بَيَانُ كُفْرِ وَضَلَالِ مَنْ زَعَمَ أَنَّهُ يَجُوزُ لِأَحَدٍ الخُرُوجُ مِنْ شَرِيعَةِ مُحَمَّدٍ ﷺ
ከነቢዩ ሙሐመድ ﷺ ሸሪዓ መውጣት ይፈቀዳል ብሎ የሚሞግት ሰው እንደካደ እና እንደጠመመ ማብራሪያ
لِسَمَاحَةِ الشَّيْخِ العَلَّامَةِ
عَبْدِ العَزِيزِ بْنِ عَبْدِ اللهِ بْنِ بَازٍ
رَحِمَهُ اللهُ
ዝግጅት፦ የተከበሩ ሸይኽ
ዐብዱልዐዚዝ ቢን ዐብደላህ ቢን ባዝ
بِسْمِ اللهِ الرَّحمَنِ الرَّحِيمِ
አስራ ሁለተኛው መልእክት:
ከነቢዩ ሙሐመድ ﷺ ሸሪዓ መውጣት ይፈቀዳል ብሎ የሚሞግት ሰው እንደካደ እና እንደጠመመ ማብራሪያ
ምስጋና ሁሉ የዓለማት ጌታ ለሆነው አላህ የተገባ ነው። ሶላትና ሰላም በነቢያትና መልክተኞች መደምደሚያ በሆኑት ነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸውና በባልደረቦቻቸውም ላይ ሁሉ ይስፈን።
በመቀጠል፦ በአሽ-ሸርቅ አል-አውሰጥ ጋዜጣ በቀን 5/6/1415 ዓ.ሂ በወጣው ቁጥር (5824) እትሙ ላይ፣ ራሱን ዐብዱልፈታሕ አል-ሓይክ ብሎ በሰየመው ሰው “የተሳሳተ ግንዛቤ” በሚል ርዕስ የተጻፈውን ጽሑፍ ተመልክቼዋለሁ።
የጽሑፉ ማጠቃለያ፡ በእስልምና ሃይማኖት በግልፅ መረጃና በዑለማዎች ባጠቃላይ የጋራ ስምምነት ሙስሊም በመሆን ብቻ የግዴታ የሚታወቅን ጉዳይ ማውገዙ ነው። ይኸውም የሙሐመድ ﷺ ተልዕኮ ለሁሉም ሰዎች አጠቃላይ መሆኑን በማስተባበል ሙሐመድን ﷺ ያልተከተለና ያልታዘዛቸው፣ ይልቁንም አይሁድ ወይም ክርስቲያን ሆኖ የቀረ ሰው በትክክለኛ ሃይማኖት ላይ ነው ብሎ መሞገቱ ነው፤ ከዛም አልፎ ከሓዲዎችንና ዓመፀኞችን በመቅጣት ባለው የዓለማት ጌታ (ጥራት ይገባውና) ጥበብ ላይ ድንበር ማለፉና ይህንንም ከንቱ ድርጊት እና ጨዋታ አድርጎ መቁጠሩ ነው።
ይህ ግለሰብ ሸሪዓዊ ማስረጃዎችን አጣምሞ አቅርቧል፣ ከአውዳቸውም ውጭ አስቀምጧቸዋል፤ ስሜቱ በሚያዘውም መልኩ ተርጉሟቸዋል። የሙሐመድ ﷺ መልዕክት ሁሉን አቀፍ መሆኑን፣ ስለ እርሳቸው ሰምቶ ያልተከተለ ሰው ካፊር መሆኑን፣ አላህም ከእስልምና ውጭ ሌላ ሃይማኖትን እንደማይቀበልና የመሳሰሉትን የሚያመለክቱ ግልፅ የሆኑ ሸሪዓዊ ማስረጃዎችንና ጽሑፎችን ቸል ብሏል፤ ይህም መሃይማኖች በንግግሩ እንዲታለሉ ነው። ይህ የፈጸመው ድርጊት ግልጽ ክህደት፣ ከእስልምና መውጣት፣ እንዲሁም ከጉድለት የጠራውንና ከፍ ያለውን አላህንና መልእክተኛውን ﷺ ማስተባበል ነው፤ ይህንንም ከእውቀትና ከኢማን ባለቤቶች ውስጥ ጽሑፉን ያነበበ ሰው ሁሉ ያውቀዋል።
የአገሪቱ ገዢ ያለበት ግዴታ ተውበት እንዲያደርግ እንዲጠየቅና በንፁሁ ሸሪዓ በተደነገገው መሰረት እንዲፈረድበትም ወደ ፍርድ ቤት ማቅረብ ነው።
