሙም፡ አላህ ሆይ! በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ ውዳሴህን እንዳወረድክ ሁሉ በሙሐመድና በቤተሰቦቻቸው ላይም ውዳሴህን አውርድ፤ በኢብራሂም ቤተሰቦች ላይ በአለማት ውስጥ በረከትህን እንዳሰፈንክ ሁሉ በሙሐመድና በቤተሰቦቻቸው ላይም በረከትህን አውርድ፤ አንተ ምስጉንና የላቅክ ነህና።) ሰላምታውም እንዳወቃችሁት ነው።»
እነዚህ እና መሰል ከነቢዩ ﷺ የተረጋገጡ ቃላቶች አንድ ሙስሊም በአላህ መልዕክተኛ ﷺ ላይ ሰላትና ሰላም ሲያወርድ ሊጠቀምባቸው የሚገቡ ናቸው፤ ምክንያቱም የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ለእርሳቸው ክብር የሚገባውን ነገር ከሰዎች ሁሉ የበለጠ የሚያውቁ ናቸውና። እንዲሁም ለጌታቸው ውዳሴም ሊውሉ የሚገቡ ቃላትንም ከሰዎች ሁሉ የበለጠ የሚያውቁ ናቸው።
ከአቅም በላይ የተጣጣሩባቸውና አዲስ የተፈጠሩ ቃላቶች፣ እንዲሁም ትክክል ያልሆነ ትርጉም ሊይዙ የሚችሉ ቃላቶችን ለምሳሌ በጥያቄው ላይ እንደተጠቀሱት ያሉትን መጠቀም ተገቢ አይደለም። ምክንያቱም በውስጣቸው ከአቅም በላይ መጣጣርን ስለያዙ፣ ውድቅ በሆኑ ትርጉሞችም ሊተረጎሙ ስለሚችሉ፣ እንዲሁም የአላህ መልዕክተኛ ﷺ ከመረጧቸውና ኡመታቸውንም ወደ እነርሱ ከጠቆሙባቸው ቃላቶች ጋር የሚቃረኑ በመሆናቸው ነው። እርሳቸው ከፍጡራን ሁሉ የበለጠ አዋቂ፣ ለእነርሱም የበለጠ መካሪና ከአቅም በላይ ከመጣጣርም የበለጠ የራቁ ናቸው። የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን።
በዚህም የተውሒድን ምንነትና የሽርክን ምንነት፣ በፊተኞቹና በኋለኞቹ ሙሽሪኮች መካከል በዚህ ጉዳይ ላይ የነበረውን ልዩነት፣ እንዲሁም በአላህ መልእክተኛ - የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - ላይ ስለሚደረገው ትክክለኛ የሰላት አፈጻጸም ለማብራራት የጠቀስናቸው ማስረጃዎች ለሐቅ ፈላጊ በቂና አሳማኝ እንደሚሆኑ ተስፋ አደርጋለሁ። እውነትን ለማወቅ ፍላጎት የሌለው ሰው ግን ስሜቱን ተከታይ ነው፤ ልቅናው ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿فَإِن لَّمۡ يَسۡتَجِيبُواْ لَكَ فَٱعۡلَمۡ أَنَّمَا يَتَّبِعُونَ أَهۡوَآءَهُمۡۚ وَمَنۡ أَضَلُّ مِمَّنِ ٱتَّبَعَ هَوَىٰهُ بِغَيۡرِ هُدٗى مِّنَ ٱللَّهِۚ إِنَّ ٱللَّهَ لَا يَهۡدِي ٱلۡقَوۡمَ ٱلظَّٰلِمِينَ50﴾
{እሺ ባይሉህም የሚከተሉት ዝንባሌዎቻቸውን ብቻ መሆኑን ዕወቅ፤ ከአላህም የሆነ መመሪያ ሳይኖረው ዝንባሌውን ብቻ ከተከተለ ሰው ይበልጥ የጠመመ አንድም የለም፤ አላህ በደለኞች ህዝቦችን አይመራምና::} [አልቀሶስ፡ 50]
አላህ በዚህች በተከበረች አንቀፅ ሰዎች አላህ ነቢዩ ሙሐመድን ﷺ ከላከበት ቅን መመሪያና እውነተኛ ሀይማኖት አንፃር ለሁለት እንደሚከፈሉ ገለፀ፦
አንደኛው፡ ለአላህና ለመልክተኛው ታዛዥ ነው።
ሁለተኛውም፡ የስሜቱ ተከታይ ነው፤ ቀጥሎም ከአላህ መመሪያ ውጭ ስሜቱን ከተከተለ ሰው የበለጠ የጠመመ እንደሌለ ተናገረ።
ታላቅና የላቀ የሆነውን አላህ ስሜትን ከመከተል እንዲጠብቀን፣ እኛንም ሆነ እናንተንም እንዲሁም ሌሎችንም ወንድሞቻችንን ለአላህና ለመልእክተኛው ﷺ ጥሪ ምላሽ ከሚሰጡት፣ ሸሪዓውን ከሚያልቁት፣ ሸሪዓውንም ከሚቃረኑ ቢድዓዎችና ስሜታዊ ዝንባሌዎች ሁሉ ከሚያስጠነቅቁት እንዲያደርገን እንማፀነዋለን። እርሱ ቸርና ለጋስ ነውና።
የአላህ ሰላትና ሰላም በባሪያውና መልዕክተኛው በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እና እስከ ትንሳኤ ቀን ድረስ በመልካም በተከተሏቸው ላይ ሁሉ ይስፈን።
***
am397v4.0 - 21/04/2026