የላቀው አላህም የሙሐመድ ﷺ መልእክተኝነት አጠቃላይ መሆኑን፣ እርሳቸውን መከተል ለሰውና ለጋኔን ባጠቃላይ ግዴታ መሆኑን በእርግጥ ገልጿል። ይህንንም ከሙስሊሞች መካከል ትንሽም ቢሆን እውቀት ያለው ሰው አይሰወርበትም።
የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿قُلۡ يَٰٓأَيُّهَا ٱلنَّاسُ إِنِّي رَسُولُ ٱللَّهِ إِلَيۡكُمۡ جَمِيعًا ٱلَّذِي لَهُۥ مُلۡكُ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِۖ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا هُوَ يُحۡيِۦ وَيُمِيتُۖ فَـَٔامِنُواْ بِٱللَّهِ وَرَسُولِهِ ٱلنَّبِيِّ ٱلۡأُمِّيِّ ٱلَّذِي يُؤۡمِنُ بِٱللَّهِ وَكَلِمَٰتِهِۦ وَٱتَّبِعُوهُ لَعَلَّكُمۡ تَهۡتَدُونَ158﴾
{(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) «እናንተ ሰዎች ሆይ! እኔ ወደ እናንተ ወደ ሁላችሁም የአላህ መልዕክተኛ ነኝ:: እርሱም ያ የሰማያትና የምድር ንግስና ለእርሱ ብቻ የሆነ ነው:: እርሱ እንጂ ሌላ አምላክ የለም:: ህያው ያደርጋል:: ይገድላልም:: በአላህ በዚያም በአላህና በቃላቶቹ በሚያምነው የማይጽፍ የማያነብ ነቢይ በሆነው መልዕክተኛውም እመኑ:: ወደ ቅኑ መንገድ ትመሩ ዘንድም ተከተሉት።» በላቸው::} [አል‐አዕራፍ: 158] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿...وَأُوحِيَ إِلَيَّ هَٰذَا ٱلۡقُرۡءَانُ لِأُنذِرَكُم بِهِۦ وَمَنۢ بَلَغَ...﴾
{…ይህም ቁርኣን እናንተንና የደረሰውን ሰው ሁሉ በርሱ ላስፈራራበት ወደኔ ተወረደ።…} [አልአንዓም፡ 19] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿قُلۡ إِن كُنتُمۡ تُحِبُّونَ ٱللَّهَ فَٱتَّبِعُونِي يُحۡبِبۡكُمُ ٱللَّهُ وَيَغۡفِرۡ لَكُمۡ ذُنُوبَكُمۡۚ وَٱللَّهُ غَفُورٞ رَّحِيمٞ31﴾
{(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!)፡- «አላህን የምትወዱ እንደሆናችሁ እኔን ተከተሉኝ:: አላህም ይወዳችኋል፤ ኃጢአቶቻችሁንም ለእናንተ ይምራልና:: አላህ መሀሪና አዛኝ ነውና።» በላቸው።} [አሊ ዒምራን: 31] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿وَمَن يَبۡتَغِ غَيۡرَ ٱلۡإِسۡلَٰمِ دِينٗا فَلَن يُقۡبَلَ مِنۡهُ وَهُوَ فِي ٱلۡأٓخِرَةِ مِنَ ٱلۡخَٰسِرِينَ85﴾
{ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከእርሱ ተቀባይነት የለዉም:: እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው::} [አሊ-ዒምራን፡ 85] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿وَمَآ أَرۡسَلۡنَٰكَ إِلَّا كَآفَّةٗ لِّلنَّاسِ بَشِيرٗا وَنَذِيرٗا...﴾
{አንተንም ለሰዎች ሁሉ በመላ አብሳሪና አስፈራሪ አድርገን ቢሆን እንጂ አልላክንህም...} [ሰበእ፡ 28] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿وَمَآ أَرۡسَلۡنَٰكَ إِلَّا رَحۡمَةٗ لِّلۡعَٰلَمِينَ107﴾
{(መልዕክተኛችን ሙሐመድ ሆይ!) ለዓለማት እዝነት አድርገን እንጂ አልላክንህም::} [አል-አንቢያእ: 107] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿...وَقُل لِّلَّذِينَ أُوتُواْ ٱلۡكِتَٰبَ وَٱلۡأُمِّيِّـۧنَ ءَأَسۡلَمۡتُمۡۚ فَإِنۡ أَسۡلَمُواْ فَقَدِ ٱهۡتَدَواْۖ وَّإِن تَوَلَّوۡاْ فَإِنَّمَا عَلَيۡكَ ٱلۡبَلَٰغُۗ وَٱللَّهُ بَصِيرُۢ بِٱلۡعِبَادِ﴾
{ለእነዚያም መጽሐፉን ለተሰጡት ሰዎችና ለመሐይሞቹ፡- «ሰለማችሁን?» በላቸው:: ቢሰልሙም በእርግጥ (ወደቀናው መንገድ) ተመሩ:: እምቢ ቢሉ ግን ባንተ ላይ ያለብህ ማድረስ ብቻ ነው:: አላህም ባሮቹን ተመልካች ነው።} [አሊ-ዒምራን: 20] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿تَبَارَكَ ٱلَّذِي نَزَّلَ ٱلۡفُرۡقَانَ عَلَىٰ عَبۡدِهِۦ لِيَكُونَ لِلۡعَٰلَمِينَ نَذِيرًا1﴾
{ያ ፉርቃንን በባሪያው ላይ ለዓለማት አስፈራሪ ይሆን ዘንድ ያወረደው (አምላክ) ክብርና ጥራት ተገባው።} [አል-ፉርቃን: 1]
ቡኻሪና ሙስሊምም ከጃቢር (ረዲየላሁ ዐንሁ) እንደዘገቡት ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«أُعْطِيتُ خَمْسًا لَمْ يُعْطَهُنَّ أَحَدٌ قَبْلِي: نُصِرْتُ بِالرُّعْبِ مَسِيرَةَ شَهْرٍ، وَجُعِلَتْ لِيَ الْأَرْضُ مَسْجِدًا وَطَهُورًا، فَأَيُّمَا رَجُلٍ مِنْ أُمَّتِي أَدْرَكَتْهُ الصَّلَاةُ، فَلْيُصَلّ، وَأُحِلَّتْ لِيَ الْمَغَانِمُ، وَلَمْ تُحَلَّ لِأَحَدٍ قَبْلِي، وَأُعْطِيتُ الشَّفَاعَةَ، وَكَانَ النَّبِيُّ يُبْعَثُ إِلَى قَوْمِهِ خَاصَّةً، وَبُعِثْتُ إِلَى النَّاسِ عَامَّةً».
"ከኔ በፊት አንድም አካል ያልተሰጠው አምስት ነገሮችን ለኔ ተሰጥተውኛል፤ የወር መንገድ ሲቀር (ጠላቶች ውስጥ) ፍርሃት በመክተት ተረድቻለሁ፤ ምድር ለኔ መስገጃም ንፅህና መጠበቂያም ተደርጋልኛለች፤ ስለዚህ ከኡመቴ ማንኛውም ሰው ሶላት ከደረሰችበት ይስገድ። ምርኮ ለኔ ተፈቅዷል፤ ከኔ በፊት ለአንድም አካል አልተፈቀደችም። ምልጃ ተሰጥቶኛል። ነቢይ የሚላከው ወደ ህዝቦቹ ብቻ ነበር። እኔ ግን ወደ ሰው ባጠቃላይ ተልኬያለሁ።"
ይህም የነቢያችን ሙሐመድ ﷺ መልክተኝነት ለሰው ልጆች ሁሉ አጠቃላይና ሁሉን አቀፍ መሆኑን፣ የቀድሞ ድንጋጌዎችን በሙሉ መሻሩንና እርሳቸውን ያልተከተለና ያልታዘዘ ሰውም ከሃዲና አመጸኛ በመሆኑ ቅጣቱ የሚገባው መሆኑን በግልጽ የሚያሳይ ነው። አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿...وَمَن يَكۡفُرۡ بِهِۦ مِنَ ٱلۡأَحۡزَابِ فَٱلنَّارُ مَوۡعِدُهُۥ...﴾
{…ከአህዛቦቹ በእርሱ የሚክድ ሰው መመለሻው እሳት ናት…} [ሁድ፡ 17] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿...فَلۡيَحۡذَرِ ٱلَّذِينَ يُخَالِفُونَ عَنۡ أَمۡرِهِۦٓ أَن تُصِيبَهُمۡ فِتۡنَةٌ أَوۡ يُصِيبَهُمۡ عَذَابٌ أَلِيمٌ﴾
{…እነዚያም ትእዛዙን የሚጥሱ መከራ እንዳትደርስባቸው ወይም አሳማሚ ቅጣት እንዳያገኛቸው ይጠንቀቁ::} [አን-ኑር፡ 63] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿وَمَن يَعۡصِ ٱللَّهَ وَرَسُولَهُۥ وَيَتَعَدَّ حُدُودَهُۥ يُدۡخِلۡهُ نَارًا خَٰلِدٗا فِيهَا وَلَهُۥ عَذَابٞ مُّهِينٞ14﴾
{አላህንና መልዕክተኛውንም የሚያምጽ ወሰኖቹንም የሚተላለፍ በውስጧ ዘውታሪ ሲሆን እሳት ያስገባዋል:: ለእርሱም አዋራጅ ቅጣት አለበት።} [አንኒሳእ፡ 14] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿...وَمَن يَتَبَدَّلِ ٱلۡكُفۡرَ بِٱلۡإِيمَٰنِ فَقَدۡ ضَلَّ سَوَآءَ ٱلسَّبِيلِ﴾
{…በእምነት ክህደትን የሚለውጥ ሰው በእርግጥ ትክክለኛውን መንገድ ስቷል፡፡} [አል-በቀራ፡ 108] በዚህ ዙሪያ የመጡ ቁርአናዊ ማስረጃዎች በርካታ ናቸው።
ጥራት የተገባው አላህ መልዕክተኛውን ﷺ መታዘዝ ከራሱ መታዘዝ ጋር አቆራኝቷል፤ እንዲሁም ከኢስላም ሌላን ሃይማኖት አድርጎ የያዘ ሰው ከሳሪ መሆኑንና ከእርሱ ምንም ዓይነት ግዴታም ትርፍ አምልኮዎቹን እንደማይቀበል አብራርቷል። የላቀው አላህ እንዲህ ብሏል፦
﴿وَمَنْ يَبْتَغِ غَيْرَ الْإِسْلَامِ دِينًا فَلَنْ يُقْبَلَ مِنْهُ وَهُوَ فِي الْآخِرَةِ مِنَ الْخَاسِرِينَ 85﴾
{ከኢስላም ሌላ ሃይማኖትን የሚፈልግ ሰው ፈጽሞ ከእርሱ ተቀባይ የለዉም:: እርሱም በመጨረሻይቱ ዓለም ከከሳሪዎቹ ነው::} [አሊ-ዒምራን፡ 85] ጥራት ይገባውና እንዲህም ብሏል፡
﴿مَنْ يُطِعِ الرَّسُولَ فَقَدْ أَطَاعَ اللَّهَ...﴾
{መልዕክተኛውን የሚታዘዝ ሁሉ በእርግጥ አላህን ታዘዘ::} [አን-ኒሳእ፡ 80] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿قُلْ أَطِيعُوا اللَّهَ وَأَطِيعُوا الرَّسُولَ فَإِنْ تَوَلَّوْا فَإِنَّمَا عَلَيْهِ مَا حُمِّلَ وَعَلَيْكُمْ مَا حُمِّلْتُمْ وَإِنْ تُطِيعُوهُ تَهْتَدُوا...﴾
{«አላህን ታዘዙ፤ መልዕክተኛውንም ታዘዙ:: ብትሸሹም አትጎዱትም:: በእርሱ ላይ ያለበት የተገደደውን ማድረስ ብቻ ነው:: በእናንተም ላይ ያለባችሁ የተገደዳችሁትን መታዘዝ ብቻ ነው:: ብትታዘዙትም ትመራላችሁ።» በላቸው።} [አን-ኑር፡ 54] የላቀው አሏህ እንዲህ ብሏል:
﴿إِنَّ الَّذِينَ كَفَرُوا مِنْ أَهْلِ الْكِتَابِ وَالْمُشْرِكِينَ فِي نَارِ جَهَنَّمَ خَالِدِينَ فِيهَا أُولَئِكَ هُمْ شَرُّ الْبَرِيَّةِ 6﴾
{እነዚያ ከመጽሐፉ ሰዎች የካዱት፣ አጋሪዎቹም በገሀነም እሳት ውስጥ ናቸው:: በውስጧ ዘውታሪዎች ሲሆኑ እነዚያ እነርሱ ከፍጥረት ሁሉ መጥፎዎቹ እነርሱ ናቸው::} [አል-በይናህ፡ 6]
ሙስሊም በሶሒሓቸው እንዳስተላለፉት የአላህ መልዕክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«وَالَّذِي نَفْسِي بِيَدِهِ؛ لَا يَسْمَعُ بِي أَحَدٌ مِنْ هَذِهِ الْأُمَّةِ، يَهُودِيٌّ وَلَا نَصْرَانِيٌّ، ثُمَّ يَمُوتُ وَلَمْ يُؤْمِنْ بِالَّذِي أُرْسِلْتُ بِهِ؛ إِلَّا كَانَ مِنْ أَهْلِ النَّارِ».
"ያ ነፍሴ በእጁ በሆነችው ጌታ እምላለሁ! ከዚህ ኡመት ውስጥ አንድም አይሁድ ይሁን ክርስቲያን ስለኔ ሰምቶ ከዚያም በዛ በተላኩበት ሳያምን የሚሞት የለም፤ ከእሳት ሰዎች መካከል ቢሆን እንጂ።"
የአላህ መልዕክተኛም ﷺ ወደ እስልምና እምነት ያልገባን ሰው ሃይማኖት ውድቅ መሆኑን በተግባራቸውና በንግግራቸው ገልፀዋል። ከክርስቲያኖችና አይሁዶች ውጪ ያሉ ከሃዲያንን እንደተዋጉ ሁሉ አይሁዶችንና ክርስቲያኖችንም ተዋግቷል። ከነርሱ መካከል ጂዝያ የሰጡትነ ተቀብለዋል። ይህም የሆነው ጥሪው (ዳዕዋው) ወደ ቀሪዎቹ ህዝቦቻቸው ከመድረስ እንዳይከለክሉና እንዲሁም ከነርሱ መካከል ወደ እስልምና መግባት የፈለገ ሰው ህዝቦቹ ያቅቡኛል፣ ይከለክሉኛል ወይም ይገድሉኛል ብሎ ሳይፈራ ወደ እስልምና እንዲገባ ነው።
ቡኻሪና ሙስሊም ከአቡ ሁረይራ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) እንደዘገቡት እንዲህ ብለዋል፦ «እኛ መስጂድ ውስጥ ሳለን የአላህ መልክተኛ ﷺ በመውጣት እንዲህ አሉ፦»
«انْطَلِقُوا إِلَى يَهُودَ، فَخَرَجْنَا مَعَهُ حَتَّى جِئْنَا بَيْتَ الْمِدْرَاسِ، فَقَامَ النَّبِيُّ ﷺ، فَنَادَاهُمْ فَقَالَ :يَا مَعْشَرَ يَهُودَ، أَسْلِمُوا تَسْلَمُوا، فَقَالُوا: قَدْ بَلَّغْتَ يَا أَبَا الْقَاسِمِ، فَقَالَ لَهُمْ رَسُولُ اللَّهِ ﷺ: ذَلِكَ أُرِيدُ، أَسْلِمُوا تَسْلَمُوا، فَقَالُوا: قَدْ بَلَّغْتَ يَا أَبَا الْقَاسِمِ، فَقَالَ لَهُمْ رَسُولُ اللَّهِ ﷺ: ذَلِكَ أُرِيدُ، ثُمَّ قَالَهَا الثَّالِثَةَ...».
«"ወደ አይሁዶች ተጓዙ።" እናም ከእርሳቸው ጋር ወጥተን ቤተ አምልኳቸው ደረስን። ነቢዩም ﷺ ቆመው ጠሯቸውና እንዲህ አሉ፦ «እናንተ አይሁዶች ሆይ! ስለሙ፤ ትድናላችሁ።» እነርሱም፦ «አቡል ቃሲም ሆይ! በእርግጥ አድርሰሃል» አሉ። የአላህ መልክተኛም ﷺ፦ «የምፈልገው ይህንኑ ነው። ስለሙ፤ ትድናላችሁ» አሏቸው። እነርሱም፦ «አቡል ቃሲም ሆይ! በእርግጥ አድርሰሃል» አሉ። የአላህ መልክተኛም ﷺ፦ «የምፈልገው ይህንኑ ነው» አሉ፤ ከዚያም ለሶስተኛ ጊዜ ይህንኑ ደገሙት...» ሐዲሥ።
ዋናው የሐዲሡ ፍሬ ሃሳብ፡ እርሳቸው ﷺ የአይሁዶች የሃይማኖት ሰዎች ዘንድ ትምህርት ቤታቸው ድረስ ሄደው ወደ እስልምና ጠሯቸው፤ እንዲህም አሏቸው፡ «ስለሙ፤ ትድናላችሁ»። ይህንንም ደጋግመው ነገሯቸው።
በተመሳሳይም ወደ ሒረቅል ደብዳቤ ልከው ወደ እስልምና ጠሩት፤ እምቢተኛ ከሆነም እርሱ እምቢተኛ በመሆኑ ምክንያት ከእስልምና የታቀቡትን ሰዎች ኃጢአት እንደሚሸከም አሳወቁት። ቡኻሪና ሙስሊም እንደዘገቡት፤ ሒረቅል የአላህ መልዕክተኛን ﷺ ደብዳቤ አስጠርቶ አነበበው፤ በውስጡም እንዲህ የሚል ነበር፦
«بِسْمِ اللَّهِ الرَّحْمَنِ الرَّحِيمِ، مِنْ مُحَمَّدٍ رَسُولِ اللَّهِ إِلَى هِرَقْلَ عَظِيمِ الرُّومِ، سَلَامٌ عَلَى مَنِ اتَّبَعَ الْهُدَى، أَمَّا بَعْدُ: فَإِنِّي أَدْعُوكَ بِدِعَايَةِ الْإِسْلَامِ، أَسْلِمْ تَسْلَمْ، وَأَسْلِمْ يُؤْتِكَ اللَّهُ أَجْرَكَ مَرَّتَيْنِ، فَإِنْ تَوَلَّيْتَ، فَإِنَّ عَلَيْكَ إِثْمَ الْأَرِيسِيِّينَ وَ
"በአላህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ በጣም አዛኝ በሆነው። ከአላህ መልዕክተኛ ሙሐመድ የሮም ታላቅ ለሆነው ሂረቅል፤ ቅኑን መንገድ በተከተለ ላይ ሰላም ይስፈን። ከዚህ በመቀጠል፡ የእስልምናን ጥሪ አቀርብልሃለሁ። ስለም፤ ሰላም ታገኛለህ፤ እስልምናን ብትቀበል አላህ ምንዳህን ሁለት ጊዜ ይሰጥሃል። ከዚህ ጀርባህን ብትሰጥ ግን፣ የተከታዮችህ ኃጢያት ባንተ ላይ ይሆናል።"
﴿يَٰٓأَهۡلَ ٱلۡكِتَٰبِ تَعَالَوۡاْ إِلَىٰ كَلِمَةٖ سَوَآءِۭ بَيۡنَنَا وَبَيۡنَكُمۡ أَلَّا نَعۡبُدَ إِلَّا ٱللَّهَ وَلَا نُشۡرِكَ بِهِۦ شَيۡـٔٗا وَلَا يَتَّخِذَ بَعۡضُنَا بَعۡضًا أَرۡبَابٗا مِّن دُونِ ٱللَّهِۚ فَإِن تَوَلَّوۡاْ فَقُولُواْ ٱشۡهَدُواْ بِأَنَّا مُسۡلِمُونَ64﴾
{የመጽሐፉ ባለቤቶች ሆይ! በእኛና በእናንተ መካከል ትክክል ወደ ሆነችው ቃል ኑ። (እርሷም) ‹አላህን ብቻ እንጂ ሌላን ላንገዛ፤ በእርሱም ምንንም ላናጋራ፤ ከፊላችንም ከፊሉን ከአላህ ሌላ አማልክት አድርጎ ላይዝ› ነው።» በላቸው። እምቢ ካሉም «እኛ ሙስሊሞች መሆናችንን መስክሩ።» በሏቸው።} [አሊ-ዒምራን፡ 64]»
ከዚያም ፊታቸውን አዙረው ወደ እስልምና ለመግባት እምቢ ባሉ ጊዜ፤ እርሳቸው ﷺ እና ሶሓቦቻቸው - አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - ተዋጓቸው፤ ጂዝያንም በላያቸው ላይ ጣሉባቸው።
እነርሱ በጥመት ላይ መሆናቸውንና ሃይማኖታቸውም በነብዩ ሙሐመድ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሃይማኖት ከተሻረ በኋላ የሐሰት መሆኑን ለማረጋገጥ፤ አላህ አንድ ሙስሊም በየቀኑ፣ በየሰላቱ እና በየረከዓው ትክክለኛና ተቀባይነት ወዳለው ወደ ቀጥተኛው መንገድ እንዲመራው እንዲጠይቀው አዟል፤ እሱም እስልምና ነው። እንዲሁም በጥመት ላይ መሆናቸውን እያወቁ በርሱ ላይ የሚፀኑ ከሆኑት አይሁዶችና መሰሎቻቸው አላህ ከተቆጣባቸው ሰዎች መንገድ እንዲያርቀው እንዲጠይቀው አዟል፤ ከነዚያ ያለ ዕውቀት ከሚገዙት፤ እነርሱ በመሳሳት መንገድ ላይ ሆነው ሳለ በቅን መንገድ ላይ እንደሆኑ ከሚሞግቱት የተሳሳቱ ሰዎች መንገድ እንዲያርቀው እንዲጠይቀው አዟል። እነርሱም፡ ክርስቲያኖችና ከሌሎች ህዝቦችም ሆነው በመሳሳትና ባለማወቅ እየተገዙ እነርሱን የሚመሳሰሉ ሁሉ ናቸው። ይህም ሁሉ ሙስሊም ከእስልምና ውጭ ያለ ማንኛውም ሃይማኖት ውድቅ መሆኑን እና ከእስልምና ውጭ በሆነ መንገድ አላህን የሚያመልክ ሁሉ የጠመመ መሆኑን በእርግጠኝነት እንዲያውቅ ነው። ይህን ያላመነ ሰው ከሙስሊሞች አይደለም። በዚህ ርዕስ ዙሪያ ከቁርኣንና ከሐዲሥ የመጡ ማስረጃዎች በርካታ ናቸው።
በመሆኑም በጽሑፉ ባለቤት -በአብዱል ፈታህ- ላይ ግዴታው፦ ወደ ንፁህ ተውበት መቻኮል እና ተውባውን የሚገልጽበትን ጽሑፍ መጻፍ ነው። ወደ አላህ እውነተኛ ተውበት በማድረግ የተመለሰ ሰው አላህ ጸጸቱን ይቀበለዋል፤ ጥራት የተገባው አላህ እንዲህ ብሏልና፦
﴿...وَتُوبُوٓاْ إِلَى ٱللَّهِ جَمِيعًا أَيُّهَ ٱلۡمُؤۡمِنُونَ لَعَلَّكُمۡ تُفۡلِحُونَ﴾
{…ምዕመናኖች ሆይ! ትድኑ ዘንድ ሁላችሁም ወደ አላህ ተጸጸቱ::} (አን-ኑር 31) የላቀው አላህ እንዲህም ይላል፦
﴿وَٱلَّذِينَ لَا يَدۡعُونَ مَعَ ٱللَّهِ إِلَٰهًا ءَاخَرَ وَلَا يَقۡتُلُونَ ٱلنَّفۡسَ ٱلَّتِي حَرَّمَ ٱللَّهُ إِلَّا بِٱلۡحَقِّ وَلَا يَزۡنُونَۚ وَمَن يَفۡعَلۡ ذَٰلِكَ يَلۡقَ أَثَامٗا68 يُضَٰعَفۡ لَهُ ٱلۡعَذَابُ يَوۡمَ ٱلۡقِيَٰمَةِ وَيَخۡلُدۡ فِيهِۦ مُهَانًا69 إِلَّا مَن تَابَ وَءَامَنَ وَعَمِلَ عَمَلٗا صَٰلِحٗا فَأُوْلَٰٓئِكَ يُبَدِّلُ ٱللَّهُ سَيِّـَٔاتِهِمۡ حَسَنَٰتٖۗ وَكَانَ ٱللَّهُ غَفُورٗا رَّحِيمٗا70﴾
{[እነዚያም ከአላህ ጋር ሌላን አምላክ የማይገዙት፤ ያችንም አላህ እርም ያደርጋትን ነፍስ ያለ ህግ የማይገድሉ እና የማያመነዝሩት ናቸው:: ይህንንም የሚሰራ ሰው ቅጣት ያገኛል::
በትንሳኤ ቀን ቅጣት ይደራረብበታል:: በእርሱም ውስጥ የተዋረደ ሆኖ ይኖራል::
ተጸጽቶ የተመለሰና ያመነ መልካምንም ስራ የሰራ ሰው ብቻ ሲቀር እነዚያም አላህ መጥፎ ስራዎቻቸውን በመልካም ስራዎች ይለውጣል:: አላህም እጅግ መሓሪና አዛኝ ነው::} [አል-ፉርቃን: 68-70] ነቢዩም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«الإِسْلَامُ يَهْدِمُ مَا كَانَ قَبْلَهُ، وَالتَّوبَةُ تَهْدِمُ مَا كَانَ قَبْلَهَا».
"እስልምና ከእርሱ በፊት የነበረውን (ወንጀል) ያፈርሳል፤ ተውበትም ከእርሱ በፊት የነበረውን ታፈርሳለች።" ነቢዩ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
«التَّائِبُ مِنَ الذَّنْبَ كَمَنْ لَا ذَنْبَ لَهُ».
«ከወንጀል ተመላሽ ወንጀል እንደሌለው ሰው ነው።»
ይህንን መልዕክት ይዘው የመጡ የቁርኣን አንቀጾችና ሐዲሦች በርካታ ናቸው።
ከፍ ያለውና የጠራው አላህ ሐቅን ሐቅ መሆኑን እንዲያሳየንና መከተሉንም እንዲወፍቀን፤ ጥመትንም ጥመት መሆኑን እንዲያሳየንና መራቁንም እንዲወፍቀን፤ በእኛም ላይ፣ በጸሐፊው ዐብዱልፈታሕም ላይ እንዲሁም በሁሉም ሙስሊሞች ላይ ንፁህ የሆነችውን ተውባ እንዲለግሰን፤ ሁላችንንም ከአሳሳች ፈተናዎች እንዲሁም ስሜትንና ሸይጧንን ከመከተል እንዲጠብቀን እማፀነዋለሁ። እነሆ እርሱ ለዚህ ተማፅኖ የተገባ እውን ሊያደርገው ቻይም እርሱ ነውና።
የአላህ ሰላትና ሰላም በነብያችን ሙሐመድ፣ በቤተሰቦቻቸው፣ በባልደረቦቻቸው እና እስከ ቂያማ ቀን ድረስ በመልካም በተከተሏቸው ላይ ሁሉ ይስፈን።
***
am397v4.0 - 21/04/2026